1 063
Suscriptores
-224 horas
-77 días
+130 días
Archivo de publicaciones
ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ለተመረጡ አሰልጣኝ መምህራን አቅም የሚገነባ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ፤
የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች በክህሎት ከሚቀስሙት ሙያ ተሰናስሎ “ETHICS AND CIVIC RESPONSIBILITY” ስልጠና ይወስዱ ዘንድ ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ለተመረጡ ስልጠናውን የሚሰጡ አሰልጣኝ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፤
በዚህም ስልጠና አእምሮን፣ ልብን እና እጅን በተግባር ማገናኘት የሚችሉ፤ ሁለንተናዊ ብቃትን የተላበሱ የአስተሳሰብ፤ የአመለካከት እና የስነ- ምግባር ባህሪ ለውጥ የሚያመጡ አሰልጣኝ መምህራንን ለማፍራት ሰው ተኮር ልል ክህሎትን መሰረት ያደረገ የዜግነት ኃላፊነትንና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ለማላበስ በሙያ ደረጃው ውስጥ የተካተቱትን ብቃት አሃዶች እና ኮርሶችን ያካተተ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፤
በመሆኑም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶበት እየሰራ ካለባቸው የክህሎት ልማት ጉዳዮች ውስጥ ወቅቱ የሚጠይቀን ሙያዊ ስነምግባር የተላበሰ ግልፅ አላማ እና ተልእኮ ያለው ትውልድ የማፍራት በመሆኑ አሰልጣኙ ሲበቃ ብቁ ሰልጣኞችን የማፍራት እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልፀዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🇪🇹✈️ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት ከምን ይጀምራል?
ይህ የእርሶዎም ጥያቄ ከሆነ ይህንን በጥንቃቄ ያስተውሉ!
👉ትክክለኛ መረጃ ያግኙ ℹ️
✅ህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፣ ህጋዊ ሥምምነት የተደረገባቸው የመዳረሻ ሀገራት፣ ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ዝርዝር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በቂ መረጃ ማግኘት፣
✅ስምሪቱ ከለመዱት የሥራ ባህል፣ ቋንቋ፣ ስርዓትና ወግን ጨምሮ በበርካታ ጉዳች እንግዳ ነገር ወደሚገጥምዎ ማህበረሰብ የሚያስገባዎ በመሆኑ በስነ-ልቦና እና በክህሎት ራስዎን ማዘጋጀት ይኖርብዎታል፣
👉በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ መመዝገብ 💻
✅የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ዋናው መግቢያ በር ነው፡፡ ስለሆነም የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም (https://lmis.gov.et) በስርዓቱ ላይ መመዝገብ ይኖርቦታል፣
✅ምዝገባውን በሁለት መልኩ ማከናወን ይችላሉ፡፡ በእጅ ስልክዎ ካሉበት ሆነውና ማስፈንጠሪያውን በመጠቀም በራስዎ ያለማንም የሰው እርዳታ መመዝገብ ችላሉ፡፡ አልያም አቅራቢያዎ በሚገኝ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ በመሄድ በባለሙያዎች እገዛ ምዝገባውን ማድረግ ይጠበቅብዎታል፣
✅ምዝገባውን እንዳጠናቀቁ በእጅ ስልክዎ በሚደርስዎ መልክት መሰረት በአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ የእጅ፣ የፊት እና የአይን አሻራ (የባዮሜትሪክስ) መረጃ መስጠት ይኖርብዎታል፡፡ በዚህ ወቅት የሚፈልጉት ሥራ የሀገር ውስጥ ወይም የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መሆኑን ለይቶ ማሳወቅ ያስፈልጋል፣
✅ይህን ምዝገባ እንዳጠናቀቁ ባለ ስምንት አሀዝ የሰራተኛ መለያ ቁጥር በእጅ ስልክዎ ይደርስዎታል፣
👉ሙያዊ ስልጠና መውሰድ🎓
✅በሚሰማሩበት የሥራ መስክ ላይ በቂ እውቀትና ክህሎትን ብቻ ሳሆን ለሥራው ቅልጥፍና ዘመኑ ያፈራቸው ቴክኖሎጂዎችን ጨምሮ ተያያዥ ጉዳችን ማወቅና አጠቃቀሙንም በበቂ ሁኔታ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም በቂ የሙያ ስልጠና ማግኘትን ይጠይቃል፣
✅በአቅራቢያ በሚገኙ የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆችና እውቅና በተሰጣቸው የግል ማሰልጠና ማዕከላት ስልጠናውን ማግኘት ይችላሉ፣
