es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 077
Suscriptores
+524 horas
+107 días
+530 días
Archivo de publicaciones
ለገቢራ - ድሬዳዋ!! በዛሬው እለት ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር በተገኙበት በለገቢራ ገጠር ቀበሌ የደረሰ የማሽላ ማሳ ሰብሎች መሰብሰብ እና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተመረቱ 26 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን ለአካባቢው ማህበረሰብ አስረክበናል። አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚሰጠው የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ዝርዝር። ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ! ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ ጥቅምት 16፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/

ድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በራስ አቅም ያስጠናው የምሩቃን እና የስራ ገበያና ፍላጎት የጥናት ውጤት ሪፖርት የቀረበበት መድረክ ተካሄደ፡፡ ይህ የዳሰሳ ጥናት እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር ያለብንን ክፍተት የለየና በቀጣይ በምን የስልጠና መስኮች ላይ ትኩረት በማድረግ መስጠት እንደሚኖርብን ያመላከተ የዳሰሳ ጥናት ነው ያሉት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ ኃላፊዋ በንግግራቸው ወቅት ወጣቶችን አሰልጥኖ ማስመረቅ ብቻ ሳይሆን በሰለጠኑበት ሙያ ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉ ሰልጣኞችን ወደ ገበያው ማስገባትና ክትትል ማድረግ እንዲሁም የድሬዳዋና የአካባቢውን ጸጋ ተጠቅመው ራሳቸውንና አካባቢያቸውን መለወጥ የሚችሉ ሰልጣኞችን ማፍራት ላይ ትኩረት አድርገው ኮሌጆች መንቀሳቀስ አለባቸው ያሉ ሲሆን ፡፡ ድሬዳዋ ከተማችን ነጻ የንግድ ቀጠና እንደመሆኗ መጠን ለ ነጻ የንግድ ቀጠናው ተፈላጊ የሆኑ ባለሙያዎችን ከማፍራት አንጻር ኮሌጆች በትኩረት መስራት ይኖርባቸዋል ። በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስራዎችን እየሰራበት ያለው መንገድ የሚበረታታና ለሌሎች አቻ ኮሌጆች እንደ ተሞክሮ የሚቀርብ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል ፡፡ በተጨማሪም በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ዲን የሆኑት አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት ይህ የዳሰሳ ጥናት በተከታታይ ሁለት አመታት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገበያው ከሚፈልገው የሰው ሀይል ፍላጎት አንጻር ያሉበትን ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገ እንደነበረና የጥናቱ ውጤትም ኮሌጁ ከተቋቋመበት አላማ አንጻር ሲታይ አላማውን ለማሳካት ምን አይነት ስራዎችን በቀጣይ ምን መስራት እንዳለበት ለኮሌጆች ፣ ለስራና ክህሎት ሚኒስቴር የጠቆመ የዳሰሳ ጥናት ነው ያሉ ሲሆን በቀጣይ በዳሳ ጥናቱ የተገኙ ግብአቶችን እቅድ ውስጥ በማካተት የሚሰራ ይሆናል ።በመጨረሻም ለዚህ ጥናት መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላቶች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ጥናቱን አስመልክቶ የEASTRIP ፕሮጀክት የM & E Specialist የሆኑት አቶ መሳይ ጥላሁን እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በICOS Consulting PLC እንዲሁም በኮሌጁ አቅም ተመሳሳይ ጥናት መደረጉን አስታውሰው አሁን የተጠናው ጥናት በራስ አቅም ማስጠናት መቻላችን በወጪ ረገድ ዋጋ ቆጣቢ የሆነና ከመረጃ ጥራት ጋር በትኩረት መስራት እንድንችል ያደረገ ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጃችን ከኢንዱስትሪው ጋር የማስተሳሰር ስራ እንዲሁም ቀሪ ጥናቶችን ደግሞ ሁሉን አሳታፊ አድርገን የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የሥራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክትር ፤የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊዎችና ተወካዮች፤ የሁለቱም ኮሌጆች ዲኖችና ም/ዲኖች እንዲሁም የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት፤የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ አባላቶች እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ስለ_ቢሯችን_ምን_ማወቅ_ይፈልጋሉ? የድሬዳዋ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይን የሚመለከት ተጠሪነቱ ለቢሮው የሆነ ቦርድ ይገኛል ይ
