es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 063
Suscriptores
Sin datos24 horas
-77 días
+230 días
Archivo de publicaciones
#ዜና |የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና በገበያ ተፈላጊ በሆነ ሞያና ክህሎት የበቁ ዜጎችን በማፍራት ብዙዎች ተጠቃሚ እነሆኑ ነው ። #DireTvአማርኛ | መስከረም 27፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ የሞያና ክህሎት ስልጠና ያለውን ጠቀሜታ በመገንዘብ በኩልም የህብረተሰቡ ንቃት መዳበሩ ይነገራል። በዚህ ዙሪያ የድሬዳዋ መገናኛ ብዙኃን ድርጅት ከቴክኒክና ሞያ ሰልጥነው ስራ ላይ ከተሰማሩ ነዋሪዎች ጋር ቆይታ አድርጓል። ነጃት ተገኔ እንደሚከተለው አዘጋጅታዋለች

Repost from E-LMIS - ብቁ
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች በሙሉ! ኦቪድ ሆልዲንግ (Ovid Holding) በሥራና ክህሎት ሚኒስትር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት E-LMIS በኩል በExecutive Assi
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች በሙሉ! ኦቪድ ሆልዲንግ (Ovid Holding) በሥራና ክህሎት ሚኒስትር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት E-LMIS በኩል በExecutive Assistant የሥራ መደብ ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል ። ስለሆነም በዚህ የሥራ እድል ለመመዝገብና ለመወዳደር በቅድሚያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ ወረዳ/ቀበሌ የአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር/ labor ID/ ይዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/ovid/ ማስፈንጠሪያ በመግባት ትክክለኛ የትምህርት፣ የስራ እና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎቻችሁን በማሰገባት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

“የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ለወጣቶች ሥራ ፈጠራ” የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተለያዩ ሙያዎች የአካባቢውን ወጣቶች ሕይወትን እንዴት እየለወጠ እንዳለ ይወቁ። 🌍💻 በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተተገበረው ይህ ስልጠና በፍላጎት ላይ የተመሰረተ የክህሎት ስልጠና እና የኢንተርፕረነርሺፕ ኮርሶችን በመስጠት ወጣቶችን በፋሽን ዲዛይን ዘርፍ የስራ ተጠቃሚነትን እያሳደገ ይገኛል። በኮሌጁ በተሰጠዉ ክህሎት እና የስልጠና እድሎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ስኬታማ ሆና ያገኘችውን የቴ/ሙ/ት/ምና ስልጠና እየሰለጠነች ያለቸውን ወጣት ውብርስት ጸጋዬን አድምጡ። ለወቅታዊ ትኩስ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃ You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC) Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/Dire Dawa Polytechnic College TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege

በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የግልና የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ጋር በዘርፉ የሰልጣኞች ቅበላ እና ምደባ ፖሊሲ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። በዚህም መድረክ ላይ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ እና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የ2018 የስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኞች ቅበላን አስመልክቶ የአፈጻጸም አቅጣጫዎች ላይ ገለጻ አድርገዋል ። በሰልጣኞች ቅበላ እና ምደባ ዙሪያ ለሚነሱ ማናቸውም የአፈጻጸም ግድፈት ተጠያቂዎቹ ቅበላውን የሚያከናውኑ ተቋማት መሆናቸውን በማስገንዘብ ህግና ስርዓትን ተከትለው ቅበላውን በመስፈርቱ መሠረት ማከናወን እንደሚገባቸው አፅንዖት ሰጥተው አሳስበዋል። በዚህም መሠረት የዘመኑ ቅበላ ወጥ በሆነ መረዳትና አፈጻጸም በሁሉም የቴክኒክና ሙያ ተቀቋማት እንዲተገበር  መመሪያ የሰጡ ሲሆን በመድረኩ ከተሳተፉ የግል እና የመንግስት ኮሌጅ አመራሮች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የሚመለከታቸው ከፍተኛ ባለሙያዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የመሰረታዊ የስራ ሁኔታ እና የሙያ ደህንነትና ጤንነት የስራ ሁኔታ ቁጥጥር በማድረግ በአሰሪና ሰራተኛው መሀከል መግባባት በመፍጠር የስራ ቦታዎችና የኢንደስትሪ ሰላም የማስፈን ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ተገለጸ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በተሰጠው ተግባርና ሃላፊነት መሰረት የግል ድርጅቶችን መሰረታዊ የስራ ሁኔታዎች በመቆጣጠር ድጋፍና ግብረመልስ የመስጠት ተግባራትን በማከናወን የስራ ቦታዎችና የኢንደስትሪ ሰላምን ለማስፈን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ በየጊዜው በሚደረጉ መሰል ምልከታዎች የተሻሻሉ ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው ከሰራተኛው የስራ ሁኔታ እና ሙያዊ ደህንነትና ጤንነት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ክፍተቶችን እና ጉድለቶቸን በመከታተል በአካል ከተገኘው ምልከታ በመነሳት በሁለትዮሽ ንግግር መፈታት የሚገባቸውን እና የሚችሉትን ጉዳዮች የሚፈቱ ሲሆን ከአቅም በላይ የሆኑትን ደግሞ በህግ አግባብ የሚፈቱ ይሆናል፡፡ ቢሮው በተመሳሳይ ከተለያዩ ተቋማት የሚመጡለትን የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮች በሁለትዮሽ ድርድር እንዲፈታ በማድረጉ ረገድ በተለይም በአሰሪና ሰራተኞች መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በመፍታት የስራ ቦታዎችና የኢንደስትሪ ሰላምን ለማስፈን እንዲያስችለው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ  በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 23/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደተር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከጤግሮስ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር ለአስተዳደራችን ስራ ፈላጊዎች ምርጥ አማራጭ የስራ እድል ይዞ ቀርቧል፡፡ #ምን ይዞ ቀረበ? ጥሩ ጥያቄ ነው…. በተመረጡ 4
የድሬዳዋ አስተዳደተር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከጤግሮስ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር ለአስተዳደራችን ስራ ፈላጊዎች ምርጥ አማራጭ የስራ እድል ይዞ ቀርቧል፡፡ #ምን ይዞ ቀረበ? ጥሩ ጥያቄ ነው…. በተመረጡ 4 የንግድ ዘርፎች ባለ ሱቅ ሊያደርጋችሁ ነው #እንዴት? በሸቀጣ ሸቀጥ በአልበሳት በኮስሞቲክስ እና በስቴሽነሪ ለተደራጁ አምስት አምስት ወጣቶች ሙሉ የሱቅ እቃ በነጻ ያቀርባል በመጀመሪያ የተረከቡትን ሸጠው ሲጨርሱ እና ዋናውን ሲመልሱ ሌላ ዙር ሙሉ የሱቅ እቃ ያቀርባል አሁን ሲጨርሱ ዋናውን መልሰው ሌላ ዙር ይመጣሎታል #ይህንን አስገራሚ እድል ተጠቃሚ ለመሆን ምን ማድረግ አለብን? 5 ሆኖ መደራጀት ለስልጠና እያንዳንዱ የማህበር አባል 4500 ብር መክፈል (የአሰልጣኞች ወጪ እና የኔነት እንዲሰማ) በመጨረሻም ንግድ ፍቃድ አውጥቶ ሱቁን ብቻ ማዘጋጀት፡፡ #ከዛስ? ከዛማ ምን ጥያቄ አለው የሱቅ ባለቤት በመሆን አስተማማኝ የስራ እድል ይፈጠርላችኋል በአምስት አመት ውስጥ ትልቅ ሱፐር ማርኬት እንዲከፍቱ ድጋፍ ይደረግላችኋል፡፡ ተጨማሪ መረጃ በሁሉም ወረዳዎች (ቀበሌ) የስራ እና ክህሎት ማስተባባሪያ ጎራ እያላችሁ መረጃውን መውሰድ ትችላላችሁ #ከዛስ? ከዛማ ምን ጥያቄ አለው የሱቅ ባለቤት በመሆን አስተማማኝ የስራ እድል ይፈጠርላችኋል በአምስት አመት ውስጥ ትልቅ ሱፐር ማርኬት እንዲከፍቱ ድጋፍ ይደረግላችኋል፡፡ ተጨማሪ መረጃ በሁሉም ወረዳዎች (ቀበሌ) የስራ እና ክህሎት ማስተባባሪያ ጎራ እያላችሁ መረጃውን መውሰድ ትችላላችሁ:: ዕድሉን ለሚጠቀሙ ሁሉ Share አድርጉላቸው።

