1 063
Suscriptores
-224 horas
-77 días
+130 días
Archivo de publicaciones
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሶሻል ሚዲያ ላይ በተሰራጨው ሀሰተኛ መረጃን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሰፊ የሪፎርም ማዕቀፍ ነድፎ በመተግበር ላይ ነው። ይህም ሰባት ዋና፣ ዋና አምዶች ያሉት ነው። አምዶቹም፦
1. የኢንዱስትሪ፣ ሙያ ምድብ እና ክፍያና ጥቅማ ጥቅም ማሻሻል
2. የሙያ ብቃት ግንባታ
3. የአገልግሎት ማላቅ
4. ዘመናዊ የሰው ኃይል አመራር
5. የብዝሃነትና አካታችነት ማረጋገጥ
6. ዲጂታላይዜሽ ማስፋፋት እና
7. የአመራር አቅም መገንባት ናቸው።
እነዚህ ሥራዎችን ለማስተግበር ፈጻሚ እና ባለቤት ተቋማት በዌቮች (Wave I, Wave II & Wave III) ተከፋፍለው ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን አፈጻጸሙም ተስፋ ሰጪ ነው።
ከሰባቱ የሪፎርም አምዶች አንዱ የአገልግሎት አቅርቦት ሂደቱን ማላቅ ነው። በተደረገው የአፈጻጸም እንቅስቃሴ ተጨባጭ እና በኢትዮጵያ የመንግስት አገልግሎት ማሻሻል ብቻ ሣይሆን ማላቅም እንደሚቻል በተግባር ታይቷል። የፌዴራሉን ጨምሮ እሰከ እዚህ ወር ባለው ጊዜ 21 የመሶብ (MESOB:-Modern Ethiopia Services for Organized Benefits) ተገንብተው በሥራ ላይ ናቸው።
በየማዕከላቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ የሆኑ አገልግሎቶች ብቻ ናቸው። የICT እውቀት የሌላቸውን ዜጎች የሚታገዙበት ሥርዓት እንዲኖረው ተደርጎ የተነደፈም ነው። በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ ከተሞች ለማስፋፋት በመረባረብ ላይ እንገኛለን። ይህንን ሥራ የሚመራ እና በአፍሪካ ተምሣሌታዊ ተግባር እና ቁመና ያለው አደረጃጀት እና ሥርዓት ለመፍጠርም ጥረት እየተደረገ ነው።
ከእነዚህ ተግባራት አንዱ የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ግንባታ ማካሄድ ነው። የግንባታ የጨረታ ሰነድ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሳይሆን በኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC) ተዘጋጅቶ እና በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ጸድቆ በ egp.mofed.gov.et አለም አቀፍ ጨረታው ወጥቷል። ለእዚህም ዲዛይን እና ግንባታ ግልጽ ጨረታ ውድድር የዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ተቋራጮች እየተሳተፉ ነው። በጨረታው ሂደት ማን እንደሚያሸንፍ የሚታወቅ ነገር የለም። ተወዳዳሪዎቹ ለመገምገም ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC)፣ ከከተማ ልማትና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጡ ባለሙያዎች ተደራጅቶ በሥራ ላይ ናቸው። አሸናፊው ከሂደቱ ይለያል ተብሎ ይጠበቃል።
እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሂደቱን የሚያደናቅፍ እና መሠረት የሌለው እና የተዛባ መረጃ በአንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቷል። ትክክለኛ መረጃው ከላይ የገለጸው ስለሆነ ለእራሱ ታዕማኒነት ሲል ማህበራዊ ሚዲያው የተዛባውን መረጃ እንዲስተካከል እመክራለሁ።
ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሶሻል ሚዲያ ላይ በተሰራጨው ሀሰተኛ መረጃን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሰፊ የሪፎርም ማዕቀፍ ነድፎ በመተግበር ላይ ነው። ይህም ሰባት ዋና፣ ዋና አምዶች ያሉት ነው። አምዶቹም፦
1. የኢንዱስትሪ፣ ሙያ ምድብ እና ክፍያና ጥቅማ ጥቅም ማሻሻል
2. የሙያ ብቃት ግንባታ
3. የአገልግሎት ማላቅ
4. ዘመናዊ የሰው ኃይል አመራር
5. የብዝሃነትና አካታችነት ማረጋገጥ
6. ዲጂታላይዜሽ ማስፋፋት እና
7. የአመራር አቅም መገንባት ናቸው።