#ስለ_ቢሯችን_ምን_ማወቅ_ይፈልጋሉ? የድሬዳዋ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይን የሚመለከት ተጠሪነቱ ለቢሮው የሆነ ቦርድ ይገኛል ይህም ቦርድ የወል የስራ ክርክሮችን የሚያይ፣ የመወሰን እና የማስማማት ስልጣን የተሰጠው ሲሆን ከመንግስት እና ከአሠሪና ሠራተኛ ማህበር ውክልና ያላቸውን አባላት ይዟል፡፡ በዚህም ይህ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ የአደረጃጀትን እና የወል የሥራ ክርክሮች ለመፍታት በቢሮው የሚከናወነውን የፍትህ ማስፈን ተግባር የሚመራበት ወጥ የሆነ ቀልጣፋና ውጤታማ  የአሠራር ሥነ-ስርዓት በመዘርጋት የቢሮውን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ ይሰራል፡፡ ቦርዱ ምን ይሰራል?   በዋናነት የወል የሥራ ክርክሮችን  በተቀላጠፈ ሁኔታ ይቀበላል፤   ችሎት ያካሂዳል፤

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠና አጠናቃቂ ለሆኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኢንተርፕሩንርሺፕ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል:: ስልጠናው በዋናነት ሰልጣኝ ተማሪዎች መደበኛ ስልጠናቸውን አጠናቀው ሲወጡ ስራ ፈጣሪነትን ተላብሰው እንዲወጡና በሚፈጥሩትም ስራ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም ባሻገር ለሀገር ኢኮኖሚ እንዲተርፉ የሚያስችላቸው የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል:: የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናውን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI)ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን ስልጠናው በቀጣዮቹ ቀናትም ቀጥሎ የሚሰጥ ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ህዳር 14/2017 ዓ.ም

በአረብ አገራት ተቀጥረው ለመሥራት የሠለጠኑ ሥራ ፈላጊዎች የቅድመ ጉዞ ስልጠና ተሰጣቸው!! በኢትዮጵያ እና በስድስት አረብ አገራት መንግሥታት ሥምምነት መሰረት ወደ አገራቱ ከሚሔዱ ሥራ ፈላጊ ዜጎች መካከል በኮሌጆች ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ለነበሩ ሰልጣኞች ጉዞ ከማድረጋቸው በፊት አስፈላጊ  የሆነ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ የሚያስቸላቸው ገለጻ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሠሪና ሠራተኛ ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባሙያዎች ተደርጎላቸዋል። በዚህም ከአገር ውጭ ለስራ ጉዞ ሲያደርጉ ቅድመ ጉዞ መደረግ እና ማሟላት የሚገባቸውን እንዲሁም በጉዞ ላይ እና ለስራ በሚሄዱበት አገር ሊገጥማቸው የሚችሉ ጉዳዮችን በተብራራ መልኩ ማግኘታቸው በቂ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ሰልጣኞች ተናግረዋል። በተያያዘ ባሳለፍነው አመት እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር ስልጠናቸውን አጠናቀው በህጋዊ መንገድ ከሁለት መቶ ሀምሳ በላይ ስራ ፈላጊዎች ወደ አረብ አገር የተላኩ ሲሆን በያዝነው አመት በመጀመሪያው ሩብ አመት ብቻ ወደ ስልሳ የሚጠጉ ስራ ፈላጊዎችን መላክ ተችሏል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለጥንቃቄ! ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማ
ለጥንቃቄ! ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማሰራጫት ህብረተሰቡን ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየዳረጉ በመሆኑ መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡  በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የሌለ መሆኑን እየገለጽን ዜጎቻችን በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣ እንግልትና ሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡  የሁለትየሽ ስምምነት በተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት የሥራ ዕድል ማግኘት ከፈለጉ የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ (lmis.gov.et) በመጠቀም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡ 