🛑 ድንበርና ወሰን የማይገድበው ሰው መሆን ይቻላል! ✨ 🤔 እንዴት? የዓለም ቋንቋ የሆነውን ክህሎት ባለቤት ሲሆኑ፤ 📚 ወቅቱ የሚፈልገውን እውቀትና ክህሎት ሲታጠቁ ድንበርም ወሰንም እርስዎን አያ
🛑 ድንበርና ወሰን የማይገድበው ሰው መሆን ይቻላል! ✨ 🤔 እንዴት? የዓለም ቋንቋ የሆነውን ክህሎት ባለቤት ሲሆኑ፤ 📚 ወቅቱ የሚፈልገውን እውቀትና ክህሎት ሲታጠቁ ድንበርም ወሰንም እርስዎን አያገድብም፡፡ ይልቁንም ዓለም እርስዎን ይፈልጋል! የክህሎት ባለቤት በመሆን፦ ✅ አለም አቀፋዊ ተፈላጊነት ይፍጠሩ! ✅ ድንበር የለሽ የስራ እድሎችን ያግኙ! 🏫 አቅራቢያዎ በሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ተቋም ዛሬውኑ የክህሎት ስልጠና ይጀምሩ! 🚀 ክህሎት - የዓለም ቋንቋ! 🌐 መስከረም 21/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት በስሩ ካሉ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ጋር ውይይት ተደረገ። በዚህም ውይይት ላይ የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያዎችና የአንድ ማዕከል አስተባባሪዎች የተገኙ ሲሆን አጠቃላይ ስለሚሰጠው አገልግሎት በተለይም የማደግ አቅም ላላቸውና ድጋፍ ለሚፈልጉ ኢንተርፕራይዞች እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ተግባራት እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ተወያይተዋል። የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም አንድ ማዕከላቱ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ አሰጣጥና መረጃ አያያዝ እንዲሁም ከፍተኛ የማደግ አቅም ያላቸውን መለየት ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግና ከዚህ ጋር በተያያዘ መረጃዎች በጠራ መልኩ ተይዘው በየአካባቢው ያለውን አቅምና ጸጋ ሊጠቀሙ እንደሚገባ አሳስበዋል። የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን ሞልቶ የተሻለ ስራ መስራት የሚችሉ ባለሙያዎች መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ የኢንተርፕራይዞች LMIS ምዝገባና LUCY MARKET ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ እና በትጋት እንዲሰሩ በማሳሰብ ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 20/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ በሚል መርሃግብር የክረምት የሙያ ክህሎት ስልጠናን ሲከታተሉ የነበሩ ከ250 በላይ ወጣቶች ተመረቁ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ዜጎች ቢያንሰ የአንድ ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ለማድረግ "አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ" በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የክረምት ስልጠናን ሲከታተሉ የነበሩ 270 ወጣቶችን አስመርቋል። በኹነቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ያለፉትን 3 ወራት በ14 ዘርፎች የተሰጠውን ክህሎት መር ስልጠና የእረፍት ጊዜያቸውን በመሰዋት ወስደው የተመረቁት ወጣቶች ህብረተሰቡ ለዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት በመቀየር በኩል የተጣለባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የአንድን ሀገር እድገትን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ቢያነስ የአንድ ሙያ ባለቤት የሆነ የሰለጠነ ዜጋ ማፍራት አስፈለጊ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው በክረምት አጫጭር ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ስራን በራሳቸው በመፍጠር በኩል አይነተኛ ክህሎት መቅሰማቸውን ገልፀዋል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው ተቋሙ ባለፉት ሁለት አመታት በዘርፉ በረካታ ወጣቶችን የሙያ እና የክህሎት ባለቤት ማድረጉን ጠቅሰው ስልጠናው ወጣቶች ያላቸውን ዝንባሌ በጊዜ አውቀው ክህሎታቸውን እንዲያሳደጉ ያገዘ እንደሆነ አሰታውቀዋል። ሰልጣኞች በበኩላቸው የወሰዱት የክህሎት ስልጠና የወደፊት ህይወታቸውን የተቃና በማድረግ በተለይም የራሳቸውን ሞያ ተጠቅመው ሥራ እንዲፈጥሩ አይነተኛ ድጋፍ እንደሚደርግላቸው ገልፀዋል። ©️ DGC

