es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 088
Suscriptores
Sin datos24 horas
+227 días
+1330 días
Archivo de publicaciones
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆች የ2016 ዓ.ም የሠልጣኝ ቅበላ የጥራት ኦዲት እየተደረገ እንደሚገኝ ገለጸ፤ ሰልጣኝ ትምህርትና ስልጠናዉን በተቀመጠዉ የስልጠና ጥራት ስታንዳርድ መሰረት እንዲሰለጥን አግባብነት ያለዉ ስልጠና ቅበላ መካሄዱን ለማረጋገጥ እንዲሁም ዜጎች ለትምህርትና ስልጠና የተሰጣቸዉን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተቋማት የስልጠና ጥራት ቁጥጥር ቡድን ከኮሌጆቹ በተሰበሰበ ሪፖርትና ማስረጃ መሰረት ጥራትና አግባብነቱን የማረጋገጥ ሥራን ይሰራል፤ በዚሁ መሰረት የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በሁለቱ  የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እና  እና በአምስት የግል ኮሌጆች በ2016 ዓ.ም የስልጠና ዘመን  የተቀበሏቸዉን ሰልጣኞች በቅበላ መመርያ መሰረት አካል ጉዳተኞችን በማካተት ቅበላዉን ስለማከናወናቸ መመዝገብ በሚገባቸዉ የሙያ ደረጃ ስለመመዝገባቸዉ ለዚሁ ሥራ በተዋቀረ የባለሙያ ቡድን ከጥር 13/2016 ዓ.ም ጀምሮ  መረጃዎችን ከኮሌጆች በማሰባሰብ  የሰልጠኝ ቅበላ የጥራት ኦዲት  ሥራዉን  በማከናወንና   ለተቋማት ግብረ-መልስ ለመስጠት በሥራ ላይ እንደሚገኝ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 27/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ኘሮጀክት ለተጠቃሚ ወጣቶች የሥራ አፈላለግ ክህሎት ስልጠና ኦረንቴሽን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ተሰጠ፤ በዚህም ወጣቶቹ ባለፉት ስድስት ወራት በኢንዱስትሪዎች ውስጥ የሥራ ላይ ልምምድ ማድረጋቸው ይታወቃል በቀጣይ ከስራ ጋር ለማስተሳሰር እንዲያስችላቸው ደግሞ ለተከታታይ አምስት ቀናት በሚወስዱት ስልጠና ሥራ የማፈላለግ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ ይሆናል፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 27/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

አስደሳች ዜና! የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ከተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም እና ከዓለም አቀፉ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት (Private Sector Development - PSD-E) ጋር በመተባበር በአይነቱ ልዩ የሆነ የውድድር መርሃ ግብብር አዘጋጅቷል፡፡ መርሃ ግብሩ በሀገራችን በተለያዩ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ኢንተርፕራይዞች ወደ መደበኛ ሥራቸው እንዲገቡ በዲጂታል ስነ-ምህዳሩ ላይ መፍትሄ አለን ለሚሉ ሥራ ፈጣሪዎች የሥልጠና፣ የምክር እና የተለያዩ አገልግሎቶችን ድጋፍ እንዲሁም የመነሻ ካፒታል ማግኘት የሚያስችል ነው፡፡ በዚህ መርሃ ግብር መሳተፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች በምታገኙት ማስፈንጠሪያ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ Exciting Announcement! 🚀 The Ministry of labor and Skills, in collaboration with UNDP Ethiopia and the GIZ Private Sector Development (PSD-E) project, is thrilled to announce the official launch of the Incubation Program! 🎉 This program has been specifically designed to provide technical assistance to Digital Entrepreneurs (DEs) who are passionate about becoming solution providers for crisis-affected communities. Aspiring digital entrepreneurs, this is your chance to shine! By joining our program, you will gain access to a wide range of valuable resources and support, including technical assistance, training, mentoring, and even seed funding. We firmly believe that this comprehensive package will pave the way for transformative success stories, empowering entrepreneurs like you to make a lasting impact on crisis-affected communities. Be sure to mark your calendars as the application deadline is fast approaching on 11 February 2024. The program, set to kick off on 26 February 2024, promises to be a game-changer in your entrepreneurial journey. To secure your spot, simply click on the link below and complete the application form: https://docs.google.com/forms/d/1TLfYpyD_9nXKjeN-6Drin-xfxuafaMniTKwTfbdLSPA/edit Apply now!