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተከናወነው የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ። በመድረኩ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀም በፕሮጀክቱ ተወካይ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ስልጠና ላይ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ጭምር በሪፖርቱ ተመላክቷል። በዚህም በመጀመርያ ዙር የፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በቀጣይ ለሚሰጠው ስልጠና እንቅፋት እንዳይሆኑ ከወዲሁ ለማስተካከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመምከር የመፍትሄ አቅጣጫዋችን ማስቀመጥ ተችሏል። መድረኩ ቀጥሎም እንደ አገር አዲስ የሆነው የሶላር ቴክኒሺያን እና ኤክስፐርት የስራ መዘርዝር 'JOB BOX ' ሰነድ ከሲቪል ሰርቪስ በመጣ ባለሙያ የቀረበ ሲሆን ሰነዱንም የሚመለከታቸው ተቋማት ሁኔታውን በደንብ ገምግመው ግብረመልስ ተሰቶበታል። በቀጣይም የተሰራው የJOB BOX ሰነድ እንዲፀድቅና የሶላር ፒቪ ተጠቃሚ ተቋማት የሶላር ኤክስፐርት/ ቴክኒሺያን በመቅጠር የሶላር ዘርፍ ላይ ያለውን ከፍተኛ ክፍተት መሙላት እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን ይህም በADRA ፕሮጀክት የሰለጠኑ ባለሞያዎችም ከሚከፈትላቸው የስራ እድልም ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደላድል ይፈጥራልም ተብሏል። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 13/2017 ዓ.ም

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በአገልግሎት ዘርፍ ላይ ከተሰማሩ ትምህርት ቤቶችና ሆቴሎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በስራ ሁኔታ እና በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና ሰጠ። በዚህም ስልጠና በዋናነት መሰረታዊ የሥራ ሁኔታ በአሰሪና ሰራተኛው መሃል ያሉ ጠቅላላ ግንኙነቶች የሰራተኛውን የቅጥር ሁኔታ፣ የስራ ሰዓት እና የሰራተኛውን ጥቅማጥቅም የሚመለከቱ ጉዳዮች በአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ 1156/2011 ላይ በተደነገገው መሠረት ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ህግና ስርዓታቸው ተከብሮ  የአሰሪና ሰራተኛው ግንኙነት ጤናማ የሚሆንበትና ሰላማዊ የስራ ከባቢ እንዲኖረው ግንዛቤ የሚፈጥርላቸው ሆኗል፡፡ በተጨማሪ የሥራ ቦታዎች ምቹ፣ ጤናማና ከአደጋ የተጠበቁ እንዲሆኑ በማስቻል  ምርታማነትን ከማረጋገጥ አኳያ ከሙያ ደህንነት እና ጤንነት አጠባበቅ አንፃር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በዚህም ለግንዛቤ ያክል የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ በተመለከተው መሰረት የሙያ ደህንነትና ጤንነትን በተመለከተ አሠሪዎች፡- 🔑 ሠራተኞች የሚሰሩት ሥራ ሊያስከትልባቸው ስለሚችለው አደጋ እንዲሁም በጤንነት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለማስወገድ ስለሚያስፈልገው ጥንቃቄ ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ፣ 🔑 የአደጋ ተከላካይ ሠራተኛ ይመድባሉ፤ የሙያ ደኅንነትና ጤንነት ኮሚቴ ያቋቁማሉ፣ 🔑 ለሠራተኞች የአደጋ መከላከያ መሣሪያ ልብስና ሌሎች ቁሳቁሶችን ያቀርባሉ፤ ስለአጠቃቀሙም መመሪያ ይሰጣሉ፣ 🔑 በሥራ ምክንያት የሚመጡ በሽታዎችንና አደጋዎችን ይመዘግባሉ፤ ለሥራ ሁኔታዎች መቆጣጠሪያ አገልግሎት ያሳውቃሉ፣ 🔑 እንደሥራው ጠባይ አዲስ ለሚቀጠሩ ሠራተኞች በራሳቸው ወጪ የጤና ምርመራ እንዲካሄድላቸው ያደርጋሉ፣ 🔑 በአደገኛ ሥራ ላይ የሚሰሩ ሠራተኞች እንደአስፈላጊነቱ የጤና ምርመራ እንዲያገኙ ያደርጋሉ፣ 🔑 ሆኖም ይህ ምርመራ ኢትዮጵያ ያፀደቀችው የዓለም አቀፍ ስምምነት ካላስገደደ በስተቀር የኤች.አይ.