es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 077
Suscriptores
+524 horas
+107 días
+530 días
Archivo de publicaciones
በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎች ወጣቶችን የስራ እድል ትስስርን የሚፈጥር ኘሮጀክት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስትራቴጂክ ፕላን ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በኮሌጁ ለኢንዱስትሪው ተፈላጊ የሆኑ የስራ ትስስሮችን መፍጠር የሚያስችል የስልጠና መርሀ-ግብር ስትራቴጂክ ፕላን ቀርቦ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ይህ ፕሮጀክት ለአምስት አመት እንደሚቆይም ተገልጿል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአለም ባንክ ባገኘው 6.7 ሚልየን ዶላር EASE (Education and Skills for Employability) ኢዱኬሽን ኤንድ ስኪል ፎር ኢምፕሎይቢሊቲ ፕሮጀክትን የማስጀመር መርሀ-ግብር ተካሒዷል። ፕሮጀክቱ በዋናነት የስራ እድል ትስስርን ይፈጥራል የተባለ ሲሆን ይህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የገጠርና የከተማ ወረዳዎችን ጨምሮ በርካቶችን የሞያ ጥበብን ወይም ስኪልን በማሰልጠን ከገበያው ጋር እንደሚያስተሳስርም ተገልፇል። በዚህ EASE ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ላይ ተገኝተው መርሀ-ግብሩን ያስጀመሩት በድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ባስተላለፉት መልእክት ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ጠንካራ አመራር ሰጪነት ወሳኝ እንደሆነ ገልፀው ለታለመለት አላማም መሰረት አድርጎ መከናወን እንዳለበት አሳስበዋል። ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማኒፋክቸሪንግ ፣ በኤሌክትሮ ቴክኖሎጂና በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ የስልጠና መስኮች ከመማርና ማስተማር ጋር ያሉ የትምህርት ጥራትን አካቶ ተወዳዳሪነትን የሚጨምሩ የኢንዱስትሪ ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ የስልጠና መስኮችን ለመቅረፅ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው ሲሉ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ ተናግረዋል። ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ በፊት በመደበኛ ከሚሰጠው ስልጠና በተጨማሪ ይህ የEASE ፕሮጀክት በዋናነት አካታች የሆነ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ይሰጣል ሲሉ የፕሮጀክቱ ዋና ኮርድኔተር አቶ ፋሲል ማዘንጊያ ገልጸዋል። ይህ EASE (Education and Skills for Employability) ፕሮጀክት ኮሌጁ ከአምስት አመት በኋላ አሁን ካለበት ስልጠና የመስጠት አቅም በቴክኖሎጂ የተደገፈ መሰረተ ልማት የተሟላለት ኮሌጅ እንዲሆን ያስችለዋልም ተብሏል። በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዳር 26/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

‹‹ከወጣቶች ጋር በመተባበር ሙስናን መከላከል፣ የነገን ስብዕና ለመቅረጽ ›› በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ በኮሌጃችን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፀረ- ሙስና ቀን በፓናል ውይይት እንዲሁም በስልጠና በዛሬው እለት ተከበረ፡፡ ሙስና የጋራ ጠላት ነው በህብረት ሆነን ያማንታገለው ከሆነ ወደምናስበው የብልጽግና ጉዞ እንዳንሄድ አስሮ ወደኋላ የሚያስቀረን ነው ስልዚህ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን ሁሉ ሙስናን የሚጠየፍ ማህበረሰብ በመፍጠር ሙስናን በጋራ ሆነን ልንታገለው ይገባል ፡፡ በኮሌጅም ደረጃ ሙስናን ለመከላከልና ለመታታገል አዳዲስ የአሰራር ስርአቶችን በማዘጋጀት የሙስና፣የብልሹ አሰራሮች እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በጋራ ሆነን በመስራት ይህንን መጥፎ ተግባር ልንከላከለው ብሎም ልናጠፋው ይገባናል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳላሃዲን አብዱልሃሚድ ናቸው፡፡ የኮሌጁ ዲን አያይዘውም ኮሌጃችን እንደ ስሙ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል እንዲሆን እንዲሁም ለሌሎች