es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 063
Suscriptores
-224 horas
-77 días
+130 días
Archivo de publicaciones
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ምን አከናወነ? ✍️   54 ኢንተርፕራይዞች በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ አስተዳደር ስርዓት (ELMIS) ፕላትፎርም ላይ ተመዝግበዋል፣ ✍️   ስራ ፈላጊ ዜጎችን በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት መተግበሪያ (Ethiopia Labor Market Information System) ላይ ከመመዝገብ አኳያ ወንድ 3218 ሴት 4208 በድምሩ 7436 ለመመዝገብ ተችሏል፡፡ ይህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ለመመዝገብ ከታቀደው 11,227 የስራ አጥ ምዝገባ መጠን አንፃር የ66.14 በመቶ አፈፃፀም የተመዘገበበት ሆኗል፡፡ ✍️   በጠቅላላው ስድስት ወራት ውስጥ በከተማ በነበረ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሦስቱም ዘርፎች ማለትም በግብርና ለ172 ዜጎች (2.3%)፤ በኢንድስትሪ ለ3183 ዜጎች (42%) እንዲሁም በአገልግሎት ለ4223 ዜጎች (55.7%) በድምሩ 7,578 ዜጎች (ወንድ 4380፤ ሴት 3198) የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡ ይህም ሦስቱም ዘርፎች በዕቅድ ተይዞ ከነበረው 8241 የስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር የ92 በመቶ አፈፃፀም ያለው ነው፡፡ ✍️   በጠቅላላው በስድስት ወራት ውስጥ በገጠር በነበረ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሦስቱም ዘርፎች ማለትም በግብርና ለ1010 ዜጎች (59.23%)፤ በኢንድስትሪ ለ155 ዜጎች (9.1%) እንዲሁም በአገልግሎት ለ540 ዜጎች (31.7%) በድምሩ 1705 ዜጎች (ወንድ 915፤ ሴት 790) የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡ ይህም በሦስቱም ዘርፎች በዕቅድ ተይዞ ከነበረው 2707 የስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር የ63 በመቶ አፈፃፀም ያለው ነው፡፡ ✍️   ከ9283 የሥራ ዕድል ውስጥ የሴቶች ድርሻ 3988 ሲሆን ይህም የ43 በመቶ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ከዕቅድ አንፃር ደግሞ የ73 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ✍️   ከ9283 የሥራ ዕድል ውስጥ አጠቃላይ የወጣቶች መጠን 6366 ሲሆን ይሕም ከጠቅላላው የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች ውስጥ የ68.6 በመቶ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ከዕቅድ አንፃር የ72.7 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡ ✍️   ለ41 አካል ጉዳተኛ ዜጎች የሥራ ዕድል እንዲፈጠርላቸው ተደርጓል፡፡ ይህም በዕቅድ ከተያዘው የ77 አካል ጉዳተኞች የስራ ዕድል ተጠቃሚነት አንፃር የ53 በመቶ አፈፃፀም ያለው ነው፡፡ ✍️ ከ973 ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ካደረጉት ውስጥ ወንድ 245 ሴት 631 በድምሩ 876 ተጨማሪ የኮምፒውተር ክህሎት ስልጠና የወሰዱ ናቸው፡፡ ✍️ በብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ከ973 ሰልጣኞች ውስጥ ከ27 ሰልጣኞች ማቋረጥ በስተቀር ቀሪዎቹ 946 ወጣቶች የስራ ትስስር ተፈጥሮላቸዋል፡፡ ✍️ ቢሮው ከቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት(LLRP) ጋር በመተባበር ለ15 በአስተዳደሩ ገጠር ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ወንድ 46 ሴት 146 በድምሩ ለ192 ዜጎች ለእያንዳንዱ ኢንተርፕራይዝ 500,000 ሺህ ብር በድምሩ 7.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጎ ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል። ✍️ ቢሮው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር የሚሰራ ግራንድ ግሩፕ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመቀናጀት በኢ-መኒ ዲጂታል ፋይናንስ በሁሉም ወረዳዎች 40 ኢንተርፕራይዞች በአጠቃላይ 200 ዜጎችን ወደ ስራ ለመግባት ዝግጁ ሆነው ተደራጅተዋል።

በድሬዳዋ አስተዳደር ከተለያዩ ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የአስተዳደሩን ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን የ2018 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ፤ በቢሮው እንዲሁም በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የተከናወነ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ቀርቦም ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል። በመጨረሻም የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ የቀረበው ሪፖርት አቀራረቡንና የተከናወኑ ስራዎችን አድንቀው በቀጣይ ሊተኮርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገባቸውን ጉዳዮች ሀሳብና አስተያየቶች አክለው አቅጣጫ ሰጥተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ፤ * በክርስትና እምነት አስተምህሮ የልደት በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ዓ
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ፤ * በክርስትና እምነት አስተምህሮ የልደት በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን ሲል ከሰማየ ሰማያት ወርዶ በከብቶች በረት ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደበት ታላቅ የትኅትና፣ የፍቅር እና የይቅርታ በዓል ነው፡፡ እኛም የጌታችንን ልደት ስናከብር እርስ በእርሳችኝ ይቅርታ በመጠያየቅ፤ እዝነትና ምኅረትን በማድረግ፣ የተቸገሩትን በመርዳት እና ለሀገራችን ሁለንተናዊ ሰላምና ብልፅግና በጎውን በማድረግ ይሁን! መልካም ገና!! አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ

ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ፤ * በክርስትና እምነት አስተምህሮ የልደት በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ዓ
+1
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ፤ * በክርስትና እምነት አስተምህሮ የልደት በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን ሲል ከሰማየ ሰማያት ወርዶ በከብቶች በረት ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደበት ታላቅ የትኅትና፣ የፍቅር እና የይቅርታ በዓል ነው፡፡ እኛም የጌታችንን ልደት ስናከብር እርስ በእርሳችኝ ይቅርታ በመጠያየቅ፤ እዝነትና ምኅረትን በማድረግ፣ የተቸገሩትን በመርዳት እና ለሀገራችን ሁለንተናዊ ሰላምና ብልፅግና በጎውን በማድረግ ይሁን! መልካም ገና!! አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ

በገጠር ክላስተሮች የMobile Trainingን በስፋት በማዳረስ ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ሰፊ የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ:: በድሬደዋ አስተዳደር ከሚገኙ የገጠር ክላስተሮች እና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ ተወካዮች እንዲሁም ከስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ጋር የአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍን በተመለከት የውይይት መድረክ በኮሌጁ ተካሂዷል። በገጠር ክላስተሮች ያለው የተፈጥሮ ፀጋ በመገንዘብ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ማከናወን ያስፈልጋል ያሉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ አክለውም የMobile Training ትግበራን በስፋትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ በሚኖረው ሂደት ክላስተሮችና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ አስተባባሪዎች የሚያስፈልጉ መሰረተ ልማቶችን በማመቻቸት የስልጠናዎችን ውጤታማነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፀዋል:: በኮሌጁ የMobile Training ሊሰጥባቸው በሚያስችሉ ዲፓርትመንቶች ላይ የተለዩ የሙያ መስኮች መኖራቸውን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም በቀጣይ ከገጠር ክላስተር አስተባባሪዎችና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ነባራዊ ሁኔታ ላይ መነሻ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ በተለያዩ ዘርፎች ስልጠናዎች እንደሚሰጡም አመላክተዋል:: በመድረኩ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ በMobile Training በገጠር ክላስተሮች ላይ ያከናወናቸው ተግባራትና ያለውን መልካም ተሞክሮ በኢ/ር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ገለፃ የተደረ ሲሆን በስልጠናው የተመዘገቡ ውጤቶችን ጨምሮ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም ቀርበው በቀጣይ ስልጠናዎች በሚሰጡበት አግባብ ላይም ውይይት ተካሂዷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በ33 ነባርና አዲስ ኢንተርፕራይዞች ላይ ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በተወጣጡ አሰልጣኝ መምህራን የካይዘን ትግበራ ጀመረ፡፡ በዚህም ለኢንተርፕራይዞች ሠራተኞች የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ (ካይዘን) ትግበራ ስልጠና/ድጋፍ በመስጠት ማብቃት እና የመስሪያ/ ማምረቻ ወርክሾፖችን በካይዘን እንዲደራጁ በማድረግ ኮሌጆች ከኢንተርፕራይዞች ጋር የሚኖራቸዉን የስራ ትስስር ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን ሠራተኞች መሰረታዊ የካይዘን እዉቀትና ክህሎትን በኢንተርፕራይዙ ማምረቻ/የስራ ቦታ በመተግበር ደረጃዉን የጠበቀ ማምረቻ ቦታ ለመፍጠር እና በአጠቃላይ የከይዘን ፍልስፍናን በመተግበር የአሰልጣኝ መምህራኑን አቅም በመገንባት የኢንተርፕራይዞችን አላስፈላጊ ብክነቶችን በማስወገድ ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል አቅም የሚፈጥር ትግበራ ይሆናል፡፡ ዳይሬክቶሬቱ ከኮሌጆች ጋር በመሆን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ በመስጠት በአስተዳደሩ ጉልህ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን  የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና ብቁ የሆነ የሰዉ ሐይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ ለማድረግ ድጋፍ እየሰጠ ይገኛል፤ በዚህም በአስተዳደሩ ዘጠኙም ወረዳዎች ለሚገኙ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ለሚደረግላቸው  ኢንተርፕራይዞች የድርጊት መርሀ ግብር በማዘጋጀት ወደ ትግበራ መገባቱን የቢሮው ም/ኃላፊና የኤጀንሲው ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

🇪🇹የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት፣ ለላቀ ተጠቃሚነት! 👉 የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (ELMIS) በኢትዮጵያውያን በልጽጎ ለኢትዮጵያውያን የቀረበ ግዙፍ እና ሁሉን አቀፍ የዲጂታል መረጃ ስርዓት ነው፣ 👉የሀገራችንን የሰው ኃይል መረጃ አያያዝና አስተዳደርን በእጅጉ የሚያዘምን እና ሥራን ከሠራተኛ ጋር በቀለለ፣ ፈጣን እና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ማገናኘት ያስችላል፣ 🔑ቁልፍ ፋይዳዎች ✅የሥራ ስምሪት ሥራን ማዘመን፦ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን እንዲሁም የርቀት ሥራዎችን  በአንድ ላይ አጣምሮ አገልግሎት ጊዜውን በዋጀ መልኩ መስጠትና ማግኘት ያስችላል፣ ✅ፍትሃዊ ተደራሽነት፦ ስርዓቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ እና ከሰው ንክኪ ነፃ እንዲሆን ተደርጎ የበለፀገ በመሆኑ፣ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ በእኩል አገልግሎት መስጠት ያስችላል፣ ✅መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ፦ የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ከሀገራዊ የልማት ፍላጎት ጋር እንዲጣጣም ወሳኝ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል፣ 🚪23+ የዕድል በሮች በአንድ ጣሪያ ስር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት አንድ ስርዓት ቢሆንም፣ በውስጡ ከ23 በላይ ንዑስ አገልግሎቶች አሉት። አብዛኞቹ አገልግሎቶች ለዜጎች በነፃ የቀረቡ ናቸው። 🧭የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ ዋና ዋና ንዑስ አገልግሎቶች በጥቂቱ ✅የሥራ ስምሪት፦ የሀገር ውስጥ፣ የውጭ ሀገር እና የርቀት (Remote) ሥራ ዕድሎችን ማግኘት አስችላል፣ ✅የሰው ኃይል አስተዳደር፦ የተቋማት የሰው ሃይል አስተዳደርና አቅም ግንባታ ሥራዎችን ለማሣለጥ ሁነኛ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል፣ ✅የሙያ ብቃት ማረጋገጫ፦ የሙያ ብቃት ምዘናና እውቅና እና የሳይኮሜትሪክ ምዘና መስጠት ያስችላል፣ ✅የብድር አገልግሎት፦ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት በመስራትና በሳይኮሜትሪ ምዘና በመታገዝ ያለ ማስያዣ የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀዋል፣ ✅የውጭ ሀገር ባለሙያዎች የሥራ ፈቃድ እና እድሳት፦ በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች ለማይሸፈኑ የሙያ መስኮች የውጭ ሀገር ባለሙያዎች ፍቃድና እድሳት ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ አግባብ መስጠት ያስችላል፣ ✅የዲጂታል ኢንተርፕራይዝ ምስረታና የዲጂታል ግብይት፦ ስርዓቱ በበይነ መረብ የማደራጀት ሥራ ከመስራቱ ባሻጋር ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎታቸውን ማስተዋወቅና መሸጥ የሚያስችላቸውን ዕድል ይዟል፣ ✅ ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ፦ ስርዓቱ ከተለያዩ የማስታወቂያ ድርጅቶች ጋር የተሳሰረ በመሆኑ ባልዎት የትምህርት ማስረጃና የሥራ ልምድ ማስታወቂያዎች በቀላሉ እንዲደርስዎ ያስችላል፣ 📊በስርዓቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች ስርዓቱ ተጠናቆ ወደ ሥራ ከገባበት እለት ጀምሮ ባለፉት አራት ዓመታት ከ3.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በስርዓቱ ተመዝግበዋል። ከዚህ ውስጥ፡- ✍️ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፣ ✍️በርካታ ዜጎችም በሀገር ውስጥና በርቀት የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ ሆነዋል፣ 🏢የተቋማት ተሳትፎ 👉 የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት: 45 ሺህ የግብርና ናሙና ቆጠራ ባለሙያዎችን ስርዓቱን ተጠቅሞ በመመልመልና በመቅጠር ፈር ቀዳጅ ነው፣ 👉 የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ ሚድሮክ ኢትዮጵያ እና ኦቪድን ጨምሮ በርካታ ተቋማት ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን መልምሎ ለተቋማቸው ለመቅጠር ስርዓቱን እየተጠቀሙበት ይገኛል፣ 🚪 የዕድሉን በር ቁልፍ በእጅዎ ያስገቡ! ✍️ከሥራ ዕድል አኳያ ስርዓቱ ለሁሉም ክልሎች እኩል ዕድል የሚሰጥ ነው፡፡ ለየትኛውም ክልልና አካባቢ የተሰጠ ኮታ የለም፡፡ ✍️በየትኛውም አካባቢም ሆነ የትምህርት ደረጃ ሁሉም እኩል እድል አለው፡፡ ይህም ማለት በስርዓቱ ላይ መመዝገብ ማለት የሀገር ውስጥ፣ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት፣ የርቀት ሥራን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ዕድሎችን በቀላሉ ለማግኘት የሚያስችል ቁልፍ በእጁ ማስገባት ማለት ነው። 📝እንዴት መመዝገብ ይቻላል? 1️⃣ በራስ መመዝገብ፦ lmis.gov.et የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም የእጅ ስልክዎን ጨምሮ መመዝገብ ይችላሉ፣ 2️⃣ በሌሎች እርዳታ መመዝገብ፦ በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች በመሄድ በማዕከሉ ባለሙያዎች እገዛ መመዝገብ ይቻላሉ፣ 📌የመመዝገቢያ መስፈርት: 👉 ዕድሜ፦ ከ15-65 ዓመት 👉 የትምህርት ደረጃ፡ በየትኛውም የትምህርት ደረጃ ላይ ያለ ሰው መመዝገብ ይችላል ⚠️ማስታወሻ ✅  ስርዓቱ ይዞ የሚመጣውን ዕድሎች ሁሉ ለመጠቀም ግላዊ መረጃ፣ የትምህርት እና የሥራ ልምዶችን በአግባቡ ማያያዝዎን ልብ ይበሉ! ታህሳስ 26/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

መንግስት በጎዳና ሕይወት ኑሮዋችንን ከመምራት ታድጎናል ሲሉ በዐ2 እና 03 ወረዳ በክረምት በጎ ፈቃድ መኖሪያ ቤት ተሰርቶ የተሰጣቸው አረጋውያን ተናገሩ። የድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ በ02 እና በ 03 ወረዳ ያስገነባቸው ሦስት የአቅመ አካማ ቤቶችን መርቆ አስረክቧል ። ቤቶቹን መርቀው ያስረከቡት የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ፤ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እና የቢሮው ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የወረዳ አመራሮች ናቸው። በወቅቱ የአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት ተቋማቸው በ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዛሬ መርቀው ያስረከቧቸውን ሦስት ቤቶች ጨምሮ ቢሮው ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር ጠቅላላ ሰባት (7) ቤቶችን ገንብቶ ለአቅመ ደካማ እማወራዎች እና አባወራዎች ማከረከባቸውን ገልፀዋል። ኃላፊው አያይዘውም ዛሬ በ02 እና 03 ወረዳ የተረከቡት ቤቶችም ጠቅላላ ከስምንት መቶ (800)ሺ ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ገልፀዋል ። ቤቶቹን የተረከቡት የ 03 ወረዳ ነዋሪ እማወራዎች ልጆቻቸውን የአገር ዳር ድንበር ለማስከበር ግዳጅ ልከው የተሰውባቸው እና በመኖሪያ ቤት እጦት በሰው በረንዳ ተጠግተው የሚኖሩ እና የጎዳና ሕይወት መምራት የጀመሩ መሆኑን አስታውሰው ዛሬ ግን መንግስት ይሄን ቤት ገንብቶ በመስጠቱ ኑራችንን በጎዳናና በሰው በረንዳ ከመምራት ታድጎናል ሲሉ ደስታቸውን ገልፀዋል። ቤቶቹን ያሰሩት የስራ ክህሎት ቢሮ ተጠሪ ተቋማት የሆኑት የድሬዳዋ ፖሊቲክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቤት ዕቃ እና የምግብ ግብዓት ለአረጋዊያኑ አጋርተዋል። ©️ DireTvአማርኛ |ታህሳስ 25 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በተዘጋጁ የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተናዎች ላይ ያተኮረ መድረክ ተካሄደ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከትኩረት ዘርፍ መ/ቤት ከተውጣጡ ባለሞያዎች እና የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የእሴት ሰንሰለት ትንተና አዘገጃጀት ላይ ከዚህ በፊት በተሰጣቸው ስልጠና መሰረት የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ገለጻ ተደርጎባቸዋል፡፡ ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ አዋጭ ቴክኖሎጂ ለኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መሆኑ ይታወቃል በዚህም የምርት ወይም የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት በመተንተን ክፍተቶችን በመለየት እና ለክፍተቶቹም የቴክኖሎጂዎችን መፍትሄ ለማስቀመጥ የእሴት ሰንሰለት ትንተና ሰነዶች ተዘጋጅተዋል፡፡ በመሆኑም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ዋና አላማ ከትኩረት መ/ቤት የተውጣጡ የተለያዩ ባለሞያዎች የዘርፋቸውን እሴት ሰንሰለት ማዘጋጀታቸውን ተከትሎ በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ሙያዊ አስተያየት እንዲሰጥበት በማድረግ ሰነዱን በማዳበርና በማስተዋወቅ በሚለዩት ቴክኖሎጂዎች የኢንተርፕራይዞችን፣ የተቋማትን እና የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት በመጨመር ለበርካታ ዜጎች የሥራ-ዕድል ለመፍጠርና እና የገቢ መጠን ለመጨመር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የኤጀንሲው ኃላፊና የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለአስተዳደሩ አንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመሰጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፤ በስልጠና መክፈቻው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት  ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለፁት፤ ቢሮው ለነባርና አዳዲስ የአንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች አዲሱን እሳቤ ለማሰረፅና ተቀናጅቶ በመስራት ወደ ተግባር ለማውረድ የተለያዩ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኙና በዚህም ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ የተቀረፁ እሳቤዎች ወደ መሬት ወርደው የልማት ፀጋዎቻችንን አልምቶ መጠቀም በሚያስችል አግባብ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል። በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደገለጹት፤ የዘርፉ የአዲሱ እሳቤዎች ዓላማ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻር ያሉ ማነቆዎችን በመፍታትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የታለመውን ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ማድረግ ሲሆን የአንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች የእሳቤዎቹን ዓላማና ግብ በአግባቡ ተረድተው ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ታስቦ ስልጠው መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ የእሳቤዎቻችን ዘረመል (DNA) የሥራ እድል ፈጠራ ጉዳዮች 1.  ከኢኮኖሚ እድገት ጋር የሚተሳሰር 2.  ከፍተኛ የማደግ አለኝታ ያላቸው ኢንተርፕራይዞች ላይ ማተኮር 3.  ክህሎት መር 4.  የእሴት ሰንሰለትን 5.  ውጤታማ የቢዝነስ ልማት ስርአት መቅረፅና መዘርጋት 6.  የኢንተርፕሩነርሽፕ ስልጠና ለስራ ጀማሪዎች 7.  ቤተሰብና ማህበረሰብ የማምረቻና የምርታማነት ማእከል 8.  የፈጠራ/አዲስ የስራ ሀሳብ መኮትኮት ዋነኛ መለያው 9.  መንግስታዊ ድጋፎችን በፈጠራ 10.  ቴክኖሎጂ መር የገበያ መሰረተ ልማት 11.  የቢዝነስ ሀሳብ ባንክ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛና EASTRIP ፕሮጀክት የGRM ኮሚቴ የ2018 የሁለተኛ ሩብ አመት መደበኛ ስብሰባውን አከናወነ፡፡ በመድረኩ ላይ በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲ
+5
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛና EASTRIP ፕሮጀክት የGRM ኮሚቴ የ2018 የሁለተኛ ሩብ አመት መደበኛ ስብሰባውን አከናወነ፡፡ በመድረኩ ላይ በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም በኮሌጁ በኩል ያለው የቅሬታ ሰሚ እንዲሁም በ EASTRIP ፕሮጀክት በኩል ያለው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የልህቀት ማእከል ግንባታው ምንም ችግር ሳይፈጠር እና ማህበረሰቡ ላይ ተጽእኖ ሳይኖረው በአግባቡ ተገንብቶ ለሚፈለገው አላማ እንዲውል እንዲሁም ችግር ቢከሰት በተገቢው መንገድ እንዲፈታ እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ ትልቅ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በኮሌጁ በኩል ያለው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ በኮሌጁ በኩል እንዲሁም በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የሚኖሩ ቅሬታዎችን በመፍታት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን ማስቀረት ተችሏል ያሉ ሲሆን አያይዘውም ባለፉት አመታት በኮሌጁ፣ በኮሚቴው እንዲሁም በፕሮጀክቱ በኩል የተሰሩ ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን የተናገሩ ሲሆን ባለፉት አመታት የተገኘውን ልምድ በመጠቀም በቀጣይም የሚሰሩ ስራዎች በሙሉ የማህበረሰቡን፣ የኮሌጁ እንዲሁም የመንግስትን ፍላጎት በተከተለ መልኩ ሊሰራና ችግሮችም በተገቢው መንገድ እንዲፈቱ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ በዛሬው እለት በተደረገው የሁለተኛ ሩብ አመት መደበኛ ስብሰባ የኮሌጁ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የ2018 እቅድ፣በመጀመሪያና በሁለተኛ ሩብ አመት የተሰሩ ስራዎች በአቶ ቴዎድስ አስፋው በኩል የቀረበ ሲሆን እንዲሁም በፕጀክቱ በኩል የተሰሩ ስራዎች የቐረበ ሲሆን በእለቱ የተገኙ የኮሚቴው አባላት የተሰሩ ስራዎች አመርቂ ናቸው በቀጣይም ይህን ተሞሮ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