ቪ/ ኤድስ ምርመራን አይጨምርም፤ 🔑 የድርጅቱ የሥራ ቦታና ግቢ በሠራተኞች ደኅንነትና ጤንነት ላይ አደጋ የማያስከትል መሆኑን ያረጋግጣሉ፣ 🔑 በድርጅቱ ልዩ ልዩ የሥራ ሂደት በሚገኙ ፊዚካላዊ፣ ኬሚካላዊ፣ ባዮሎጂካዊ፣ ኢርጎኖሚካዊና ሥነ ልቦናዊ ምንጮችና ምክንያቶች ሳቢያ በሠራተኞች ደኅንነትና ጤንነት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ተገቢውን ጥንቃቄ የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡ በመሆኑም የሠራተኞችን የሙያ ደህንነትና ጤንነት በማረጋገጥ ጤናማ አምራች ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት በቢሮው የአሠሪና ሠራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም ይህ ስልጠና በብዙ መልኩ አሠሪና ሠራተኛው አዋጁ ባስቀመጠው የሙያ ደህንነትና ጤንነት መብትና ግዴታቸውን ተረድተው የሚያከብሩበትንና የሚያስከብሩበትን ብሎም የጋራ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በመውሰዳቸው በቀጣይ ደህንነትና ጤንነቱ የተጠበቀ ሙያተኛና ምርታማ የሆኑ ተቋማትን መፍጠር ያስችላቸዋል ብለዋል ፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡ ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጅ ውስጥ የነበ
+5
የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡ ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጅ ውስጥ የነበራቸውን ትምህርታቸውና ስልጠና አጠናቀው ሲወጡ የግላቸውን ስራ ፈጥረው ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንና ብሎም አገራቸውን እንዲጠቅሙ ከመደበኛው ስልጠና በዘለለ የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና መስጠት አስፈላጊ ነው፡፡ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎች ከቅጥር ይልቅ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ማስቻል ዋና አላማቸው ስለሆነ ሁሉም አካላት ለዚህ ስራ ተረባርቦ መስራት እንደሚገባ በስልጠና ወቅት ተገልጿል፡፡ በዛሬው እለት እየተሰጠ የሚገኘው የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) እና በኮሌጁ የተዘጋጀ ነው። የስልጠናውም ለ4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ እንደሆነ በስልጠናው ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

TVT Harmonized ሰነድ ላይ ትኩረት ያደረገ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገኙ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎችና ለስልጠና አስተባባሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ተጀመረ፡፡
+2
TVT Harmonized ሰነድ ላይ ትኩረት ያደረገ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገኙ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎችና ለስልጠና አስተባባሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ተጀመረ፡፡ የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ትግበራውንም ወጥነት ባለው መልኩ በጥራት ለመፈጸም ቅንጅታዊ ስራዎች የሚመሩበት ሰነድ በ2016 ዓ.ም መዘጋጀቱ የሚታወስ ሲሆን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች፣የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች የስልጠና አስተባባሪዎች እንዲሁም መምህራን በትምህርትና ስልጠናው ውስጥ ያላቸውን ድርሻ ላስገንዘብ አላማውን ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንደሆነም በስልጠናው ወቅት ማወቅ ተችሏል፡፡ የTVT Harmonized ሰነድ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ስልጠና በቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬቶች በቅንጅት ተካሂዷል፡፡ስልጠናውም እስከ ህዳር 13/2017 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቢሮ አዘጋጅነት ለጥቃቅንና አነስተኛ፣ መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስለሚሰጠው የኢንዱስትሪ
+5
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቢሮ አዘጋጅነት ለጥቃቅንና አነስተኛ፣ መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስለሚሰጠው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ድጋፍ ላይ ያተኮረ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተከናወነ፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙትና ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት የ2016 ዓ.ም አፈፃፀምን መነሻ በማድረግና የተለዩ ችግሮችን በመለየት በ2017 በጀት ዓመት የተሸለ አፈጻጸም እንዲኖረን ባለድርሻ አካላት ተባብረን በጋራ ልንሰራ ይገባናል ብለዋል፡፡ አያይዘውም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ በኮሌጆች ብቻ ተፈጻሚ የሚሆን ሳይሆን ባለድርሻ አካላት በጋራ በመሆን በሚከውኑት ተግባር ነው ለውጥ የሚመጣው ስለዚህም በዘንድሮ አመት በተሰራ የኢንተርፕራይዞች የፍላጎት ዳሰሳና ጥናት ላይ መሰረት በማድረግ ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ኢንተርፕራይዞችም ከተለመደው አሰራር በመውጣት የሚደረግላቸውን ድጋፍ በመቀበል ውጤት ለማስመዝገብ ተግተው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም የ2016 ዓ.ም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አፈፃፀም ላይ፣ የ2017 ዓ.ም በተሰራ የዳሰሳ ጥናት እና በቀጣይ ስለሚደረግላቸው ድጋፍ እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የሙያ ብቃት ምዘናን በተመለከተ አጠቃላይ ገለጻ በአቶ ዘየደ ተክሌ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይ ባለድርሻ አካላት ውይይት በማድረግ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ትግበራውንም በጥራት ለመፈጸም ቅንጅታዊ ስራዎች የሚመሩበት ሰነድ መዘጋጀቱ ተገለጸ፤ ቴ/ሙ/ት/ስ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል መንዳት፣ ስራ ፈጣሪነትን እና ፈጠራን ማጎልበት፣ አለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን በማጎልበት እና ማህበረሰባዊ ተሳትፎን በማስተዋወቅ ላይ ትልቅ ዋጋ አለው፤ ዘርፉ እንደ ስትራቴጂ ቀጣይ ዕድገቱን እና ልማቱን ለማረጋገጥ በልህቀት፣ በአካታችነት እና በትብብር መርሆዎች በመመራት በጋራ መስራትን ትኩረት ይሰጣል። በዚህም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ሪፎርም ካደረገባቸው የሰነድ ስራዎች ውስጥ የዘርፉ የተቀናጀ አሰራር ለማምጣት የሚያስችል ሰነድ ላይ በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት በኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬቶች በቅንጅት ተካሄደ፡፡ በመሆኑም TVT Harmonized ሰነድ ላይ እንዴት ወደ ስራ መግባት እንደሚቻል ከዲፓርትመንት ተጠሪዎች እና ከስራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ግንዛቤ በመፍጠር ወደ ስራ የሚገባባቸው ዋናዋና ጉዳዮች ላይ በመወያየት የሁለት ወራት ዕቅድ ማዘጋጀት ተችሏል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ትግበራውንም በጥራት ለመፈጸም ቅንጅታዊ ስራዎች የሚመሩበት ሰነድ መዘጋጀቱ ተገለጸ፤ ቴ/ሙ/ት/ስ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል መንዳት፣ ስራ ፈጣሪነትን እና ፈጠራን ማጎልበት፣ አለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን በማጎልበት እና ማህበረሰባዊ ተሳትፎን በማስተዋወቅ ላይ ትልቅ ዋጋ አለው፤ ዘርፉ እንደ ስትራቴጂ ቀጣይ ዕድገቱን እና ልማቱን ለማረጋገጥ በልህቀት፣ በአካታችነት እና በትብብር መርሆዎች በመመራት በጋራ መስራትን ትኩረት ይሰጣል። በዚህም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ሪፎርም ካደረገባቸው የሰነድ ስራዎች ውስጥ የዘርፉ የተቀናጀ አሰራር ለማምጣት የሚያስችል ሰነድ ላይ ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት በኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና የሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬቶች በቅንጅት ተካሄደ፡፡ በመሆኑም TVT Harmonized ሰነድ ላይ እንዴት ወደ ስራ መግባት እንደሚቻል ከዲፓርትመንት ተጠሪዎች እና ከስራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ግንዛቤ በመፍጠር ወደ ስራ የሚገባባቸው ዋናዋና ጉዳዮች ላይ በመወያየት የሁለት ወራት ዕቅድ ማዘጋጀት ተችሏል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