🌍 ስኬታማ ጥናታዊ ጉዞ (Study Tour) በጀርመን፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እና የትብብር እድሎች ዳሰሳ 🇪🇹🇩🇪 NIRAS ከኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር እና KFW ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በጀርመን ሀገር የተካሄደውን የጥናት ጉዞ ጠቃሚ ተሞክሮ በጥቂቱ ላካፍላችሁ ወደድኩ። ይህ ትምህርታዊና የስራ ጉዞ በኢትዮጵያ እና በጀርመን መካከል ያለውን ትብብር በማጎልበት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና አለምን ለመቃኘት ያለመ ነው። ጥናታዊ ጉብኝታችን በመጀመሪያው ቀን በቦን፣ ጀርመን በሚገኘው UNEVOC እና bibb አስደናቂ ውይይቶችን የመካፈል እድል አግኝተናል። በእለቱም በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የሁለቱ ሀገራት የትብብር መንገዶች ላይ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ ያላቸው ገለጻዎችና አበረታች ውይይቶች ተካሂደዋል። የአለም አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ማዕከል በሆነው UNEVOC የተደረገው ጉብኝት በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን በተመለከተ ጠቃሚ ግንዛቤዎችን አግኝተንበታል። በተለይም የራሳችንን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓት ለማጎልበት ከሀገረ- ጀርመን ሊለምዱ እና ሊተገበሩ የሚችሉ አዳዲስ አካሄዶችን ለመዳሰስ እድሉን አግኝተናል። የጀርመኑ የፌዴራል ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት bibb ላይ የተካሄዱት ውይይቶችም በተመሳሳይ ትልቅ ትምህርት የሰጡ ነበሩ። በሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት፣ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ስለዘረጓቸው ሽርክናዎች እና በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አማካኝነት የሥራ ገበያን ፍላጎት በማሟላት ረገድ ስላሏቸው ልምዶች ውይይት አድርገናል። በተለይም የቢአይቢቢ ባለሙያዎችና አመራሮች የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠናን ዘመኑ ከደረሰበት ቴክኖሎጂ አኳያ በመቅረጽ ረገድ ያላቸው የፈጠራ ሀሳብና ለትግበራው የሚያሳዩት ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነበር። በጥናት ጉብኝቱ ወቅት የትምህርት ሚኒስቴርን፣ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን፣ የቻንስለር ሚኒስቴርን ጨምሮ በባቫሪያ የሚገኙ ሌሎች ተቋማትን ጨምሮ የተለያዩ ታዋቂ ተቋማትን ጎብኝተናል። እነዚህ ጉብኝቶች በጀርመን ስላለው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ገጽታ አጠቃላይ ግንዛቤን እንድንጨብጥ እና የትብብር መስኮችን እንድንመረምር አስችሎናል። በተመሳሳይ የተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማትን በግልም ሆነ በመንግሥት ባለቤትነት የተያዙ እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች መፈልፈያ ማዕከላትን ለመጎብኘት ጥሩ አጋጣሚ አግኝተናል። ተቋማቱ በምን አግባብ ተማሪዎችን ለስራ ገበያው እያዘጋጁ እና ስራ ፈጣሪነትን እያሳደጉ መሆናቸውን ማየታችን ሌላኛው ጠቃሚ ተሞክሮ ነበር። በአጠቃላይ ይህ የጥናት ጉዞ በኢትዮጵያና በጀርመን መካከል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ አዳዲስ የትብብር መንገዶችን ከፍቷል። ለኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓት መጎልበትና ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያግዙ አዳዲስ አመለካከቶችን፣ አዳዲስ ሀሳቦችን እና ተግባራዊ ግንዛቤዎችን ሰጥቶናል። ለተከታታይ 7 ቀናት ያካሄድነው ጥናታዊ ጉዞ በኢትዮጵያ የክህሎት ልማትን ለማሳደግ እና አለም አቀፍ አጋርነትን ለማሳደግ ትልቅ ልምድና እውቀት የተቀሰመበት ነበር። ጥር 25/2016 ዓ.ም ሙኒክ - ጀርመን Via Robel Getachew Head of Dire Dawa BoLS

