ch
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

前往频道在 Telegram
917
订阅者
无数据24 小时
+47 天
-430 天
帖子存档
ሚያዚያ 19/2018 ዓ/ም ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ለተመዘገቡ ስኬቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አማካኝነት "የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቶ የማስተዋወቅ ፕሮግራም በተካሄደበት ወቅት ነው። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ የሆኑት አቶ አ/ረሂም ርዳ የመክፈቻ ንግግር  ያደረጉ ሲሆን ብልጽግና በቀድሞ ስርዓት ውስጥ የነበሩ ብልሽቶች ምክንያት በህዝብ ግፊት ተጸንሶ በተለይም በወጣቱ ሃይል በርካታ መስዋትነት ተወልዶ ሀገር በቀል የመደመር እሳቤ ይዞ ኢትዮጲያን በኢትዮጰያዊን ትጋትና ውጤት ከድህነት ኋለቀርነት በማላቀቅ ወደ ከፍታ ለማሸጋገር  ወጣት እና ወጣቶች ፓርቲ ነው። ፓርቲያችን ብልጽግና ገና በተመሰረተ አጭር ጊዜ በአንድ የምርጫ ጊዜ ብቻ የኢትዮጰያን ታሪክ የቀየረና እየቀየረ ያለ ታላቅ ፐርቲ መሆኑን አቶ አ/ረሂም ገልጸዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፍታ አረቦ አማካኝነት የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ከወጣቶች ጋር ውይይት ተደርጎበታል። የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ እና የወረዳው የክልል ምክር ቤት እጩ የሆኑት አቶ ኸይሩ መሀመድ በመድረኩ እንደገለጹት ፓርቲው የተለያዩ የፖለቲካ ስብራቶችን በማስተካከል፣ ሀገራዊ ቅቡልነት ያለው የሀገረ መንግስት ስርአት የመገንባት፣ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ኢትዮጵያን የዓለም ተምሳሌት ለማድረግ እየሰራ የሚገኝ ፓርቲ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው  ይህንን ሀገራዊ ህልም እውን ለማድረግ እና የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማፋጠን ወጣቶች  ለብልፅግና ፓርቲ ድምጹን ሊሰጥ እንደሚገባ መልዕክታቸው  አስተላልፈው ወጣቶች ታች በመውረድ አስፈላጊውን የግንዛቤ ስራ መስራት እንዳለባቸው አስታውቀዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራ ስኪያጅ እና የክልል ምክር ቤት እጩ  አቶ አ/ሃፊዝ ሁሴን በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ  የጠራ ግልጽ የሆነ እሳቤ ያለው ለህዝብ ለሰላም ፣ለአብሮነት እንዲሁም ለብሄራዊ ጥቅም የቆመ ኢትዮዽያን በአለም የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የሚሰራ ፓርቲ መሆኑን ገልጸው ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ለተመዘገቡ ስኬቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ እንደነበር  አስገንዝበዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የክልል ምክር ቤት እጩ አቶ ሚፍታ ሁሴን የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ሠላማዊ፣ ፍትሀዊ፣ ነጻና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ወጣቶችን ሃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል። አቶ ሚፍታ አክለውም የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምልክት የመደመር የአንድነትና የትብብር እንዲሁም የምግብ ሉዓላዊነታችን ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶ መምረጥ እንዳለባቸው ተናግረዋል። የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ እና የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ወይዘሮ ነጅብያ ማህሙድ ባስተላለፉት መልክት የወረዳችን ወጣቶች በሌሎች አካባቢዎች እንደሚገኙ ወጣቶች ለብልጽግና ፓርቲ መመስረት እና አሁን ለደረሰበት ደረጃ የበኩላቸውን ሚና እንደተወጡ ጠቅሰው ወጣቶች የመምረጥ መብታቸውን በመጠቀም ምርጫቸው ብልጽግና ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ባለፉት አመታት የተመዘገቡ ውጤቶች በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የበኩላቸው ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል።

የሳምንቱ አበይት ዜናዎች ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም 🎤 ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር! በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ  ፅ/ቤት አስተባባሪነት በኢንጌ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የይምረጡኝ  የቅስቀሳ ፕሮግራም  ተካሄዷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሚሆኑ ነፍሰ-ጡር እና አጥቢ እናቶች የዶሮ ስርጭት ተደረገላቸው። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ የኢትዮጵያ ግሎባል ቴካንዶ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ለገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እግር ኳስ ክለብ የመለያ ድጋፍ አደረገ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ባለፉት 5 ዓመታት በመንግስት፣ በባለሀብት፣ በግብረ ሰናይ ድርጅቶችና በማህበረሰብ ተሳትፎ ከ224 ሚሊዮን ብር በማሰባሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የወረዳችን ሰላም እና ደህንነት ለመጠበቅ የሀይማኖት ተቋማት ኃላፊነት የጎላ በመሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጉባኤ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ  የ''ቡና ጠጡ'' የጎዳና ላይ የቅስቀሳ ፕሮግራም በመሀል አምባ ከተማ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ከአጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት መስራት ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከልና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጥላሞ ቀበሌ የበልግ በቆሎ እርሻ ልማት አሁናዊ ሁኔታ በምስል:-

