es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 064
Suscriptores
Sin datos24 horas
-77 días
+230 días
Archivo de publicaciones
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት አባላት በዛሬው  እለት “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ ዓመታት የትኩረት መስኮች ላይ የሚመክር የውይይት መድረክ  አካሄደዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የህብረት አባላት በሀገራዊ ቀጣይ የእድገት ጉዞ ላይ የጠራ ግንዛቤን እንዲጨብጡና ለሀገራዊ ለውጡ በሁሉም መስክ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አቅም የሚፈጥርላቸው ይሆናል። ሲካሄድ በቆየው ውይይትም የድሬዳዋን የብልፅግና ተምሳሌትነት እንዲሁም የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በቀጣይም የፓርቲውን አሻጋሪ ዕሳቤዎች በቁርጠኝነት ለመፈፀምና ለማስፈፀም ተግባቦት የሚፈጥር ሲሆን የውይይት መድረኩ በነገው ዕለት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት አባላት በዛሬው  እለት “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ ዓመታት የትኩረት መስኮች ላይ የሚመክር የውይይት መድረክ  አካሄደዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የህብረት አባላት በሀገራዊ ቀጣይ የእድገት ጉዞ ላይ የጠራ ግንዛቤን እንዲጨብጡና ለሀገራዊ ለውጡ በሁሉም መስክ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አቅም የሚፈጥርላቸው ይሆናል። ሲካሄድ በቆየው ውይይትም የድሬዳዋን የብልፅግና ተምሳሌትነት እንዲሁም የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በቀጣይም የፓርቲውን አሻጋሪ ዕሳቤዎች በቁርጠኝነት ለመፈፀምና ለማስፈፀም ተግባቦት የሚፈጥር ሲሆን የውይይት መድረኩ በነገው ዕለት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና| የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በረጅም አመታት በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ያካበተውን ጠካራ ልምድ ለኮምቦልቻ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በዛሬው እለት አካፈ
+3
#ዜና| የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በረጅም አመታት በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ያካበተውን ጠካራ ልምድ ለኮምቦልቻ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በዛሬው እለት አካፈለ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስራ በአቶ መሀመድአወል ጠሃ እንዲሁም የፕሮጀክቱን አፈጸጸም እና የግንባታ ሂደቱን እስካሁን የደረሰበት ደረጃ በፕጀክቱ መሃንዲስ ሃምዲ ኢብራሂም እንዲሁም በEASTRIP ፕሮጀክት አባላት ገለጻ ተደርጓል፡፡ የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት የልኡክ ቡድኑ አባላት እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አራያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለመላው ሃገራችን የሚበቃ ነው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ነሀሴ 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ዜጎች ከአንድ በላይ የሞያ ባለቤት በመሆን በተለያዩ የሞያ አማራጮች እራሳቸውን ማጎልበት እንዳለባቸው ተገለፀ። የአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቢሮ ወጣቶችንና 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በተለያዩ የሞያ ዘርፎች በአጫጭር ስልጠናዎች ተጠቃሚ የሚያደርግ የሞያ ስልጠና በሁለቱ የቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች እየተሰጠ ይገኛል። በአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቢሮ በስሩ በሚገኙት የኢትዮጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በድሬዳዋ ፓሊቴክኒክ ኮሌ በክረምቱ ወራት የቴክኒክ እና ሞያ ንቅናቄ ማስጀመሪያ ስልጠና መርሀግብርን ኮሌጆቹ ከሚሰጧቸው መደበኛ ስልጠናዎች በተጨማሪ በአጫጭር ስልጠናዎች የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የተፈተኑና ሌሎች ወጣቶችን በማሳተፍ በተለያዩ ዘርፎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። በስልጠናው ሲሰለጥኑ ያገኘናቸው ወጣት ኤፍራታ መስፍንና ወጣት ይታገሱ ዮሴፍ በዚህ እድል ተጠቃሚ ከሆኑ የድሬዳዋ ወጣቶች መካከል ናቸዉ ። በቤት እና በሰፈር ውስጥ ጊዜያቸውን በከንቱ ከማባከን በአጫጭር ስልጠናዎች ይህ በመመቻቸቱ ከትምህርታቸው ባሻገር የሞያ ባለቤት ለመሆን ችለዋል ። የድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምክትል ዲን አቶ አብዱልፈታህ እና የኢት-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ጥናትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዳይሬክተር እና የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ እንደገለፁት የክረምት ስልጠና መርሃ ግብር ተማሪዎችና ወጣቶችን የሞያ ባለቤት ከማድረግ በተጨማሪ በራስ መተማመን መንፈሳቸውን በማጎልበት እራሳቸውን ለቀጣይ የህይወታቸው እንዲለውጡ የሚያግዛቸው እንደሆነ ይናገራሉ ። ዲኖቹ አያይዘውም በዚህ በተመቻቸላቸው እድል ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልክታቸውንም ያስተላልፋሉ ። በድሬዳዋ አስተዳደር በስራ ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሞያ ልማት አሰልጣኝ ባለሞያ አቶ ሀይለአብ ወርቁ እንደገለፁት እንደ የመንግስት አቅጣጫ ዜጎች ከአንድ በላይ የሞያ ባለቤት መሆን እንዳለባቸው በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ዜጎች ባሉት ኮሌጆች ሞያ በመቅሰሠም ተጠቃሚ እንዲሆኑ የታሰበ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ ሀይለአብ አክለውም በቀጣይ የቴክኒክና ሞያ/TVET ሣምንት ንቅናቄ በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ዜጎች የቴክኒክና ሞያ ዙሪያ ያላቸውን አመለካከት በመቀየር ግንዛቤ በሚያገኙበት መንገድ እንደሚከበር ገልጸዋል ። በመርሀግብሩ የተሳተፉ ከ400 በላይ ሰልጣኞች በኮሌጁ ከ12 በላይ የተለያዩ የስልጠና መስኮች እየሰለጠኑ ይገኛሉ ። ©️ DireTvአማርኛ

#ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት መደበኛ ስራና የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም ለኮሌጁ የቦርድ አባላት በዛሬው እለት ቀረበ፡፡ የኮሌጁን መደበኛ ስራ ሪፖርት ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን በአቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ኮሌጁ ከዝግጅ ት ምእራፍ አንስቶ እስከ በጀት አመቱ ማጠቃለያ ድረስ የተሰሩ ስራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን ለቦርዱ አባላት የገለጹ ሲሆን አያይዘውም የቴክኒክና ሙያ አዲሱን እሳቤ ከተቋሙ አሁናዊ ሁኔታ ጋር ያለበትን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡በ2018 በጀት አመት በኮሌጁ ሊሰሩ የታሰቡና ሊተገበሩ የሚገቡ እቅዶች ለቦርዱ አባላት አቅርበዋል፡፡ በመቀጠልም የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም በፕሮጀክቱ M&E specialist በሆኑት በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቧል፡፡ ከሪፖርቶቹ በኋላም በቀረበው የእቅድ አፈጻጸም ላይ የቦርድ አባላቶች የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ም/ሰብሳቢና የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር በኮሌጁ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ የታዩ አመርቂ ውጤቶች እጅግ የሚያስደስቱና የሚያበረታቱ ናቸው ያሉ ሲሆን በቀጣይ አመት ሊሰሩ የታሰቡ ስራዎች ላይም የስራ መመሪያ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ በስተመጨረሻም የቦርዱ አባላት በኮሌጁ የተሰሩ ስራዎችን ተዘዋውርው የጎበኙ ሲሆን የአረንጓዴ አሻራም በኮሌጁ አኑረዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ነሀሴ 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege

አድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ለኮሌጁ የፑል አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት በGreen TVET እሳቤ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ:: የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት አድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) በኮሌጁ ትግበራውን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በGreen Energy ዙሪያ በርካታ ስራዎችን በኮሌጁ እንዲሁም በአስተዳደሩ ማከናወኑን አስታውሰው ፕሮጀክቱ ያስቀመጠውን ግብ ከማሳካት አንፃር ብዙ ተግዳሮቶችን አልፎ አሁን ላይ ከሌሎች የፕሮጀክት ሳይቶች አንፃር የተሻለ አፈፃፀም እያስመዘገብ እንደሚገኝም ገልፀዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህን በ Green TVET እሳቤ ላይ ያተኮረ የግብዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ያስፈለገው በቀጣይ ኮሌጁ በትኩረት ከሚሰራባቸው ተግባራት ውስጥ የGreen TVET አንዱ በመሆኑ ከወዲሁ በዘርፉ እሳቤ ላይ ሰፋ ያለ ግንዛቤ እንዲኖር ለማስቻል ያለመ እንደሆነው ገልፀዋል:: በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በቅድሚያ የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ዋና አላማ ግብን አስመልክቶ በፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎ ገለፃ የተደረገ ሲሆን ዋና አስተባባሪው አያይዘውም ፕሮጀክቱ ከጅምሩ እንስቶ በኮሌጁ በቆየባቸው አመታት ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ያከናቸውን ዋና ዋና ቁልፍ ተግባራትና ያስመዘገባቸውን አመርቂ ውጤቶች በዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል:: የGreen TVET እሳቤ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ሰነድ በኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን Green Energy ከTVET ዘርፍ ጋር ያለውን ቁርኝትና ከቅርብ አመታት ወዲህም በዘርፉ ተቀዳሚ ትኩረት እያገኘ እንደሆነ በሚያመላክት ሁኔታ የግንዛቤ ስልጠናውን መስጠት ችለዋል:: የመድረኩ ተሳታፊዎች በተሰጣቸው የግንዛቤ ስልጠና መነሻነት ሀሳቦችን በማንሳት በግሩፕ የተወያዩ ሲሆን Green Energy ከትምህርትና ስልጠና አኳያ፣ ከቴክኖሎጂ አኳያ እንዲሁም አጠቃላይ ከኮሌጁ እንቅስቃሴ አኳያ በምን መልኩ አቀናጅቶ ለመተግበር ያስችላል የሚሉ ጉዳዮችን በዝርዝር አስቀምጠዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ነሃሴ 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በIOM የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም በEDI የስልጠና ሰጭነትና አስተባባሪነት ሲካሄድ የቆየው የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞችና ምሩቃን የንግድ ሃሳብ pitching ስልጠና እና ውድድር ተጠናቀቀ። በአስተዳደ