photo content
+9

የምን ባለሙያ መሆን ይፈልጋሉ? 🔹 የቴክኖሎጂ 🖥️፣ የውበት 💄፣ የአውቶሞቲቭ 🚗፣ የፈርኒቸር 🪑፣ የሆቴልና ቱሪዝም 🏨፣ የኮንስትራክሽን 🏗️፣ የፋሽን ዲዛይን 👗 ወይስ ሌላ? 🔧 ፍላጎት
የምን ባለሙያ መሆን ይፈልጋሉ? 🔹 የቴክኖሎጂ 🖥️፣ የውበት 💄፣ የአውቶሞቲቭ 🚗፣ የፈርኒቸር 🪑፣ የሆቴልና ቱሪዝም 🏨፣ የኮንስትራክሽን 🏗️፣ የፋሽን ዲዛይን 👗 ወይስ ሌላ? 🔧 ፍላጎትዎን እውን ያደርጉ ዘንድ የቴክኒክና ተቋሞቻችን (TVET) ሙሉ ዝግጅታቸውን አጠናቀው እርስዎን ለመቀበል በመጠባበቅ ላይ ናቸው። ✅ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ ቴክኒክና ሙያ ተቋም በመሄድ ፍላጎቶን እውን ማድረግ የሚያስችልዎትን ስልጠና ያግኙ።✨ እጀ-ወርቅ ባለሙያ ሆነው የነገ መዳረሻዎን እራስዎ ይወስኑ! 🥇 መስከረም 19/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

🔑 ቴክኒክና ሙያ: የስኬት ቁልፍ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና የመጨረሻው ግብ በክብር የሚያስቀምጡት የምስክር ወረቀት አይደለም። ይልቁንም ነገዎን ከዕድልና እጣ ፈንታ እንዲሁም ከጥገኝነት ነፃ አውጥተው
🔑 ቴክኒክና ሙያ: የስኬት ቁልፍ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና የመጨረሻው ግብ በክብር የሚያስቀምጡት የምስክር ወረቀት አይደለም። ይልቁንም ነገዎን ከዕድልና እጣ ፈንታ እንዲሁም ከጥገኝነት ነፃ አውጥተው በራስዎ መሻት እንዲቀርጹ የሚያስችልዎትን አቅም በእጅዎ ማድረጉ ነው። ሙያ የሚያጎናፅፍዎ ሦስቱ ነፃነቶች፦ 💸 የገንዘብ ነጻነት: ሰርቶ ለማትረፍ፣ አትርፎ ለመቆጠብ እና ቆጥቦ ኢንቨስት በማድረግ ለቤተሰብ/ለህብረተሰብ/ለሀገር የተሻለ ነገር ለመፍጠር የሚያስችል ⚡ ኃይል፣ 🛠️ የሙያ ነጻነት: በራስ መንገድ መሄድ፣ የሚወዱትን የሙያ መስክ የመምረጥ እና የራስዎ አለቃ የመሆን በራስ የመተማመን አቅም፣ 🚀 የሕይወት ነጻነት: በዕድልና እጣ ፈንታ አለፍ ሲልም በሰዎች በጎ ፍቃድ ሳይሆን በራስዎ ፍላጎት የሚመራ ሕይወት የመኖር ብቃት 👉 ታዲያ ምን ይጠብቃሉ! አሁኑኑ አቅራቢያ ወደሚገኝ የቴክኒክና ሙያ በመሄድ እውነተኛ ነፃነትዎን የሚያጎናፅፍዎትን ቁልፍ መቅረፅ ይጀምሩ። መስከረም 17/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y