እነዚህ ሥራዎችን ለማስተግበር ፈጻሚ እና ባለቤት ተቋማት በዌቮች (Wave I, Wave II & Wave III) ተከፋፍለው ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን አፈጻጸሙም ተስፋ ሰጪ ነው።
ከሰባቱ የሪፎርም አምዶች አንዱ የአገልግሎት አቅርቦት ሂደቱን ማላቅ ነው። በተደረገው የአፈጻጸም እንቅስቃሴ ተጨባጭ እና በኢትዮጵያ የመንግስት አገልግሎት ማሻሻል ብቻ ሣይሆን ማላቅም እንደሚቻል በተግባር ታይቷል። የፌዴራሉን ጨምሮ እሰከ እዚህ ወር ባለው ጊዜ 21 የመሶብ (MESOB:-Modern Ethiopia Services for Organized Benefits) ተገንብተው በሥራ ላይ ናቸው።
በየማዕከላቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ የሆኑ አገልግሎቶች ብቻ ናቸው። የICT እውቀት የሌላቸውን ዜጎች የሚታገዙበት ሥርዓት እንዲኖረው ተደርጎ የተነደፈም ነው። በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ ከተሞች ለማስፋፋት በመረባረብ ላይ እንገኛለን። ይህንን ሥራ የሚመራ እና በአፍሪካ ተምሣሌታዊ ተግባር እና ቁመና ያለው አደረጃጀት እና ሥርዓት ለመፍጠርም ጥረት እየተደረገ ነው።
ከእነዚህ ተግባራት አንዱ የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ግንባታ ማካሄድ ነው። የግንባታ የጨረታ ሰነድ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሳይሆን በኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC) ተዘጋጅቶ እና በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ጸድቆ በ egp.mofed.gov.et አለም አቀፍ ጨረታው ወጥቷል። ለእዚህም ዲዛይን እና ግንባታ ግልጽ ጨረታ ውድድር የዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ተቋራጮች እየተሳተፉ ነው። በጨረታው ሂደት ማን እንደሚያሸንፍ የሚታወቅ ነገር የለም። ተወዳዳሪዎቹ ለመገምገም ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC)፣ ከከተማ ልማትና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጡ ባለሙያዎች ተደራጅቶ በሥራ ላይ ናቸው። አሸናፊው ከሂደቱ ይለያል ተብሎ ይጠበቃል።
እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሂደቱን የሚያደናቅፍ እና መሠረት የሌለው እና የተዛባ መረጃ በአንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቷል። ትክክለኛ መረጃው ከላይ የገለጸው ስለሆነ ለእራሱ ታዕማኒነት ሲል ማህበራዊ ሚዲያው የተዛባውን መረጃ እንዲስተካከል እመክራለሁ።
ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሶሻል ሚዲያ ላይ በተሰራጨው ሀሰተኛ መረጃን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሰፊ የሪፎርም ማዕቀፍ ነድፎ በመተግበር ላይ ነው። ይህም ሰባት ዋና፣ ዋና አምዶች ያሉት ነው። አምዶቹም፦
1. የኢንዱስትሪ፣ ሙያ ምድብ እና ክፍያና ጥቅማ ጥቅም ማሻሻል
2. የሙያ ብቃት ግንባታ
3. የአገልግሎት ማላቅ
4. ዘመናዊ የሰው ኃይል አመራር
5. የብዝሃነትና አካታችነት ማረጋገጥ
6. ዲጂታላይዜሽ ማስፋፋት እና
7. የአመራር አቅም መገንባት ናቸው።
እነዚህ ሥራዎችን ለማስተግበር ፈጻሚ እና ባለቤት ተቋማት በዌቮች (Wave I, Wave II & Wave III) ተከፋፍለው ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን አፈጻጸሙም ተስፋ ሰጪ ነው።
ከሰባቱ የሪፎርም አምዶች አንዱ የአገልግሎት አቅርቦት ሂደቱን ማላቅ ነው። በተደረገው የአፈጻጸም እንቅስቃሴ ተጨባጭ እና በኢትዮጵያ የመንግስት አገልግሎት ማሻሻል ብቻ ሣይሆን ማላቅም እንደሚቻል በተግባር ታይቷል። የፌዴራሉን ጨምሮ እሰከ እዚህ ወር ባለው ጊዜ 21 የመሶብ (MESOB:-Modern Ethiopia Services for Organized Benefits) ተገንብተው በሥራ ላይ ናቸው።
በየማዕከላቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ የሆኑ አገልግሎቶች ብቻ ናቸው። የICT እውቀት የሌላቸውን ዜጎች የሚታገዙበት ሥርዓት እንዲኖረው ተደርጎ የተነደፈም ነው። በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ ከተሞች ለማስፋፋት በመረባረብ ላይ እንገኛለን። ይህንን ሥራ የሚመራ እና በአፍሪካ ተምሣሌታዊ ተግባር እና ቁመና ያለው አደረጃጀት እና ሥርዓት ለመፍጠርም ጥረት እየተደረገ ነው።