photo content
+8

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የመንግስት ሰራተኞች  የብልፅግና ፓርቲ  መሠረታዊ ድርጅት የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ። በተካሄደው ኮንፈረንስ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ አሚን አብዱላሂ  እንዳሉት መሠረታዊ ድርጅቱ ባለፉት 6 ወራት በርካታ የፖለቲካ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀው  በተለይ ደግሞ ከመንግስት ስራ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የተገኘው ውጤታማ አፈጻጸም በጥምረት መቅረቡ ፖለቲካውን ህብረተሰቡን የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ ለመስራት  ወሳኝ ሚና እንዲጫወት አድርጎታል ብለዋል። በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የመሠረታዊ ድርጅቱ የስድስት ወር የዕቅድ ክንውን ሪፖርት፣ የቀጣይ 6 ወር እቅድ፣ የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ሪፖርት ቀርቦ ሰፉ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን        በመጨረሻም የእጩነት ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ አባላትን ወደ ሙሉ አባልነት በማሸጋገር እና የቀጣይ 6 ወራት መሠረታዊ ድርጅቱ እና  የህዋስ አደረጃጀትን የሚመሩ የመሠረታዊ ድርጅትና ህዋስ አመራር ምርጫን በዴሞክራሲያዊ መንገድ  በማከናወን  ፕሮግራሙ ተጠናቋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 25/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለሴት አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለሴት የኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራንና ለኤጀንሲው ባለሙያዎች አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኞች መስጠት ተቸሏል፡፡ በዚህም ስልጠናው በኮሌጆችና በኤጀንሲው የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች ከማይንድ ሴት እስከ አመራርነት ባሉ ሃሳቦችና ተሞክሮዎችን የተመለከቱ ሲሆን ከዚህ ባለፈ የእርስበርስ ግንኙነትን ሊያጠናክሩና ወደ መጡበት ተቋም ሲለሱ ግብ ተኮር የሆነ ውጤት የሚያስገኝ ስራ መስራት የሚያስችላቸውንግንዛቤ እዲፈጥሩ ማስቻሉን የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ኢንደስትሪው ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ከፍ የሚያደርጉ በሁለትዮሽ መደጋገፍ ላይ የተመሰረቱ ስራዎች በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና አሰልጣኞች ካላቸው የትምህርትና የተቋም ውስጥ የስራ ልምድ በተጨማሪ በሙያቸው የሚጠበቅባቸውን የእውቀት፤ የክህሎት እና የሙያ ስነ-ምግባር  ከኢንዱስትሪው እንዲቀስሙ እንዲሁም በኢንዱስትሪ ውስጥ የቴክኖሎጂ እና የአሰራር ክፍተት ካለ ችግሩን በመፍታት ከኢንዱስትሪው ጋር መልካም ግንኙነት እና ታማኝነትን ለመፍጠር   የአሰልጣኞች ኢንዱስትሪ ውስጥ ቆይታ  /TVT TRAINERS INDUSTRY ATTACHMENT/ ይተገበራል፤፤ በዚህም መሰረት የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት ቡድን የAUTOMOTIVE  ዘርፍ አሰልጣኝ መምህራን ውስጥ  በMOENCO ድሬደዋ ቅርንጫፍ ላፉት 20ቀናት ቆይታ ሲያደርጉ ቆይተዋል፤ በዚህ ቆይታቸውም 1.  