Bashewam Primary & Junior School 1-8
Ir al canal en Telegram
2 754
Suscriptores
+324 horas
+47 días
+5130 días
Archivo de publicaciones
ለባሸዋም ትምህርት ቤት የተማሪዎች ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡
፡
ውድ የባሸዋም ተማሪዎች እና ወላጆች እንኳን ለ2017ዓም የትምህርት ዘመን እና የትምህርት ቤታችን 25ኛ አመት የምስረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፡ እያልን ከዚህ በታች ባለው መመሪያ መሰረት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንድትልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን ።
የ2017ዓም ትምህርት ከኬጂ (ቅድመ አንደኛ) እስከ 12ኛ ክፍል ነገ ረቡዕ መስከረም 8/2017ዓም ይጀምራል ።
መስከረም 8 - 10/2017ዓም ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን በመሆኑ ወላጆች ልጆቻችሁን ከቀኑ 6:45 ትምህርት ቤት በመምጣት እንድትወስዱ እናሳስባለን ።
ትምህርት ከጠዋቱ 2:30 ስለሚጀመር ተማሪዎች ቀደም ብለው ከጠዋቱ 2:00 በፊት ትምህርት ቤት መገኘት ይኖርባቸዋል ።
ከኬጂ( ቅድመ አንደኛ) እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ፡ ወላጆች ትምህርት ቤት በመምጣት ልጅዎን በየክፍሉ ለተመደቡ ረዳት መምህራን በአግባቡ እንዲያስረክቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
ከቅድመ አንደኛ እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ምሳ እቃ እና ቦርሳቸው ላይ ስማቸው መፃፍ አለበት ።
ሁሉም ተማሪዎች የተማሪ የደንብ ልብስ Uniform አሟልተው መምጣት አለባቸው ፡ ዩኒፎርም ሳይለብስ የሚመጣ ተማሪ ትምህርት ቤት ውስጥ የማናስገባ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን ።
ማንኛውም ተማሪ ከመስከረም 9/2017ዓም ጀምሮ ወደ ትምህርት ቤት የሚገባው የተማሪ መታወቂያ በማሳየት በመሆኑ ልጅዎ መታወቂያ ይዞ(ዛ) ወደ ትምህርት ቤት መምጣቱን(ቷን) እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን ።
ጀማሪ ተማሪዎች መታወቂያቸውን አንገታቸው ላይ ማንጠልጠል አለባቸው ። ወላጆች ትምህርት ቤት ሲመጡ የህፃኑን(ኗን) መታወቂያ መያዝ አለባቸው ።
የትምህርት ቤት የትራንስፖርት ሰርቪስ አገልግሎት ተጠቃሚ ወላጆች ወይም መጠቀም የምትፈልጉ ፡ ረቡዕ መስከረም 8/2017ዓም አገልግሎት መስጠት ስለምንጀምር፡ መጠቀም የምትፈልጉ መስከረም 8 እና 9/2017ዓም በአካል በመምጣት ፋይናንስ ክፍል እንድትመዘገቡ እና ክፍያ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን።
ባሸዋም ትምህርት ቤት ፡ "ሁሌም ለለውጥ ዝግጁ ነን"።
መስከረም 7/2017ዓም
ለባሸዋም ትምህርት ቤት ተማሪዎች ፡ ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡
፡
የትምህርት ቤታችን 25ኛ አመት የምስረታ በዓል እና ለ2017ዓም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሰን - አደረሳችሁ እያልን ፡
፡
የ2017ዓም ትምህርት ከኬጂ እስከ 12ኛ ክፍል ረቡዕ መስከረም 8/2017ዓም የሚጀመር መሆኑን እያሳወቅን፡ ተማሪዎች ለትምህርት የሚጠቀሙባቸው መሳሪያዎች ( ቁሳቁስ) አሟልተው እንዲመጡ እናሳስባለን።
ትምህርት ከጠዋቱ 2:30 ስለሚጀመር ተማሪዎች ቀደም ብለው ትምህርት ቤት መገኘት ይኖርባቸዋል ።
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ!
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን!
መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን !
ለባሸዋም ትምህርት ቤት ተማሪዎች ፡ ወላጆች ወይም ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ ፡
፡
የትምህርት ቤታችን 25ኛ አመት የምስረታ በዓል እና ለ2017ዓም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሰን - አደረሳችሁ እያልን ፡
፡
የ2017ዓም ትምህርት ከኬጂ እስከ 12ኛ ክፍል ረቡዕ መስከረም 8/2017ዓም የሚጀመር መሆኑን እያሳወቅን፡ ተማሪዎች ለትምህርት የሚጠቀሙባቸው መሳሪያዎች ( ቁሳቁስ) አሟልተው እንዲመጡ እናሳስባለን።
ትምህርት ከጠዋቱ 2:30 ስለሚጀመር ተማሪዎች ቀደም ብለው ትምህርት ቤት መገኘት ይኖርባቸዋል ።
ባሸዋም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2016ዓ.ም በተደረገ የውጪ ኢንስፔክሽን ግምገማ በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ ት/ቤቶች ውስጥ የላቀ ውጤት በማስመዝገቡና 3ኛ ደረጃ በመውጣቱ የሰርተፍኬትና የዋንጫ ተሸላሚ በመሆኑ እንኳን ደስ አለን!!!
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