✅ስልጠናውን እንዳጠናቀቁም የሙያ ብቃት ምዘና መውሰድ ይኖርብዎታል፣
👉ህጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎች ጋር አስፈላጊውን ሂደት መጨረስ🤝
✅ስልጠናዎን በምዘና እንዳጠናቀቁ ሙሉ የስልጠናና የብቃት ምዘና መረጃዎ በተዘረጋው ስርዓት መሰረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ወዳለማው የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በቀጥታ ይገባል፣
✅በሰው ሰራሽ አስተውሎት በሚታገዘው በዚህ ስርዓት ሥራ ፈላጊውን ከሠራተኛ ፈላጊው ጋር ወደሚያገናኙ ኤጀንሲዎች አውቶሜትድ በሆነ መልኩ ድልድል ይደረጋል፣
✅ በዚህም መሰረት ኤጀንሲው ለጉዞ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ ያደርጋል
👉የቅድመ ጉዞ ስምሪት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና✈️
✅ይህ ስልጠና ስለሚሄዱበት ሀገር ባህል፣ ሕግ፣ ሃይማኖት፣ ስለ ሥራ ውልዎ እና ስለ መብትና ግዴታዎ የሚሰጥ ሥልጠና ነው። ይህንን ሥልጠና መውሰድዎ መብትዎን ብቻ ሳይሆን ግዴታውንም አውቀው በስነ-ልቦና ተዘጋጅተው እንዲሄዱ ያደርግዎታል፡፡
📣ማሳሰቢያ
✅የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለውም!
✅ህጋዊ ያልሆነ የሥራ ስምሪት ላልተገባ ወጪና እንግልት ከመዳረጉም በላይ ህይወትን ለአደጋ የሚያጋልጥ የጨለማ መንገድ ነው!
✅ስምሪቱን የተመለከተ መረጃ ከሚኒስቴር መስሪያቤቱ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅች እና በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ መዋቅር ቢሮዎች ብቻ ያግኙ
✅ ለማንኛውም አስተያየትና ጥቆማ 9138 ነፃ የሥልክ መስመር ይጠቀሙ
ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
በድሬዳዋ አስተዳደር በገጠር ቀበሌዎች የሚገኙ አርሶና አርብቶ አደሮችን በተለያዩ የገቢ አማራጮች በማሳተፍ ምርትና ምርታማነታቸውን በዘላቂነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ከቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት(LLRP) ጋር በመተባበር በድሬዳዋ አስተዳደር በዋሄል ክላስተር ሀሎቡሳ ገጠር ቀበሌ ለሚገኙ አርሶና አርብቶ አደሮች 150 ያህል ፍየሎች ድጋፍ ተደርጓል።
በድጋፍ ስነስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት በድሬዳዋ አስተዳደር በገጠር ቀበሌዎች የሚገኙ አርሶና አርብቶ አደሮችን በተለያዩ የገቢ አማራጮች በማሳተፍ ምርትና ምርታማነታቸውን በዘላቂነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው መሰል የእርባታ ፍየሎች ድጋፍ በቅርቡ ለ13 ማህበራት እንደሚደረግ ገልፀዋል።
አቶ ሮቤል አክለውም በበጀት አመቱ በጥቅሉ ለ42 ኢንተርፕራይዞች መሰል ድጋፎችን ለማድረግ መታቀዱንም አስታውቀዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና፣ውሐ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢህሳም ሁሴን በበኩላቸው ፕሮጀክታቸው የገጠሩን ማህበረሰብ ከጠባቂነት በማላቀቅ ኑሮውን የሚያሻሽሉ ተግባራትን አቅዶ እየተገበረ መሆኑን ገልፀው አሁን በዋሄል ክላስተር በሀሎቡሳ ቀበሌ ለሚገኙ 3 ማህበራት 150 ያህል ፍየሎች ድጋፍ መበርከቱን ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አልዪ በበኩላቸው በአስተዳደሩ ከከተማው ባሻገር በአራቱም የገጠር ክላስተሮች የሚገኙ 15 ኢንተርፕራይዞች ተቋማቸው ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀው በዚህም ማህበረሰቡ ዘላቂ ገቢ እንዲኖረው እንደሚያስችለው አብራርተዋል።
በሀሎቡሳ ቀበሌ የሚገኙት ኢንተርፕራይዞች አባላት የሆኑትና ድጋፉ የተደረገላቸው አርሶና አርብቶ አደሮች በወቅቱ ባጋሩን ሀሳብ እንዳሉት ቢሮውና ፕሮጀክቱ ባደረጉላቸው የቤት እንስሳት ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው በዚህም ከእርሻ ስራቸው ጎንለጎን በአማራጭ ገቢ መስገኛ መሳተፋቸው ኑሯቸውን እንደሚደግፍላቸው ገልፀዋል፤ ለዚህም አመስግነዋል።
©️ DireTvአማርኛ | ታህሳስ 09 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
Repost from E-LMIS - ብቁ
🌏✈️ውጪ ሀገር/UAE የመስራት ህልም አሎት?
🚀በሥራና ክህሎት ሚንስቴር በቀረበው የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት በተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል። አሁንም በዚሁ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ወደተባበሩት አረብ ኤምሬትስ/UAE/ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች የሰው ሃይል ይፈለጋል።
📌የኮንትራት ቆይታ:ሁለት አመት
📌ተፈላጊ ፃታ:ወንድ
🚧የሞያ ዘርፎች:-
1.Construction Laborers (የኮንስትራክሽን ሰራተኛ / ረዳት)
2.Mason(ግንበኛ)
3.እስቲል ፊክሰር (ፌራዩ)
4.Shuttering Carperter (አናፂ)
5. Delivery Boy (ሞተረኛ)
6. Walkers (እግረኛ ተላላኪ)
7. Plumber (የቧንቧ ሰራተኛ)
8. Electrician (የኤሌክትሪክ ሰራተኛ)
9. Scaffholders (የብረት መወጣጫ ባለሞያ)
10. Ductmen (የቬንትሌሽን ባለሞያ)
11. Supervisors and Foreman
12. Timekeepers (የሰራተኛ ሰአት ተቆጣጣሪ)
13. Camp Boss Assistant (የካምፑ አለቃ ተጠሪ)
☝️በተዘረዘሩት የሞያ ዘርፎች ለመወዳደር https://forms.lmis.gov.et/triple-one-uae/ በመግባት ፓስፓርት፣ የሰራተኛ መለያ ቁጥር/Labor id/፣ የነዋሪነት መታወቂያ እና አስፈላጊ መረጃዎችን በማስገባት ከታህሳስ 08 እስከ ታህሳስ 14 2018 መወዳደር ይቻላል።
💰የትኬት፣ የጤና ምርመራ እና ቪዛ በአመልካቾች የሚሸፍኑ ወጪዎች መሆኑን እንገልፃለን። ሌሎች በስራ ቆይታ ላይ የሚያስፈልጉ የመኖርያ ቤት፣የማብሰያ ክፍልእና ከነማብሰያ እቃዎች፣ኢንሹራንስ እና የህክምና ወጪ በአሰሪው የሚሸፈኑ ወጪዎች ይሆናል።
በ9138 ነጻ የጥሪ ማእከል ይደውሉ።
ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ከሶስተኛ ዙር ትግበራ የተሻለ አፈፃፀም እየተመዘገበ መሆኑ ተገለፀ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በስሩ ከሚገኙ የወረዳ የአንድ ማዕከል አስተባባሪ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር "ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ' ፕሮጀክት የሦስተኛው ዙር አጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎች ትግበራ የ 5 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በተለይ የስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍን በማሻሻል በኩል ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
'ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ' ከመጀመሪያውና ከሁለተኛው ዙር የስራ አፈፃፀም ተሞክሮ እየተወሰደ ክፍተቶች እየተሞሉ በሦስተኛው ዙር የፕሮጀክቱ አፈፃፀሙ የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩ የሁሉም ወረዳዎች የሦስተኛው ዙር 'ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ 'ፕሮጀክት የስራ ቅጥር አፈፃፀም እና አጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎች ትግበራ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
#DireTvአማርኛ | ታህሳስ 08 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ከተለያዩ የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 7/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የተቋማትን አቅም በማጠናከር የተሻለ አፈጻጸም እንዲያስመዘግቡ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን EAC ፕሮጀክት ለኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተለያዩ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ
የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን EAC ፕሮጀክት ከሚተገብራቸው ስራዎች አንዱ የተቋማትን አቅም መገንባት መሆኑ ይታወቃል፡፡ከነዚህ ተቋማት አንዱ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡
በዚህ መሰረት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚገኘው EAC ፕሮጀክት በዛሬው እለት ለኮሌጁ አምስት ዴስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች፣አንድ ኤልሲዲ ፕሮጀክተር እና አንድ ፕሪንተር ድጋፍ አድርጓል፡፡
በድጋፍ ርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት የአካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱ መሀመድ ድጋፉ ከኮሌጁ ጋር የምንሰራቸውን ስራዎች ወደላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር በአንጻሩ ከኮሌጁ የምናገኛቸውን የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች አሰተማማኝ ደረጃ ላይ ያደረሰ ብለዋል፡፡
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ከአካባቢ ጥበቃ EAC ፕሮጀክት የተደረገው ድጋፍ ተቋማትን በስራና በቴክኖሎጂ ለማስተሳሰር ያለው ሚና የላቀ እና በሌሎችም ተቋማት ሊለመድ የሚገባው ምሳሌ የሚሆን መልካም ተግባር ነው ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን አክለውም ያለን የስራ ግንኙነት የላቀ ደረጃ የደረሰ መሆኑን ማሳያ ሲሆን ኮሌጁም ለፕሮጀክቱ እያደረገ ያለውን ድጋፍ በአይነትና በጥራት አንዲጨምር ትልቅ ኃላፊነት ለኮሌጁ የሰጠ ነው ብለዋል፡፡
የEAC ፕሮጀክት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ በላይነህ ደስታ የተሰጡት ድጋፎች ከኮሌጁ ጋር አብሮ ለመስራትና የፕሮጀክቱን አላማዎች በቀላሉ ከምናሳካባቸው መንገዶች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ለስራው መሳካት የተባበሩትን አካላት ሁሉ አመስግነዋል ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን ያደረሰን መረጃ ያመላክታል
#DGC
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
<<የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከድሮ እሳቤ በመውጣት ትምህርትና ስልጠናቸውን የአሰራር ሂደታቸውን የስራ ፈጣሪነት የተላበሰ እንዲሆን ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡>>
#ዜና|በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሞችን ስርዓቶች አስተሳሰብ እና ስራ ፈጣሪነት ሚናዎች እንዲሁም ልምዶችን መለወጥ የሚያስችል ስልጠና ለኮሌጁ ማህበረሰብና ለባለ ድርሻ አካላት በዛሬው እለት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ተቋማትን ስንገነባ የስራ ፈጣሪነት የተላበሱ ሆነው እንዲገነቡ በርካታ ስራዎችን እየሰራን ቆይተናል ያሉት በስልጠናው ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ የቢሮው ኃላፊ አያይዘውም መንግስታችን ኢንተርፕሩናል መንግስት እንደመሆኑ መጠን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ይህንን ተረድተው ከተለመደው አሰራር በመውጣት ተግባራዊ እንቅስቃሴዎችን ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡ይህንንም እሳቤ በማህበረሰቡ ዘንድ በማስረጽ ረገድ EDI የሚሰራው ስራ ትልቅ ነው ብለዋል፡፡በመጨረሻም በዚህ ስልጠና የተገኘውን ግብአት በመጠቀም ኮሌጁን ኢንተርፕሩናል ኮሌጅ እንዲሆን ሁሉም የኮሌጁ አካላቶች እንዲሁም ባለ ድርሻ አካላት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
ይህ በዛሬው እለት ከ EDI ጋር በመተባባር የሚሰጠው ስልጠና ከመንግስት እንደ ቢሮ ያለ እሳቤ ነው ይህንን እሳቤ ደግሞ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም በለ ድርሻ አካላቶች ከወቅቱ ጋር መራመድ የሚችሉና የስራ ፈጣሪነትን የተላበሱ ሊሆኑ ይገባል ያሉት የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ አያይዘውም ከዚህ በፊት ስንሰራበት የነበረውን አሰራር በመቀየር ከአዲሱ እሳቤ ጋር ትምህርትና ስልጠናዎችን አስተሳስረን ልንሰጥ ይገባል ብለዋል፡፡
አዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ በርካታ ጉዳዮችን ይዞ የመጣ እንደ መሆኑ መጠን ኮሌጃችንን በአዲሱ እሳቤ የተቃየኘ የትምርትና ስልጠና ስራዎችን ለመስራት ከመቼውም ጊዜ በላይ ወደ ተግባር ለማስገባት እየሰራ ይገኛል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ የኮሌጁ ዲን አያይዘውም በተያዘው በጀት አመት የዘርፉን እሳቤ መቀየር የሚችሉ እንዲሁም የኮሌጁን እና የአካባቢውን ማህበረሰብ ሊለውጡ የሚችሉ በርካታ ስራዎችን እየሰራን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስፈልጉ ለውጦችን ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ጋር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡
በዛሬው እለት በኮሌጁ እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ስልጠና ሲሆን ስልጠናውንም ከEDI በመጡ አሰልጣኝ አቶ ቴዎድሮስ አበበ አማካኝነት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በስልጠናው ላይም የሽራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች፣ከፍተኛ ባለሙያዎች፣የኢንዱስትሪ አማካሪ የቦርድ አባላት፣የኮሌጁ ሰራተኞች እና አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን የዘርፉን ለውጥ የመምራት አስተሳብን የመላበስ እንዲሁም የተቋሙን የኢንተርፕራይዝ ልማት አስተዳደርና የራስን ገቢ በዘላቂነት የማመንጨት ሂደት ውስጥ የሚገጥሙ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ሰለባለ ድርሻ አካላቶች በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ የሚያስችል ስልጠና እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 07/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የአርዳይታ ግብርና ቴ/ሙ/ስ/ኮሌጅ አመራሮችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡
የአርዳይታ ግብርና ቴ/ሙ/ስ/ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት ከሚተገበርባቸው 24 የሚሆኑ የሀገሪቱ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አንደኛው ሲሆን በዚህም የኮሌጁን ዲኖች ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ያለውን የስራ እንቅስቃሴ ለመመልከት እንዲሁም በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ያለውን ተሞክሮ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን የስራ ልምድ ልውውጥ በኮልጁ ማካሄድ ችለዋል::
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብር ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ የEASE ፕሮጀክት ትግበራን ጨምሮ ጠቅላላ በተቋም የተመዘገቡ የአፈፃፀም ውጤቶችን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከምስረታው አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል::
ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው አቀባበልና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻ በማድረግ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ካሳየው የስራ አፈፃፀም ብዙ ልምዶችን መቅሰም መቻላቸውንም ገልፀዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው የልምምድ ልውውጥ መርሃ-ግብርም የተሳካ ቆይታን በኮሌጃችን ማድረግ ችለዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 6/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኮሌጁ እየሰለጠኑ የሚገኙ ሰልጣኞች ከዘመኑ ጋር እኩል እንዲራመዱ እና ለቀጣይ የስራ ጊዜ ዝግጁ እንዲሆኑ እየሰራ እንዳለ ገለጸ፡፡
#ዜና|የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች በዘንድሮ አመት ኮሌጁን ከተቀላቀሉ እንዲሁም ከነባር ሰልጣኞች ጋር የጋራ ውይይት በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡
በውይይ መድረኩ ላይ በመገኘት እንዲሁም ከሰልጣኞች ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ እንዲሁም ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም ወጣቶች ቢያንስ የአንድ ሙያ ባለቤት እንዲሆኑ እንዲሁም ቀጣዩን የስራ ጊዜ በICT የተደገፈ እንደመሆኑ መጠን ሰልጣኞች ለዚህ ደግሞ ዝግጁ እንዲሆኑ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራን ከነዚህም ውስጥ የኢንተርፕሩነርሺፕ፣የዲጂታላይዜሽን፣የስራ አፈላለግ እና የህይወት ክህሎት ስልጠና እየሰጠን እንገኛለን ያሉ ሲሆን የኮሌጁ ዲን አያይዘውም ከኮሌጃችን ሰልጥነው የሚያጠናቅቁ ሰልጣኞቻችን በሙሉ ከሚሰለጥኑት ስልጠና በተጨማሪ ሌሎች የሙያ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ እና በተለያዩ ስራዎች እንዲሳተፉ ሰፊ ስራዎችን ሰርቷል ብለዋል፡፡
ሰልጣኞች ስልጠናቸውን አጠናቀው ወደ ስራው አለም ሲቀላቀሉ በአግባቡ የተጣለባቸውን ኃፊነት እንዲወጡ ለስራ ዝግጁ የሚያደርጉ ስልጠናዎችን ከመደበኛው ስልጠና ጎን ለጎን እንዲወስዱ እየተደረገ እንዳለ ለሰልጣኞቹ ያብራሩ ሲሆን በመጨረሻም በኮሌጁ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች ከዘመኑ ጋር እኩል የሚራመዱ እና ለቀጣይ የስራ ጊዜ ዝግጁ እንዲሆኑ እንዲሁም ሃገር ወዳድ ዜጎች እንዲሆኑ ሁሉም አካላት በጋራ በመሆን መስራት ይገባናል ብለዋ፡፡
በዛሬው እለት በተደረገው የጋራ የውይይት መድረክ ላይ ሰልጣኞች ከኮሌጁ ጋር ስላላቸው የግንኙነት አግባብና መብትና ግዴታ ሰነድ የቀረባ ሲሆን በተጨማሪም 5 ሚሊዮን ዜጎች ስለሚሳተፉበት Ethio coders ስልጠና ማብራሪያ ተሰጥቷል በቀጣይም ከመደበኛ ስልጠናው ጎን ለጎን ሰልጣኞች ስልጠናውን እንደሚወስዱ በእለቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