+9
በIOM የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም በEDI የስልጠና ሰጭነትና አስተባባሪነት ሲካሄድ የቆየው የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞችና ምሩቃን የንግድ ሃሳብ pitching ስልጠና እና ውድድር ተጠናቀቀ። በአስተዳደሩ ከሚገኙ ሁለቱ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የተመረጡና የንግድ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች ከነሀሴ 14/2017 ዓ.ም እስከ ነሀሴ 18/2017 ዓ.ም ለአምስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ስልጠና እና የንግድ ሃሳብ ውድድር ፍፆሜውን አግኝቷል:: በእለቱ በነበረው የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የIOM ተወካይ አቶ ዘሪሁን እንደገለፁት ይህን መሰል ፕሮግራሞች ወጣቶች የተሻለ የንግድ ሃሳብ እንዲያጎለብቱ እና የንግድ ሃሳባቸውን እንዴት መግለፅ እንዳለባቸው የሚረዱበት እንዲሁም የቢዝነስ አጋር የሚያገኙበትን አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ያሉ ሲሆን አክለው በውድድሩ ጥሩ ውጤት ያስመዘገቡትን ወጣቶች በሀገር አቀፍ ውድድር ላይ እንዲሳተፉ የሚደረግ ይሆናልም ብለዋል:: በተጨማሪም በውድድሩ አሸናፊ የሆኑት ወጣቶች የንግድ ሃሳባቸውን ወደ መሬት የሚያወርዱበትን እና ንግዳቸውን የሚያስፋፉበት መንገድ እንደሚመቻችላቸውም በመድረኩ ማወቅ ተችሏል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ነሃሴ 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮጵያ ማንሠራራት ጅማሮ፤ የደም ጠብታ የላብ ጠብታ የዕንባ ጠብታ የውኃ ጠብታ ድምር ውጤት መሆኑን፣ ይህ ግድብ ህያው ምልክት ሆኖ ለትውልድ ሲመሰክር ይኖራል።
+4
የኢትዮጵያ ማንሠራራት ጅማሮ፤ የደም ጠብታ የላብ ጠብታ የዕንባ ጠብታ የውኃ ጠብታ ድምር ውጤት መሆኑን፣ ይህ ግድብ ህያው ምልክት ሆኖ ለትውልድ ሲመሰክር ይኖራል።

ሙያዊ ክፍተትን መሰረት ያደረገው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሦስተኛ ቀን ውሎ በተንቀሳቃሽ ምስል

#|እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!! በኮሌጃችን ውስጥ ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክት ፕሮጀክቱን ከሚያጸድቁ አካላቶች ከGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NE
+4
#|እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!! በኮሌጃችን ውስጥ ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክት ፕሮጀክቱን ከሚያጸድቁ አካላቶች ከGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD No Objection በማግኘታችን የተሰማኝን ደስታ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ የፕሮጀክቱ በኮሌጃችን ተግባራዊ መሆኑ የአካባቢውን ብሎም የቀጠናውን ወጣቶች በICT የዳበረና እውቀት ያለው ትውልድ ለመገንባት ያስችለናል፡፡ ከዚህም አልፎ ከተማችንን ስማርት እንድትሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ይህ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን ቀን ከሌት ለለፋችሁ ለአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣የኮሌጁ ማኔጅምንት አባላት፣የEASTRIP ፕሮጀክት አባላት እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰብና የICT ትምህርት ክፍል አባላት ምስጋናዬን ለማቀቅረብ እወዳለሁ፡፡ አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ የኮሌጁ ዲን ነሀሴ 16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በ2018 በጀት ዓመት በቢሯችን የሚከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ:- *** በቢሮው የተያዙ ፕሮጀክቶች *** የከተማና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ *** ለዜጎች አጫጭርና መደበኛ ስልጠና እና *** የአሰ
+3
በ2018 በጀት ዓመት በቢሯችን የሚከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ:- *** በቢሮው የተያዙ ፕሮጀክቶች *** የከተማና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ *** ለዜጎች አጫጭርና መደበኛ ስልጠና እና *** የአሰሪና ሰራተኛ ተግባራትን በቁርጠኝነት ለመፈፀም በዛሬው እለት ከአስተዳደሩ ም/ቤት ጋር ተፈራርመናል። አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