1 064
Suscriptores
-124 horas
-47 días
+530 días
Archivo de publicaciones
#ዜና /አምራች ድርጅቶች በአስተዳደሩ ልማት በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ተገለፀ
#DGC ታህሳስ 23/2018
የኮካኮላ ቤቬሬጅ አፍሪካ በኢትዮጵያ በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የሰራውን የኮካ ሰፈር የወንዝ ተፋሰስ ልማት አስመርቋል።
በመድረኩ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ መንግስት በሚከተለው ሰው ተኮር ስትራቴጂ በተለይም የዜጎችን በፅዱና ምቹ ሁኔታ የመኖር መብት የማረጋግጡ ስራዎች በሰፊው እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ለዚህም ማሳያ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች በልዩ ሁኔታ ገጠርን ጨምሮ እየተከናወነ ያላው የኮሪደር ልማት ተጠቃሽ እንደ ሆነ ተናግረዋል።
ተቋሙ አሁን እንዳከናወነው የወንዝ ዳር ልማት ሁሉ በተለያዩ ዘርፎች ማስቀጠል እንዳለበት ሌሎች በአስተዳደሩ ያሉ የተለያዩ ፋብሪካዎች የኮካኮላን ተሞክሮ መውሰድ ተመሳሳይ ተግባር መፈፀም እንዳለባቸው ምክትል ከንቲባው ጠቁመዋል።
የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊና የወረዳ 5 ደጋፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ፋብሪካው በወረዳው የነዋሪዉን ማህበራዊ ቀውስ ሲያስከትል የቆየ የነበረ ስፍራን በዚህ መልኩ እንዲያምር ማድረጉ የሚያስመሰግነወደ እንደሆነና በቀጣይ ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት የስራ እድል እንዲፈጠር ይሰራል ብለዋል።
አቶ ንጉስ አለሙ ገብረሚካኤል የኮካ-ኮላ ቤቨሬጅስ አፍሪካ በኢትዮዽያ የህዝብ ግንኙነት፣ ኮሙኒኬሽን እና ሰስተነብሊቲ ዳይሬክተር አካባቢው የቆሻሻ መጣያ ከመሆን ባለፈ እኩይ ተግባራ የሚፈፀምበት እንደነብር ገልፀዋል።
ይንን በመመልከት ብሎም ለማህበረሰቡ መስጠት የሚገባውን ማህበራዊ አገልግሎት ግዴታ ለመወጣት ፕሮጀክቱ ማከናወኑን፣ በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ 1ኪሎ ሜትር በላይ አንደሚጠጋ ተናግረዋል።
ፋብሪካው ድሬዳዋ ላይ 60 አመት ቆይታ እንዳለው የገለፁት አቶ ንጉሱ በቀጣይም ከመንግስት ጎን በመሆን የማህበረሰቡን ችግር የሚቀርፉ ስራዎችን ለማከናወን ጥረት እንደሚያደርግ ገልፀዋል።
በዳግማዊ ፍቃዱ
ፎቶ፦አገኘሁ ሸዋረጋ
ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.diredawacommunication.org
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/DGCOMU
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/@Direcommunication
ቴሌግራም፦ https://t.me/DDGCAB
ትዊተር፦ https://twitter.com/DawaOffice
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በድሬዳዋ አስተዳደር ከሴክተር ተቋማትና ከወረዳ አንድ ማዕከላት ለተወጣጡ የባለድርሻ አካላት አዲስ በተሻሻለው የውጭ አገር ስራ ስምሪት አዋጅ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ለባለድርሻ አካላት አዲስ በተሻሻለው ህጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1389/2017 ላይ በባለሙያዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
በዚህም ተሳታፊዎች አዲሱን አዋጅ በመረዳት በህገወጥ መንገድ ለስራ ወደ ውጭ አገር መላክ ወንጀልን በመከላከል ዜጎች ህጋዊ መንገድን ብቻ ተከትለው እንዲሄዱ ከቢሮው ጋር በቅንጅት ለመስራት መግባባት ተፈጥሯል፡፡
በማጠቃለያውም ሥራ ፈላጊው ህብረተሰብ ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሞዴል ኢንትርፕራይዞች ባዛር በበዓላት ወቅት የሚታየውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ከፍተኛ አሰተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተገለፀ።
መጪውን የገና በዓል በማስመልከት የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ከአሜሪካን ኮሌጅ ኦፍ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር የሞዴል ኢንተር ፕራይዞች ኤግዚብሽን እና ባዛር አዘጋጅቷል ።
በባዛሩ ከ 60 በላይ ኢንተርፕራ ይዞች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ይዘው ቀርበዋል ።
የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት ኢንተር ፕራይዞቹ ይዘውት የቀረቡት ምርትና አገልግሎት በበዓላት ወቅት የሚታየውን የዋጋ ንረት ከማረጋጋት አኳያ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል ::