ከእነዚህ ተግባራት አንዱ የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ግንባታ ማካሄድ ነው። የግንባታ የጨረታ ሰነድ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሳይሆን በኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC) ተዘጋጅቶ እና በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ጸድቆ በ egp.mofed.gov.et አለም አቀፍ ጨረታው ወጥቷል። ለእዚህም ዲዛይን እና ግንባታ ግልጽ ጨረታ ውድድር የዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ተቋራጮች እየተሳተፉ ነው። በጨረታው ሂደት ማን እንደሚያሸንፍ የሚታወቅ ነገር የለም። ተወዳዳሪዎቹ ለመገምገም ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC)፣ ከከተማ ልማትና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጡ ባለሙያዎች ተደራጅቶ በሥራ ላይ ናቸው። አሸናፊው ከሂደቱ ይለያል ተብሎ ይጠበቃል።
እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሂደቱን የሚያደናቅፍ እና መሠረት የሌለው እና የተዛባ መረጃ በአንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቷል። ትክክለኛ መረጃው ከላይ የገለጸው ስለሆነ ለእራሱ ታዕማኒነት ሲል ማህበራዊ ሚዲያው የተዛባውን መረጃ እንዲስተካከል እመክራለሁ።
ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የመንግስት ሰራተኛው በለውጥ ትግበራው ሂደት ላይ የራሱን ሚና መወጣት እንዲችል ተገቢውን መረጃ መስጠትና ግንዛቤ ማስጨበጥ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በበጀት አመቱ ከመደበኛ ስራዎች ጎን ለጎን በመንግስት አቅጣጫ መሰረት ትኩረት ተደርጎባቸው በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ለተቋሙ ሰራተኞች የግንዛቤ መፍጠርያ መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ ላይ እንደ ሀገር በቀጣዮቹ 2ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅደው ከተጀመሩ ቁልፍ ተግባራት መካከል እንደ ቴክኒክና ሙያ ተቋም እንዲተገበሩ ከተቀመጡ ዝርዝር ተግባራት ውስጥ በተቋም ደረጃ የተዘጋጀው እቅድና አሁን የደረሰበት አፈፃፀም ቀርቦ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል::
ይህ የግንዛቤ መድረክ በዋናነት ያስፈለገው የመንግስት ሰራተኛው በመንግስት የሚወርዱ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ግልፅነት ተፈጥሮለት ታች ፈፃሚው ድረስ እንዲወርድ ለማስቻል ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም ሀገራችን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ስርዓትን እየዘረጋች እንደምትገኝና ጊዜው ከሚሰጠን ቴክኖሎጂዎች ጋር በመጣጣም የአገልግሎት አሰጣጣችንን የተቀላጠፈ በማድረግ እንደ ተቋም የተገልጋይ እርካታን በዘላቂነት ማረጋግጥ ይጠበቅብናልም ብለዋል::
በግንዛቤ መስጫ መድረኩ በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ከተቀመጡት የ100% ግቦች.. የ "1" ግቦች እና የ "መቀነስ"ግቦች ጋር ተያይዞ የሚተገበሩ ዝርዝር ተግባራት ላይ በኮሌጁ ዲን አማካኝነት ገለፃ የተደረ ሲሆን በተጨሚሪም የ5million Initiative Program በተመለከተ አጠቃላይ ሰራተኛው የሚሰለጥንበት አግባብ ላይ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠርም ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 2/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የተርንኪ ፕሮጀክት ዳግም ውልደት !
ከአመታት በኋላ የቀድሞው ተርንኪ ፕሮጀክት የአሁኑ በድሬዳዋ ስራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምርት ማዕከል ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ማሽኖችን ጠግነን ለምርት ዝግጁ አድርገናል።
በቅርብ ቀናት ሙሉ በሙሉ ወደ ምርት በመግባት “እያመረትን እናሰለጥናለን፤ እያሰለጠንን እናመርታለን” መርሀችንን ተግባራዊ በማድረግ ተቋማዊ አቅማችንን እናሳድጋለን።
©️ Robel Getachew
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በስሩ ካሉ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ጋር ውይይት ተደረገ።
በዚህም ውይይት ላይ የአንድ ማዕከል አመራሮች የተገኙ ሲሆን የሶስተኛው ዙር "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት አፈጻጸም ከፌደራል በመጣ የሱፐርቪዥን ብድን የተሰጠ ግብረመልስ ላይ እና አጠቃላይ ስለሚሰጠው አገልግሎትና እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ተግባራት እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ተወያይተዋል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አዲስ ለተመደቡ የአንድ ማዕከል አመራሮች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው አንድ ማዕከላቱ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለዜጎች ስራ መፍጠር ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግና ከዚህ ጋር በተያያዘ መረጃዎች በጠራ መልኩ ተይዘው በየአካባቢው ያለውን አቅምና ጸጋ ሊጠቀሙ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን ሞልቶ የተሻለ ስራ መስራት የሚችል አመራር መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ ስራ ፈላጊውን ዜጋ ወደ ስራ የሚያስገቡ እንደ ብቃት ያሉ ፕሮጀክቶችን የተሳካ ለማድረግ በትጋት እንዲሰሩ በማሳሰብ በአስተዳደሩ እና በወረዳ ደረጃ የተመሰረተውን የሥራና ክህሎት ምክር ቤት አቅም መጠቀም ይገባል ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 1/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽን(Job fair) ዝግጅት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ምክክር ተደረገ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ይህን የምክክር መድረክ ሲያዘጋጅ የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽኖች አሰሪውና ስራ ፈላጊው በአንድ ቦታ የሚገናኙበትና ሥራ ፈላጊው አሰሪው ላቀረበው ክፍት የሥራ ቦታ የሚያመለክትበት ቀጣሪው ቃለመጠይቅ የሚያደርግበትን መድረክ በልዩ ሁኔታ ለማካሄድና ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ ትኩረት እንደተሰጠው የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል፡፡
በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ተሳታፊ የሆኑ ባለድርሻ አካላት በአጠቃላይ ሥራ ፈላጊውና (job seekers) እና ቀጣሪዎች (Employers) በቀላሉ መገናኘት እንዲችሉ መንግሥት ከሚሰጣቸው የስራ ስምሪት አገልግሎቶች መካከል ሥራና ሰራተኛ ማገናኘት ኤግዚብሽን (Job fair) ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በማስተካከልና በመናበብ ሊሰሩ በሚችሉበት አግባብ ላይ በሰፊው ተወያይተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 1/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በእርሻ እና ከብት እርባታ ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በኩል ከሶስት መቶ ሺህ ብር በላይ ድጋፍ ተሰጠ።
የግብርና ውሃ ማዕድና ኢነርጂ ቢሮ በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በሥራና ክህሎት ቢሮ በኩል 15 ለሚሆኑ በእርሻ ስራና በከብት እርባታ ለተደራጁ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተር ፕራይዞች 350ሺ ብር ድጋፍ አድርጓል::
በእርሻ እና በከብት እርባታ ዘርፎች ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በኩል ከሶስት መቶ ሺህ ብር በላይ ድጋፍ ተሰጠ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና፣ውሃ፣ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በስራና ክህሎት ቢሮ በኩል 15 ለሚሆኑ በእርሻ ስራና በከብት እርባታ ለተደራጁ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች 350ሺ ብር ድጋፍ አድርጓል።
ከአራቱ የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡት ኢንተርፕራይዞች የተሰጠው ድጋፍ በአጠቃላይ ድጋፍ ለማድረግ ከታሰበው 500ሺ ብር ላይ 70 በመቶው ሲሆን ቀጣይ የሚያሳዩት የስራ አፈፃፀም ታይቶ ቀሪው 30 በመቶው እንደሚለቀቅላቸው ታውቋል።
የድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት ኢንተርፕራይዞቹ በተደረገላቸው የገንዘብ ድጋፍ በሚያደርጉት ውጤታማ የስራ እንቅስቃሴ በአረአያነታቸው ለሌሎች ተመሳሳይ ኢንተርፕራይዞች ድጋፉ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በመሆኑም ድጋፉ የተደረገላቸው ኢንተርፕራይዞች የስራ ባህላቸውን በመቀየር እና የተገኘውን የስራ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመለውጥ እንዲተጉ አሳስበዋል ::
የግብርና ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው ፣ መንግስት በሀገር ደረጃ ድህነትን ለማጥፋት እና ከጥገኝነት መላቀቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ድሬዳዋም ይህንን ለማሳካት ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረው ከነዚህም ውስጥ ደግሞ አንዱ የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል::
የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት
ስራ አስኪያጅ አቶ ኢሳም ሁሴን ድጋፉ በአይነቱ የተለየ መሆኑን ጠቅሰው ድጋፍ የተደረገላቸው ኢንተርፕራይዞች የ 50 ሺ ብር ቅድመ ቁጠባቸው ላይ የተጨመረላቸው መሆኑን ጠቁመዋል።
©️ DireTvአማርኛ | ህዳር 30 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