A,B,C,D -Maintenance Service 2.  Diagnosing ABS,Motor,AT 3.  EFI-OBD Operation 4.  AT/EC Diagnostic እና ሌሎችም በዘርፉ በ21ኛው ክ/ዘ የተደረሰበት ክህሎት፤እውቀት እና የኢንዱስትሪውን የስራ ባህል ማግነጥ መቻላቸውን በተደረገው ምልከታ መገንዘብ የተቻለ ሲሆን፤ የካምፓኒው  ሃላፊዎችም እና አስተባባሪዎችም የአሰልጣኞች  ያላቸውን ክህሎት እያካፈሉ መሆኑን ይህ ግንኙነትም በተለይ ለሰልጣኞች የስራ እድል ምችችት በር ከፋች መሆኑን ገልፀዋል፤፤ የካምፓኒው አመራሮች የዘርፉን ስትራቴጂ በመረዳት አሰልጣኞቹን ተቀብለው እያደረጉ ላሉት የቴክኖሎጂ እና እውቀት ሽግግር በዘርፉ ያለን የስልጠና ጥራት እና የኢንዱስትሪውን ተረካቢነት እያረጋገጠ ያለ ቅንጅታዊ አሰራር መሆኑን አቶ ታሪኩ ለገሰ  ለካምፓኒውና ለባለሙያዎቹ  ምስጋና አቅርበው  ውጤታማ የሆነ ቀሪው ጊዜ እንዲኖራቸው አሳውቀዋል ፤፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 21/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት አዲሱን የዘርፉን ፖሊሲና ስትራቴጂ መሰረት በማድረግ የተቋማት አቅም ለማሳደግ እንዲያስችል ለሁለቱ የመንግስትና የግል ኮሌጆች የዲፓርመንት ተጠሪዎች፣ የስልጠና አስተባበሪዎች እንዲሁም ለኤጀንሲው ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡ በዚህም ኮሌጆቹ አዲሱን የዘርፉን ፖሊሲና ስትራቴጂ የትግበራ ደረጃ ከፍ ለማድረግ እንዲያስችል ከዚህ በሚከተሉት ዋናዋና የትግበራ ማንዋሎች ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ 1. Technical and Vocational Training (TVT) Green TVT Guideline፤ 2. Assessment and Certification Management Manual፤ 3. የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የሙያ ደረጃ አዘገጃጀትና ትግበራ ማኑዋል፤ 4. VOCATIONAL GUIDANCE AND COUNSELING GUIDELINE FOR ETHIOPIAN TVT፤ 5. የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት አመታዊ የውድድርና ደረጃ መወሰኛ  ማኑዋል፤ 6. የትብብር ስልጠና ማስተግበሪያ ማኑዋል፤ 7. Occupational Competence Assessment Tool Development Manual፤ በመሆኑም የስልጠና ተቋማት በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ መሰረት ሰልጣኞችን ለማሰልጠንና ዘርፉን ተመራጭ በሆነ መልኩ ዜጎችን ለማገልገል እንዲያስችል ታሳቢ ያደረገ የአቅም ገንባታ ስልጠና መስጠቱ አስፈላጊ በመሆኑ ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 20/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት ቡድን ለኢትዮ-ጣልያን እና ድሬዳዋ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የ ELECTRICAL ELECTRONICS አሰልጣኝ መምህራን ለ15ቀናት በ POER SYSTEMS SYMULATION AND ANALISIS, PSIM, MATLAB, ETAB, MULTYSYSTEM and MOTOR XP የሶፍትዌር እና የተግባር ስልጠናዎችን ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በተጋበዙ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና አስጀምረዋል፤፤ ስልጠናው  አሰልጣኞች ካላቸው እውቀት በተጨማሪ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካሉ አሰልጣኞች በሙያው እውቀትን እና ልምዶች ለመካፈል እንዲሁም የቴሙትስ አሰልጣኞች ያላቸውን የካበተ የተግባር እውቀት እና ልምዶችን ለዩኒቨርስቲ አሰልጣኞች የሚያካፍሉበት የሁለትዮሽ እውቀት ሽግግር የሚደረግበት አጋጣሚ መሆኑን ተጋባዥ አሰልጣኙ  ብርሃኑ ደገፋ (ዶ/ር) ገልፀዋል፤፤ ቴክኒክና ሙያ በየወቅቱ የዘመነውን የቴክኖሎጂ እና የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት አድርጎ በየጊዜው ስልጠናውን የሚያዘምን እንደመሆኑ አሰልጣኞችም ብቁ እና ተወዳዳሪ ስልጠና አጠናቃቂዎችን ለማፍራት እንዲችሉ ወቅታዊ  ስልጠናዎችን  የሚያገኙበት ዕድሎችን እንደሚመቻችም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፤፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

የ EASTRIP ፕሮጀክት የሁለተኛ ሩብ አመት የስራ አፈጻጸም   ከስራና ክህሎት ሚንስቴር እና ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ በተወውጣጣ የSupervision team ግምገማ  በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተከናወነ፡፡ የ EASTRIP ፕሮጀክት የሁለተኛ ዙር የስራ አፈጻጸም ግምገማ ሂደቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን  ሲሆኑ በንግግራቸውም    እንኳን ወደ ትንሿ ኢትዮጵያ  የፍቅር ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ፡፡ በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የ EASTRIP ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ ማቺንግ ፈንድ ከመመደብ በዘለለ ለፕሮጀክቱ መሳካት እንቅፋት የሆነውን የበጀት ልዩነቶችን በመጋራት ያሳየው ተነሳሽነት ለሌሎች ከተሞች አርአያ የሆነ ተግባር ፈጽመዋል ይህም ፕሮጀክቱ  ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ዲኑ አያይዘውም ኮሌጁ ስራዎችን ለማሳለጥ እንዲሁም የተቀላጠፈ አሰራሮችን ለማምጣት በማቀድ የተለያዩ ICTን መሰረት ያደረጉ አሰራሮችን በመዘርጋት እንዲሁም  ጥናቶችን በማጥናት ፕሮጀክቱ ቀጣይነት እንዲኖረው በትጋት እንደሚሰራ ለ Supervision team ገልጸዋል፡፡ የግምገማ ሂደቱን ለማከናወን የመጣውን ልኡክ ቡድኑን የመሩት አቶ  መለሰ  እንዳሉት  አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አርአያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ወቅት በከተማ አስተዳደሩና በኮሌጁ ማኔጅመንት የሚወሰዱት የመፍትሄ እርምጃዎች ለሌሎች ኮሌጆች እንደ መልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡ድሬዳዋን የምስራቅ አፍሪካ ማዕከል ለማድረግ የሄዳችሁበት ርቀት እና ሰልጣኞችን ከሶማሊ ላንድ ተቀብላችሁ እያሰለጠናችሁ መሆኑን እንዲሁም ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያላችሁ ቅርበት በጣም የሚበረታታና ለሌሎች ኮሌጆችም እንደ አርአያ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ለተደረገላቸው የሞቀ አቀባበል እንዲሁም ስለተደረገላቸው ገለጻ የኮሌጁን ማኔጅመንት እንዲሁም የኮሌጁን የEASTRIP ፕሮጀክት ሰራተኞች ከልብ አመስግነዋል፡፡ በግምገማ ሂደቱ ላይ ስለኮሌጁ እንዲሁም ስለ EASTRIP ፕሮጀክት  M&E specialist በሆኑት አቶ መሳይ ጥላሁን እንዲሁም Industry Liaison ከፍተኛ ባለሞያ በሆኑት አቶ መሃመድ አወልጠሃ በኩል በቂ ገለጻ የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም  በገለጻው ላይ የተለያዩ ውይይቶች የተደረገ ሲሆን በተነሱት ሃሳቦች ላይና አስተያየቶች ላይ የኮሌጁ ዲን እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላቶች ምልሽ ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 17/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