ኃላፊው አክለውም ይህ ኤግዚብሽን እና ባዛሩ ኢንተርፕራይዞቹ የሚገጥማቸውን የገበያ ተደራሸነት በመቅረፍም በኩልም ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል ::
የከንቲባ ጽ /ቤት እና የካቢኒ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን በበኩላቸው ኢንተር ፕራይዞችን ከማበረ ታታት እና ገበያን ከማረጋጋት አንፃር ቢሮው እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ እንደሆነ ተናግረዋል።
የሴት ኢንተር ፕራይዞችን ለማበረታታት በልዩ ትኩረት እየሰራ የሚገኘው የአሜሪካን ኮሌጅ ኦፍ ቴክኖሎጂ የማርኬት ሊንኬጅ ልዩ ባለሙያ አቶ ኤርሚያስ መኮንን በባዛሩ ላይ ለተሳተፉት ሴት ኢንተርፕራይዞች ፕሮጀክታቸው በቀጣይም የሚደግፍ መሆኑን ገልፀዋል::
በባዛሩ ላይ የተሳተፉ የኢነትርፕራይዝ ባለቤቶች በበኩላቸው በባዛሩ ላይ መጪውን በዓል በማስመልከት ምርታቸውን ከመደበኛው ገበያ ዋጋ ባነሰ ሂሳብ ማቅረባቸውን በመጠቆም ህብረተሰቡ እንዲሸምት ጥሪ አቅርበዋል።
በከዚራ ጎዳና ላይ የተከፈተው ባዛር እስከ ታህሳስ 28 / 2018 ዓ.ም የሚቆይ እንደሆነም በወቅቱ ተገልጿል ::
©️ DireTvአማርኛ |ታህሳስ 23 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
+4
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በተለያየ ዘርፍ ስኬታማ መሆን የቻሉ ሴቶችን በመጋበዝ ለኮሌጁ ሴት አሰልጣኝ መምህራንና ሴት ሰልጣኞች ልምድና ተሞክሮ የሚቀስሙበት መድረክ አካሂዷል::
በመድረኩ ተገኝተው በህይወታቸው ያካበቱትን ከፍተኛ ልምድና ተሞክሮ ለተሳታፊዎች ማካፈል የቻሉት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ድሬደዋን በመወከል የፓርላማ አባል የሆኑት ክብርት ቢፍቱ መሀመድ(ዶ/ር) እና በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ መምህርት የሆኑት ዶ/ር ፈቲያ እንዲሁም በኮሌጁ ለረጅም አመታት በብቃት እያሰለጠኑ የሚገኙት አሰልጣኝ መምህርት ለምለም ገ/ስላሴ ሲሆኑ በዚህም በተለያዩ የስራ ሀላፊነቶች ላይ ተሰማርተው ስኬት እንዲያስመዘግቡ ያስቻላቸው የህይወት ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች አካፍለዋል::
ኮሌጁ የተቋቋመበትን ዓላማና ተልዕኮ ለማሳካት በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ የሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም የዚህ መድረክ ዋና ዓላማም ከፍተኛ ጫናን ተቋቁመው ስኬታማ የሆኑ እንዲሁም በተሰማሩበት ዘርፍ ለሀገር እድገት የድርሻቸውን እያበረከቱ ከሚገኙ ሴት እህቶቻችን ተሞክሮ እንዲወስዱ ለማድረግና ወደራሳቸው ህይወት በመውስድም በተግባር እንዲጠቀሙበትም ለማስቻል መሆኑንም ገልፀዋል::
በእለቱ በተካሄደው መድረክ በተሳታፊዎችና በተጋባዥ እንግዶች መካከል ነፃ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን በዚህም ሴቶች ሚገጥሟቸውን አስቸጋሪ የህይወት ጎዳናዎች በራስ መተማመን፣ በብልሃትና በጥበብ መሻገር አሸናፊ ሆነው እንዲወጡና የህይወት መንገዳቸውንም በስኬት እንዲመሩ የሚያግዛቸው መሆኑን ምክር ለግሰዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስራ አመራር ኮሚቴ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያው ስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ100 ቀን ዕቅድ ትግበራ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያው ስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም የተመዘገቡ ውጤቶችንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመንቀስ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን እና የ100 ቀን ዕቅድ ትግበራ ለማሳካት ሁሉም የቢሮው ማህበረሰብ በትጋት እንዲተገብር ድጋፍና ክትትል እንድያደረግ ስምሪት መሰጠቱ ተገልጿል ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት እንደ ሴክተር በመደበኛ ከታቀደው ተጨማሪ ዝግጁነት በማከል የ100 ቀን ዕቅድን በማሳካት በዘርፉ የአስተዳደሩ ነዋሪን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ሴቶችን በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች እንዲበቁ ማስቻል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የሴቶችን የአመራር ክህሎት፣ በራስ መተማመን እና የውሳኔ አሰጣጥ ችሎታን ማሳደግ ላይ ያተኮረ የLeadership ስልጠና ሰጥቷል።
በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ በትኩረት ከሚያከናወኑ ተግባራት መካከል ሴቶችን በልዩ ሁኔታ የማብቃትና በሁሉም ዘርፎች የመሪነት ሚና ላይ በንቃት እዲሳተፉ ማስቻል እንደሆነ የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ወቅቱ ሴቶችን ለማብቃት ዘርፈ ብዙ ስራዎች የሚከናወኑበት ጊዜ በመሆኑ ሴት እህቶቻችን አቅማቸውን ለማሰየት ጥሩ መደላድል የሚፈጥርላቸው መሆኑንም ገልፀዋል::
በእለቱ የተዘጋጀው የLeadership ስልጠና በኮሌጁ ለሚገኙ ሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ከየዲፓርትመንቱ ለተወጣጡ ሴት ሰልጣኝ ተማሪዎች ከሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በመጡት ዶ/ር ፈትያ አማካኝነት ስልጠናውን በጥሩ ሁኔታ መስጠት የተቻለ ሲሆን በቀጣይም መሰል ስልጠናዎችን በተከታታይ በማዘጋጀት ሲቶችን የማብቃት ተግባራት እንደሚከናወኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
ባሉበት የሒሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያስተሳስሩ!
****
ውድ የባንካችን ደንበኞች፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኅዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መመሪያ መሠረት፤ ሁሉም ደንበኞች የባንክ አገልግሎቶች ለማግኘት እና ሒሳብ ለማንቀሳቀስ የፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል::
በዚህ መሠረት ባንካችን ደንበኞች ወደቅርንጫፍ ቀርበው የሒሳብ ቁጥራቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ከሚያጣምሩበት አሠራር በተጨማሪ ባሉበት አገልግሎቱን የሚያገኙበትን አማራጭ አመቻችቷል።
በመሆኑም ከታች በተቀመጠው የአሠራር ቅደም ተከተል መሠረት የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥርዎን (16 አሀዝ-FAN Number) በማስገባት የባንክ ሒሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያጣምሩ::
1. ይህን ማስፈንጠሪያ 👉 https://cbefayda.cbe.com.et/ በመጫን/ በማስገባት ገፁን ይክፈቱ፣
2. የሂሳብ ቁጥርዎን አስገብተው ‘Get OTP’ የሚለውን ይጫኑ፣
3. ሒሳብ ሲከፍቱ ያስመዘገቡትን የስልክ ቁጥር በሚጠቀሙበት የተንቀሳቃሽ ስልክ የተላከልዎትን የአንድ ጊዜ የሚስጥር ቁጥር (OTP) አስገብተው “Verify OTP” የሚለውን በመጫን ያረጋግጡ፣
4. “Log with OTP” የሚለውን ይጫኑ፤
5. የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥርዎን (16 አሀዝ-FAN Number) አስገብተው ‘Get OTP’ የሚለውን ይጫኑ፣
6. በድጋሚ በተንቀሳቃሽ ስልክዎ የተላከልዎትን የአንድ ጊዜ የሚስጥር ቁጥር (OTP) አስገብተው “Verify” የሚለውን በመጫን ያረጋግጡ፣
7. “Allow” የሚለውን ይጫኑ፣
8. “Accept and Update” የሚለውን ሲጫኑ “Update complete. Pending Approval” የሚል መልእክት ይመጣልዎታል። ጨርሰዋል።
+4
የሙያ ብቃት ምዘናና ሰርተፍኬሽን ሥራ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጅታል ሥርዓት ሊገባ ነው
የሙያ ብቃት ምዘና ሰርተፍኬሽን አሰራር ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት እና አሰራሩን ለማዘመን፤ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት አካል ሆኖ የለማውን ዲጂታል የሙያ ብቃት ምዘናና ሰርተፍኬሽን ስርዓት ን ወደ ተግባር ማሸጋገር የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ለዘርፉ አስፈጻሚ አካላት መስጠት ተጀምሯል፡፡
በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የምዘና ማዕከላት መረጃ ያካተተው ይህ ስርዓት የሙያ ብቃት ምዘናንም ጭምር ከማንዋል በተላቀቀ መልኩ መስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ አዝመራ ከበደ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከብቃት ምዘና ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን የሚቀርፍ አሰራር በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት በኩል ለምቶ ለትግበራ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ይህም ባለፉት ዓመታት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በማንዋል በታገዘ መልኩ ሲሰጥና ለተለያዩ ብልሹ አሰራሮች ተጋላጭ የነበረው የሙያ ብቃት ምዘናና ሰርተፍኬሽን ሙሉ በሙሉ ወደ ድጅታል ስርዓት ማሸጋገር