ሚያዚያ 18/2018 ዓ/ም ትላንት ለሊት ከስልጤ ዞን በዘራፊዎች  የተወሰደው አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪን በቁጥጥር ስር ማዋሉን  የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ከወላይታ ሶዶ ወደ ቡታጅራ መስመር  ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3---49700 A.A የሆነው አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ በስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ዘራፊዎች  ሾፌሩንና  ረዳቱን ከግንድ ጋር አስረው ተሽከርካሪውን ይዘው መሰወራቸዉ ገልፀን ነበር። ተዘርፎ የተወሰደው ተሽከርካሪ በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ኢንጌ ከተማ ትላንት ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 4:30 ሰዓት ላይ ተሽከርካሪውን  ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረዳው ፖሊስ ገልጿል። የወረዳው ፖሊስ እንደገለፀው ከሆነ ተሽከርካሪው በሆሳዕና ሌራ ጉብሬ አድርጎ ወደ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ  ወረዳ እንደመጣ አረጋግጫለሁ ብሏል። ተሽከርካሪውን የያዘው ግለሰብ እራት በልቼ እመጣለሁ በማለት ከአንድ ግለሰብ ጊቢ ዉስጥ አቁሞት በሄደበት መያዙ ተገልጿል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን አድኖ ለመያዝ የተጠናከረ ክትትል እያደረገ መሆኑን ከወረዳወ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

ሚያዝያ 18/2018 ዓ/ም ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር! በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ  ፅ/ቤት አስተባባሪነት በኢንጌ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የይምረጡኝ  የቅስቀሳ ፕሮግራም  ተካሄዷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በመድረኩ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚወዳደሩ የብልጽግና ፓርቲ እጩዎች ፣ የወረዳ አስተባባሪ የክላስተሩ ቀበሌ ደጋፊ አመራሮችና የክላስተር ከሁሉም የማህበራዊ መሠረት የተውጣጡ የፓርቲው አባላት ተገኝተዋል። ዝርዝር ዜና ቀጥለን እንመለሳለን

ሚያዚያ 16/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሚሆኑ ነፍሰ-ጡር እና አጥቢ እናቶች የዶሮ ስርጭት ተደረገላቸው። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አማካኝነት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ግብርና ጽ/ቤት አመቻችነት በደነብ ቀበሌ በሽርና ግራር በተመረጡ ሞዴል መንደሮች ለ50 እናቶች ለእያንዳዳቸወ 10 ዶሮ በድምሩ 500 ዶሮ ተሰራጭቷል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የእንስሳት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ፈድሉ ኡስማን የፕሮግራም ዋና አላማ በወረዳው የሚገኙ ነብሰጡር፣ እናቶች የስርዓተ ምግብ እጥረት ላለባቸው ከሁለት ዓመት በታች ላሉ ህፃናትንና በስርዓተ ምግብ እጥረት እንዳይጎዱ አልሞ እየሠራ ያለ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ፈድሉ ኡስማን አክለውም መቀንጨርንና መቀጨጭን ለመቀነስና የማህበረሰቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በአምስት መቶ ሺህ ብር በጀት በመመደብ ለ50 አጥቢና ነብሰጡር እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት ለእያንዳዳቸወ 10 ዶሮ በድምሩ 500 ዶሮዎች በዛሬው እለት ማሰራጨታቸውን አስታውቀዋል። የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በድጋፉ ወቅት ተገኝተው የስርዓት ምግብ መሻሻል የእናቶችን ጤና ፣የልጆችን መቀጨጭና መቀንጨር የሚከላከል እና ጤናማ ትውልድ ለመገንባት ከፍተኛ ድርሻ ያለው ተግባር በመሆኑ በተቋም ደረጃ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። የዚህ እድል ተጠቃሚ የደነብ ቀበሌ እናቶች የተሰጧቸውን ዶሮዎች በመንከባከብ እና በማባዛት ራሳቸውንና ልጆቻቸውን ከመመገብ ባለፈ በዚህ ፕሮግራም ላልታቀፉ እናቶች ተደራሽ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። በእለቱ ድጋፍ ለተረገላቸው እናቶች በስርዓት ምግብ ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱ ተመላክቷል።