es
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Ir al canal en Telegram
917
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
-330 días
Archivo de publicaciones
ሚያዚያ 22/2018 ዓ/ም የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የ9 ወር የስራ አፈጻጸም እና የዜጎች ቻርተር ውይይት በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። ፨፨፨፨፨//፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በመክፈቻ ንግግራቸው መምሪያው በዞኑ እየተሰሩ ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት በተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። በቴሌቪዥን ፣በሬድዮ፣በህትመት ውጤቶችና የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች በመጠቀም መረጃን ለህዝቡ ተደራሽ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል። እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ወቅታዊ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን በማጠናከር ተቋሙ በሰው ሀይል ፣በቁሳቁስ እና በበጀት እንዲደገፍ በመደረጉ አበረታች ለውጦች መጥተዋል ብለዋል። በተቋሙ የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመለየት ዘርፊን የማጠናከር ስራ እየተሰራ ሲሆን የጉራጌ የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣበያ ለመክፈት ወደ ተግባር ተገብቶ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አቶ ሸምሱ ገልጿል። 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ፣ፍትሀዊ እና ታማኒነት ያለው እንዲሆን በሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዘርፉ በአጽንኦት እየተሰራበት ስለመሆኑ አስታውቀዋል። በውይይት መድረኩም የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣የመምሪያው ባለሙያዎች ፣የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና የተቋሟት ፍካል ፐርሰኖች ተገኝተዋል።

ሚያዝያ 21/2018 ዓ/ም አካል ጉዳተኞችን እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች በመደገፍ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ባለድርሻ አካላት ሊያግዙ እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህን ያስታወቀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዜጎች ቻርተር የህዝብ ክንፍና አካቶ ትግበራ ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ባካሄደበት ወቅት ነው። የጽህፈት ቤቱ ልማት እቅድ ባለሙያ የሆኑት አቶ መሀመድ ሙደሲር እና አቶ አ/ፈታ ጀማል የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ አመት የዜጎች ቻርተርና የህዝብ ክንፍ ሰነድ አደነደዲሁም አካቶ ትግበራ ሪፖርት አቅርበው ውይይትና ምክክር ተደርጓበታል። ከተነሱት ሃሳብና አስተያየቶች መካከል ተቋሙ በርካታ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚያስተናግድ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው፣ ሁሉም ተቋማት የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ አካቶ መሰራት እንደሚያስፈልግ፣ሞዴል ቀበሌ መፍጠር እንደሚገባ ፤ዕድሜያቸው ለስራ ያልደረሱ ህፃናት ጉልበት ብዝበዛን መከላከል እንደሚገባ፤ከተቋሞች ጋር በቅርበትና በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው በተለያዩ ድርጅቶች ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞችን ክትትልና ደሞዝ ክፍያቸው መከታተል ፤ተግባራትን በወጥነት ማስቀጠል እንደሚገባና አካል ጉዳተኞችን ተቋሞች መቅጠር እንደሚገባቸው የሚሉት የተነሱ ሀሳቦች ናቸው። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ መሀመድ ሳኒ ደንበል በመድረኩ ተገኝተው እንደገለፁት ሞዴል ቀበሌ በመፍጠር ለሌሎች ቀበሌዎች ተሞክሮ በሚሆን መልኩ እንደሚሰሩ ገልፀው፤ የአቅመ ደካሞችን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራ እንዲሁም በተለያዩ ድርጅቶች ቀጥረው የሚያሰሩ ድርጅቶች ዕድሜያቸው ለስራ ያልደረሱ ህፃናት ከመቅጠር እየታረሙ መሄዳቸውና ለውጥ መምጣት መቻሉን ተናግረዋል። አቶ መሀመድ ሳሊ አክለው አረጋውያን እና አካል ጉዳተኛ ዜጎችና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ በሚደረገወ ርብርብ ተወላጅ ባለሃብቶች፣ የልማት ማህበራትን እንዲሁም የረጂ ድርጅቶች እገዛቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበው፤ በመድረኩ የተቋማት የልማት እቅድ ባለሙያ፣ የዜጎች ቻርተር እና የህዝብ ክንፍ አባላት ተሳትፈዋል።

የጉራጌ ዞን አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ ሚያዚያ 21/2018(ወልቂጤ)፦የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ላጫ ጋሩማ የተጓደሉ የአመራር ቦታዎችን መነሻ በማድረግ በሽግሽግና በምደባ የተለያዩ ሹመት ሰጥተዋል!! በዚህም መሰረት፦ 1. አቶ ናስር ሀሰን ፦የጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልፅግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ 2. አቶ ደሳለኝ ፈቀደ ፦ የጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ 3)አቶ ደሳለኝ ገብሬ ፦የአስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል!! የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ለተሿሚዎች መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ይመኛል!!

ሚያዚያ 19/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሚሆኑ የጎምራ ቀበሌ   ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 500 ዶሮ ድጋፍ ተደረገላቸው። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አማካኝነት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ በጎምራ ቀበሌ በተመረጡ ሞዴል መንደሮች በአምስት መቶ ሺህ ብር በጀት በመመደብ ለ50 እናቶች ለእያንዳዳቸወ 10 ዶሮ በድምሩ 500 ዶሮ ተሰራጭቷል። የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና የግብርና ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የእንስሳት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ፈድሉ ኡስማን በድጋፉ ወቅት ተገኝተዋል። መረጃው የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ነው።

ሚያዚያ 19/2018 ዓ/ም ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ለተመዘገቡ ስኬቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አማካኝነት "የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቶ የማስተዋወቅ ፕሮግራም በተካሄደበት ወቅት ነው። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ የሆኑት አቶ አ/ረሂም ርዳ የመክፈቻ ንግግር  ያደረጉ ሲሆን ብልጽግና በቀድሞ ስርዓት ውስጥ የነበሩ ብልሽቶች ምክንያት በህዝብ ግፊት ተጸንሶ በተለይም በወጣቱ ሃይል በርካታ መስዋትነት ተወልዶ ሀገር በቀል የመደመር እሳቤ ይዞ ኢትዮጲያን በኢትዮጰያዊን ትጋትና ውጤት ከድህነት ኋለቀርነት በማላቀቅ ወደ ከፍታ ለማሸጋገር  ወጣት እና ወጣቶች ፓርቲ ነው። ፓርቲያችን ብልጽግና ገና በተመሰረተ አጭር ጊዜ በአንድ የምርጫ ጊዜ ብቻ የኢትዮጰያን ታሪክ የቀየረና እየቀየረ ያለ ታላቅ ፐርቲ መሆኑን አቶ አ/ረሂም ገልጸዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፍታ አረቦ አማካኝነት የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ከወጣቶች ጋር ውይይት ተደርጎበታል። የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ እና የወረዳው የክልል ምክር ቤት እጩ የሆኑት አቶ ኸይሩ መሀመድ በመድረኩ እንደገለጹት ፓርቲው የተለያዩ የፖለቲካ ስብራቶችን በማስተካከል፣ ሀገራዊ ቅቡልነት ያለው የሀገረ መንግስት ስርአት የመገንባት፣ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ኢትዮጵያን የዓለም ተምሳሌት ለማድረግ እየሰራ የሚገኝ ፓርቲ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው  ይህንን ሀገራዊ ህልም እውን ለማድረግ እና የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማፋጠን ወጣቶች  ለብልፅግና ፓርቲ ድምጹን ሊሰጥ እንደሚገባ መልዕክታቸው  አስተላልፈው ወጣቶች ታች በመውረድ አስፈላጊውን የግንዛቤ ስራ መስራት እንዳለባቸው አስታውቀዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራ ስኪያጅ እና የክልል ምክር ቤት እጩ  አቶ አ/ሃፊዝ ሁሴን በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ  የጠራ ግልጽ የሆነ እሳቤ ያለው ለህዝብ ለሰላም ፣ለአብሮነት እንዲሁም ለብሄራዊ ጥቅም የቆመ ኢትዮዽያን በአለም የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የሚሰራ ፓርቲ መሆኑን ገልጸው ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ለተመዘገቡ ስኬቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ እንደነበር  አስገንዝበዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የክልል ምክር ቤት እጩ አቶ ሚፍታ ሁሴን የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ሠላማዊ፣ ፍትሀዊ፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ወጣቶችን ሃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል። አቶ ሚፍታ አክለውም የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምልክት የመደመር የአንድነትና የትብብር እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነታችን ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶ መምረጥ እንዳለባቸው ተናግረዋል። የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ እና የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ወይዘሮ ነጅብያ ማህሙድ ባስተላለፉት መልክት የወረዳችን ወጣቶች በሌሎች አካባቢዎች እንደሚገኙ ወጣቶች ለብልጽግና ፓርቲ መመስረት እና አሁን ለደረሰበት ደረጃ የበኩላቸውን ሚና እንደተወጡ ጠቅሰው ወጣቶች የመምረጥ መብታቸውን በመጠቀም ምርጫቸው ብልጽግና ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ባለፉት አመታት የተመዘገቡ ውጤቶች በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የበኩላቸው ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል።