ያስችላል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የለማውን ሲስተም ለመተግበር ዋነኛ ሚና ያላቸው የሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የሙያ ብቃት ምዘና ኤጀንሲ የሥራ ሃላፊዎች እና የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ባለሙያዎች ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ታህሳስ 21/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ወጣቶችን በዲጂታል ክህሎት ማስታጠቅ የዲጂታል ኢኮኖሚውን ግንባታ በአጭር ጊዜ እውን ለማድረግ እደሚረዳ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ ሰልጣኝ ተማሪዎች የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" (5 Million Ethiopian Coders) ስልጠና እንዲወስዱ ለማስቻል የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ::
የ5 ሚልዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና ዋና አላማ ወጣቶች የኮዲንግ ክህሎት በመማር የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ስራዎችን እንዲያገኙ ወይም የራሳቸውን ፈጠራ በመጠቀም ሀብት እንዲፈጥሩ ለማስቻል እንደሆነ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም የICT ዘርፉ የሀገራችን ኢኮኖሚ ሙሰሶ ተደጎ በትኩረት እየተሰራበት በመሆኑን ጭምር ወጣቶች በቀጣይ ህይወታቸው ለውጥ ሊያመጡ የሚያስችሉ መሰል ክህሎቶች ላይ ትኩረት አድርገው ቢሰሩ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋልም ብለዋል::
ሰልጣኞች ከመደበኛ ትምህርትና ስልጠናቸው ጎን ለጎን ጊዜው የሚሰጠንን ዲጂታል ክህሎቶች መቅሰም ተፈላጊነታቸውን ይበልጥ ያሳድጋል ያሉት ደግሞ የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊ የሆኑት አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ መንግስት በነፃ ለዜጎቹ ያመቻቸውን ይህን የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" ስልጠና በአግባቡ በመጠቀም የክህሎት ባለቤትና ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉም አስገንዝበዋል::
ሰልጣኞች የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" (5 Million Ethiopian Coders) ስልጠናውን ሲወስዱ ከምዝገባው ጀምሮ ስልጠናውን ተከታትለው ሰርተፊኬት እስከመውሰድ ድረስ ያለውን ሂደት በቅደም ተከተል ግንዛቤ የሰጡት በኮሌጁ የICT ዲፖርትመንት ተጠሪ የሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ፉንታሁን ሲሆኑ በቀጣይም ለዚሁ አላማ በተዘጋጁ የዲፖርትመንቱ Labና በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት ሰልጣኞች የኮዲንግ ስልጠናውን በኮሌጁ እንደሚወስዱ ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የሴቶች ክንፍ የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ።
የጥያቄና መልሱ መርሃግብር አላማም የብልፅግና ፓርቲ ሴት አባላትን ለማብቃት ሲሆን በዚህም በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች የፓርቲውን ዕሳቤ የተከተለ ተሳታፊነትን ማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶታል።
የጥያቄና መልስ ውድድሩ ጥያቄዎች በዋነኝነት በብልፅግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ሴቶች ክንፍ መተዳደሪያ ደንብ ዙሪያ ላይ ሲሆን ሰፊ ሀገራዊ ጉዳዮችንም የዳሰሰ ሆኗል።
ለጥያቄና መልስ ውድድሩ አሸናፊዎች ማበረታቻ ሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የሴቶች ክንፍ የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ።
የጥያቄና መልሱ መርሃግብር አላማም የብልፅግና ፓርቲ ሴት አባላትን ለማብቃት ሲሆን በዚህም በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች የፓርቲውን ዕሳቤ የተከተለ ተሳታፊነትን ማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶታል።
የጥያቄና መልስ ውድድሩ ጥያቄዎች በዋነኝነት በብልፅግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ሴቶች ክንፍ መተዳደሪያ ደንብ ዙሪያ ላይ ሲሆን ሰፊ ሀገራዊ ጉዳዮችንም የዳሰሰ ሆኗል።
ለጥያቄና መልስ ውድድሩ አሸናፊዎች ማበረታቻ ሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