አቻ ኮሌጆች አርአያ መሆን የሚችል ተቋም ለመገንባት ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በጋራ በመስራት ሙስናን መከላከል ይገባናል ያሉ ብለዋል፡፡ ሃገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ብዙ ወጣቶች የሚገኝባት ሃገር እንደመሆኗ መጠን ወጣቶች ሙስናን የሚጠየፉ ለማድረግ በስልጠና ስርአታችን ውስጥ አካተን ማስተማር ይገባናል ብለዋል፡፡ በማስቀጠል በፓናል ውይቱና የስልጠና መድረኩ ላይ በአቶ በለጠ እሸቱ የኮሌጁ የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና መከታተያ ባለሙያ ሙስና በአለም አቀፍ እንዲሁም በሀገራችን ደረጃ አሁናዊ ሁኔታ የሚዳስ ሰነድ ለከኮሌጁ ማህበረሰቦች በማቅረብ የተለያዩ ውይይቶች እንዲሁም ግልጽነት የሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ከተደረገ በኋላ ተሳታፊው በጋራ ሙስና የጋራ ጠላት እንደ ሆነ በመረዳት ሁሉም ሰው ከወጣቶች ጋር በጋራ ለመታገል ቃል በመግባት መድረኩ ፍጻሜ አግኝቷል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

A Rising Economic Powerhouse in Africa

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ እና በአስተዳደሩ ካይዘን ኢንስቲትዩት መካከል የካይዘን ትግበራ ድጋፍ፣ ክትትል እና ግምገማ ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡ በዋናነት መድረኩ ኤጀንሲው ከኢንስቲትዩቱ ጋር የተናበበ የጋራ ዕቅድ ባለመኖሩ የተመላከቱ አለመናበቦችን ለማጥራት ይህም ኢንዱስትሪዎች ላይ የካይዘን ትግበራ ሲከናወን ኢንዱስትሪዎች ፍላጎታቸውን በሚጨምር  እና በአሰልጣኞች ላይም የጊዜ ብክነትን በማይፈጥር መልኩ ውጤታማ ስራ ለመስራት መግባባት ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡ በዚህም መድረክ ላይ በአጠቃላይ በኮሌጆች እየተሰጠ ያለውን የካይዘን ትግበራ ድጋፍን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ እና እየሰፋ የመጣውን የካይዘን ጽንሰ ሃሳብና ትግበራን ለማዘመን የሚያስችሉ ስልጠናዎች ሊሰጡ እንደሚገባ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የኤጀንሲው ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ በተያያዘ ለአሰልጣኞች በካይዘን ደረጃዎች በመመዘን ሰርተፍኬት የመስጠቱ ሁኔታ እየታደሰ የሚሄድ እና ቀጣይነት ያለው ሊሆን እንደሚገባው፤ በተለይ ኮሌጆች በካይዘን ትግበራ የተሻለ ልምድ ቢኖራቸውም ከኢንስቲትዩቱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት የተበቀ በማድረግ በካይዘን ትግበራ የተገኙ ውጤቶችን እንደ አስተዳደር አንጸባራቂ ሆነው እንዲወጡ ማድረግ ላይ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ተነስቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በምስራቅ ዕዝ ደረጃ-3 ሪፈራልና ማስተባበሪያ ሆስፒታል ውስጥ የተቋቋመው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ላይ የ2017 ዓ.ም የሰልጣኞች ቅበላ ዶክመንት ለማጣራትና የሰልጣኝ መረጃ አደረጃጀት የሚመለከት የድጋፍና ክትትል ስራ ተከናወነ። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የማሰልጠኛ ተቋማት ህጋዊ የማሰልጠን ፈቃድ የሚሰጥና በሰጠው ፈቃድ መሠረት በየጊዜው ድጋፍና ክትትል በማድረግ የስልጠናው ጥራት መጠበቁን ያረጋግጣል። በዚህም በምስራቅ ዕዝ ደረጃ-3 ሪፈራልና ማስተባበሪያ ሆስፒታል ውስጥ የተቋቋመው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም በነርሲንግ ሙያ ዘርፍ በደረጃ አራት ወንድ 555 ሴት 81 በአጠቃላይ 636 የተቀበላቸው ሰልጣኞችን የትምህርት ማስረጃ ህጋዊነትና ትክክለኛነት ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ለተቋሙ የስልጠናውን ጥራት እንዲያስጠብቅ ሙያዊ ድጋፍ አግኝቷል። በተያያዘ በአስተዳደሩ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለሚያከናውኗቸው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተግባራት ቢሮው በቅርበት በመከታተልና በትብብር መንፈስ የመረጃ አያያዝ ስርዓታቸውን እንዲያሳድጉና ጥራት ያለው ስልጠና መስጠት እንዲችሉ የሚደረገው እገዛና ድጋፍ በሌሎችም ተቋማት በተመሳሳይ የሚቀጥል እንደሚሆን አቶ ታሪኩ ለገሰ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ በዚህ በጀት አመት ባለፉት ወራት በዘርፉ አዲሱ ዕሳቤ ላይ እስከታችኛው የቢሮው መዋቅር የተፈጠረው ግንዛቤ ተናቦ ለመስራት ሁነኛ መሳሪያ ሆኖ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገለጸ። በሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ ባለሙያዎች ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ለአምስት ቀናት ያካሄደው የድጋፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ሲጠናቀቅ በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል የማዘመን እና ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራዎችን ተመልክቷል፡፡ የባለሞያዎች ቡድኑ ባካሄዳቸው ጉብኝት ላይ ከአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውና ከቢሮው አመራሮች ጋር የተወያዩ ሲሆን በአስተዳደሩ ከዚህ ቀደም በተደረገው የድጋፋዊ ሱፐርቪዥን የተሰጡ ግብረመልሶችን እንደ ግብዓት በመውሰድ እየተከናወኑ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ስራዎች አበረታች ሆነው ተመልክተዋቸዋል። የአቅም ግንባታ ስራዎች፣ የክህሎት ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ሰላማዊ የኢንዱስትሪ የስራ እንቅስቃሴዎች ለመፍጠር የተከናወኑ ስራዎች አበረታች ናቸው በዚህም የበለጠ በማጠናከር የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ ጥረት መደረግ እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በተካሄደው ድጋፋዊ የግምገማ ሂደት የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በተቀናጀ መንገድ በመተግበር አመታዊ ዕቅድን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ጥረት እንደሚያደርጉ ለዚህም በተገኙ ውጤቶች በመርካት የማይቀመጥ መዋቅር መፈጠሩ ከፍ ያለ ውጤት ለማምጣት አቅም ይሆነናል ብለዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 25/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የግልና የመንግስት ኮሌጆች የተዘጋጀ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤ የስልጠናው ዋና አላማ በቢሮው በተለይም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍን የሚመሩና የሚሰሩ አመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጊዜው የሚጠይቀውን እና የሚፈልገውን ክህሎት ተላብሰው ተልዕኮ መፈጸም እንዲችሉ ታስቦ በተለያዩ ርዕሶች የተሰጠ መሆኑን የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል፡፡ በዚህም ከኮሌጆቹ የተወጣጡ የትምህርትና ስልጠና ክፍል ተጠሪዎች፣ የስልጠና አስተባባሪዎችና የሬጅስትራር ክፍልን የሚመሩ በስልጠናው ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን የሰልጣኞች ቅበላና ምደባ ፖሊሲ፣ የተቋም ውስጥ ምዘና እንዲሁም TVT Harmonized የዘርፉ ስርዓተ ሰነዶች በቢሮው ባለሙያዎች ቀርበው ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲው ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በስልጠናው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት አመራሩ እና ከፍተኛ ባለሙያው ከዘመኑ ጋር ለመራመድ በወሰዱት ስልጠና እራስን የማብቃት ስራ በዚህ ስልጠና የሚጠናቀቅ እንዳልሆነና ክህሎታቸውን ለማዳበር ቢሮው መሰል ስልጠናዎችን በየጊዜው እንደሚያዘጋጅም ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 25/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘውን አጠቃላይ የሥራና ክህሎት ስራዎች አፈጻጸም የመጨረሻውን የመስክ ምልከታ ውሎ አካሄደ። በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ቴሬሳ የተመራው ቡድኑ አስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ በበጀት አመቱ የተሰሩ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ ባለፉት ተከታታይ ቀናት ያደረገ ሲሆን በዛሬው ዕለት በስራ ዕድል ፈጠራ አንድ ማዕከላትን በማስተባበር የተፈጠሩ የስራ ዕድሎችን፣ በኢንተርፕራይዝ ልማት በዶሮ እና በከብት እርባታ የተገኙ ውጤት የተገኘባቸው ልማቶች እንዲሁም በክህሎት ልማት በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በስልጠና ከስልጠና ጎን ለጎን የተሰሩ ስራዎች ምልከታ ተደርጎባቸዋል። የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በአስተዳደሩ በነበረው ቆይታ በሰፊው የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ ሰው ተኮር የሆኑ የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ስራዎችን የተመለከቱ ሲሆን በነገው ዕለትም የድጋፍና ክትትሉ የመስክ ምልከታ ግብረመልስ ለቢሮው የሚቀርብና  የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