የሳምንቱ አበይት ዜናዎች ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም 🎤 ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር! በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ  ፅ/ቤት አስተባባሪነት በኢንጌ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የይምረጡኝ  የቅስቀሳ ፕሮግራም  ተካሄዷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሚሆኑ ነፍሰ-ጡር እና አጥቢ እናቶች የዶሮ ስርጭት ተደረገላቸው። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ የኢትዮጵያ ግሎባል ቴካንዶ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ለገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እግር ኳስ ክለብ የመለያ ድጋፍ አደረገ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ባለፉት 5 ዓመታት በመንግስት፣ በባለሀብት፣ በግብረ ሰናይ ድርጅቶችና በማህበረሰብ ተሳትፎ ከ224 ሚሊዮን ብር በማሰባሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የወረዳችን ሰላም እና ደህንነት ለመጠበቅ የሀይማኖት ተቋማት ኃላፊነት የጎላ በመሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጉባኤ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ  የ''ቡና ጠጡ'' የጎዳና ላይ የቅስቀሳ ፕሮግራም በመሀል አምባ ከተማ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ከአጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት መስራት ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከልና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጥላሞ ቀበሌ የበልግ በቆሎ እርሻ ልማት አሁናዊ ሁኔታ በምስል:-

ሚያዚያ 18/2018 ዓ/ም ትላንት ለሊት ከስልጤ ዞን በዘራፊዎች  የተወሰደው አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪን በቁጥጥር ስር ማዋሉን  የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ከወላይታ ሶዶ ወደ ቡታጅራ መስመር  ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3---49700 A.A የሆነው አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ በስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ዘራፊዎች  ሾፌሩንና  ረዳቱን ከግንድ ጋር አስረው ተሽከርካሪውን ይዘው መሰወራቸዉ ገልፀን ነበር። ተዘርፎ የተወሰደው ተሽከርካሪ በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ኢንጌ ከተማ ትላንት ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 4:30 ሰዓት ላይ ተሽከርካሪውን  ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረዳው ፖሊስ ገልጿል። የወረዳው ፖሊስ እንደገለፀው ከሆነ ተሽከርካሪው በሆሳዕና ሌራ ጉብሬ አድርጎ ወደ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ  ወረዳ እንደመጣ አረጋግጫለሁ ብሏል። ተሽከርካሪውን የያዘው ግለሰብ እራት በልቼ እመጣለሁ በማለት ከአንድ ግለሰብ ጊቢ ዉስጥ አቁሞት በሄደበት መያዙ ተገልጿል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን አድኖ ለመያዝ የተጠናከረ ክትትል እያደረገ መሆኑን ከወረዳወ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።