''እያገረሸ የመጣዉን የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ ስርጭት ለመግታት ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል። ''  * የሥራና ክህሎት ቢሮ: ህዳር 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች የኤች ኤድስ ቀንን ''ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የኤች አይ ቪ አገልግሎት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል አከበሩ። በአሉ በሽታዉን መከላከልና መቆጣጠር እንዲቻል በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መነቃቃትና ግንዛቤ መፍጠር አላማ አድርጎ ይከበራል። እያገረሸ የመጣዉን የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ ስርጭት ለመግታት ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በበዓሉ ላይ ተናግረዋል፤ መዘናጋቱን ተከትሎ በሀገራችን ብሎም በአስተዳደራችን እየተስፋፋ የመጣዉን የበሽታዉን ስርጭት ለመቀነስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። በበዓሉ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት ተደርጓል በዚህም የሁሉንም ማህበረሰብ ሰብዓዊ መብት ባከበረ መልኩ የኤች አይ ቪ ኤድስ የጤና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስራ ሊሰራ እንደሚገባ ተጠቁሟል፤ በሽታዉ በርካታ አምራች ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለና ስርጭቱ እየጨመረ የመጣ በሽታ በመሆኑ ሁሉም ማህበረሰብ አስከፊነቱን በመረዳት ስርጭቱን ለመግታት ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በዓሉ በዓለም ለ37ኛ በሀገራችን ለ36 ኛ ጊዜ ''ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የኤች አይ ቪ አገልግሎት ለሁሉም'' በሚል መሪ ሀሳብ ተከብሯል።

photo content
+9

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አመቻችነት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስራዎች በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል በአሰልጣኝ መምህራን የውስጥ አቅም በኮሌጁ የማሽን ሾፕ የሚገኙ በተለያየ ምክንያት የተበላሹ ሶስት ማሽኖች (Conventional Lathe Machine, Conventional Milling Machine and CNC Lathe Machine) ተጠግነው ወደ ስራ እንዲገቡ ተደረገ፤ የማሰልጠኛ ማሽኖቹ ጥገና በአሰልጣኝ መምህራኑ መካከል የልምድና የእውቀት ሽግግር አንዳቸው ለሌላቸው በማድረግ አሰልጣኝ መምህራኑ የክህሎት አቅማቸውን በአንድ በኩል ሲያሳድጉ ከዚሁ ጎን ለጎን ማሽኖቹን ጠግነው ለትምህርትና ስልጠናው ዝግጁ በማድረግ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አድርገዋል፤ በማጠቃለያውም የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እንደተናገሩት ለ15 ቀናት በተከናወነው የጥገና ስራ በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ዘንድ ያለውን የክህሎት ክፍተት መሙላት ከመቻሉ ባሻገር የነበረውን የማሽን ብልሽት ችግር ለመፍታት ያስወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ማስቀረት መቻሉን ገልጸው በኮሌጁ የውስጥ አቅም የተከናወነ መሆኑ ደግሞ የኮሌጁን አቅም የሚያጠናክር እንደሚሆንና በተለይም በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በሚገኙ ዲፓርትመንቶች የጥገና ቡድን መቋቋሙ ውጤት የሚያስገኝ መሆኑንና በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በተመሳሳይ  የሚቀጥል መሆኑን  ገልፀዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