1 089
Suscriptores
+324 horas
+257 días
+1730 días
Archivo de publicaciones
ማስታወቂያ
ለሚመለከተው ሁሉ
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ከሃገር ውስጥ እና በሃገር ውጪ ያሉ የስራ ዕድሎችን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ባለው የሪፎርም ስራና በተዘረጋው ቴክኖሎጂ በአምስት ወራት(ወ.ሴ) ከ146,291 በላይ ዜጎች በውጭ ሃገር የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል።
ሚንስቴር መስሪያቤቱ በውጭ ሃገር የሰራተኛ ስምሪት የዜጎቻችን ደህንነት እና ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሁም ብልሹ አሰራርን የሚከላከል ቴክኖሎጂ በውስጥ አቅም አልምቶ እጅግ ፈጣን የሆነ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በመሆኑም ሚንስቴር መስሪያቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በሚያከናውናቸው የሪፎርም ተግባራት እና በዘርፉ በሚሰጠው ፈጣን አገልግሎት እንዲሁም የስምሪት መደረሻዎችን ለማስፋት ከተለያዩ ሃገራት ጋር እየገባናቸው ያሉ አዳዲስ ስምምነቶች የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ፍላጎት ያላቸው በመሆኑ በተዘረዘረው የሞያ መስክ ተመዝግበው ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆናቹ ዜጎች በኢትዮጲያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት https://www.lmis.gov.et ድህረ-ገጽ ላይ ገብታቹ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
1. Driver - ሹፌር
2. Cleaner - የጽዳት ባለሞያ
3. Chef - በሼፍ
4. Laborer - በጉልበት ሰራተኝነት
5. Security Guard/ Security Officer - የጥበቃ ባለሞያ
6. Technician - ቴክኒሺያን
7. Carpenter - የእንጨት ባለሞያ
8. Store Keeper - የሱቅ ጠባቂ
ተመዝጋቢዎች ድህረ-ገጹ ላይ በሚደረገው ምዝገባ መረጃዎቻችሁን በትክክል የማስገባት ሃላፊነት ያለባችሁ ሲሆን መረጃዎቻችሁን አስገብታችሁ ስትጨርሱ ሲስተሙ በሚሰጠው የባዮሜትሪክስ ቁጥር አቅራቢያችሁ በሚገኙ አንድ ማዕከላት በመሄድ የባዮሜትሪክስ ምዝገባ በማደረግ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ እናስታውቃለን።
ማሳሰቢያ:
ለመመዝገብ የፓስፖርት ባለቤት መሆን የማያስፈልግ ሲሆን ፤ የባዮሜትሪክስ ምዝገባ የሚያከናውኑ አንድ ማዕከላትን ዝርዝር https://lmis.gov.et/ossc-lists ከዚህ ላይ ማግኘት ይቻላል።
የሥራዎ ባለቤት እርስዎ ኖዎት !
ማሳሰቢያ
ከሃገር ለስራ ለምትወጡ ዜጎች !!
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር በሚፈጠሩ የስራ ዕድሎች ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ሰፊ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በተለይም የውጭ ሃገር የስራ ስምሪት የዜጎቻችን ደህንነት እና ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሁም ብልሹ አሰራርን የሚከላከል ቴክኖሎጂ በውስጥ አቅም አልምቶ በአምስት ወራት ከ146,000 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ መካከለኛው ምስራቅ፣ አውሮፓና አሜሪካ እንዲሁም ወደ ኤሲያ በማሰማራት እጅግ ፈጣን የሆነ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በዚህ ለምቶ ተግባራዊ በተደረገው ቴክኖሎጂ አስፈላጊውን ሰነድ ላሟሉ ዜጎች ቀደም ብሎ ለፕሮሰስ ይወሰድ የነበረውን ከ4 እስከ 6 ወራት በ10 ደቂቃ አገልግሎቱን መስጠት የሚያስችል ሲሆን ዜጎችም በሄድቡት ሃገር ደህንነታቸው ተጠብቆ፣ መብታቸው እና ጥቅማቸው ተከብሮ መስራት እንዲችሉ በየሃገራቱ የሚገኙ ኢምባሲዎቻችና ቆንጽላዎች የዜጎችን ደህንነት ማስጠብቅ እንዲችሉ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ በውጭ ሃገር ስራና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች እንዲሁም በግል ጥረት ስራ አግኝታችሁ ወደ የትኛውም የአለም ክፍል የምትሄዱ ዜጎች በቦሌ አየር መንገድ የኢምግሬሽን አገልግሎት በማግኘት ከሃገር መውጣት እንድትችሉ በቅድሚያ ከሥራና ክህሎት ሚንስቴር ተገቢውን ሂደት ማለፍ ያለባችሁ መሆኑን እናሳስባለን።
የሥራዎ ባለቤት እርስዎ ኖዎት !
የዝግጅት ምዕራፍ ሥራዎችን የሚመለከት የመስክ ምልከታ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና በስሩ በሚገኙ ተቋማት ላይ በማካሄድ የሚገኘው የሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ቀን ቀጥሎ የተከናወኑ የተለያዩ ስራዎችን ምልከታ አደረገ።
በዚህም የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችን አንድ ማዕከላት ድረስ በመውረድና የኢንተርፕራይዝ ልማት ጋር በተያያዘ በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፉም የኢንደስትሪውን ሰላምና ደህንነት ከማጠበቅ አንጻር ኢንደስትሪዎች ላይ ተዘዋውረው ተጨባጭ ሁኔታውን መመልከት ችለዋል፤
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በተለይም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከኢንዱስትሪዎች ጋር በፈጠረው የሁለትዮሽ ግንኙነት የተሰሩ ምርታማነታቸው የተረጋገጠና import substitute የሆኑ የተለያዩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች ያሉበትን ደረጃ በተግባር ተመልክቷል።
Fly finger የብስኩት ማሸጊያ ማሽን መለዋወጫ (spare part) እና ፖምፕ ካፕሊንግ ለድሬዳዋ ምግብ ኮምፕሌክስ፤ Stainless steel pusher የሳሙና ማሸጊያ ማሽን መለዋወጫ (spare part) ለኮኔል ሳሙና ፋብሪካ እንዲሁም Bearing roller holder የማዳበሪያ ማምረቻ ማሽን መለዋወጫ በድሬዳዋ ኢንደስትሪ ፓርክ (free tread zone) ለሚገኘው ለሀን ፕላስ ፋብሪካ የተሰሩና ምልከታ የተደረገባቸው ከብዙ በጥቂቱ ናቸው፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በ2016 ዓ.ም ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ስልጠና ተሰጠ።
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ ለመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችና ለግል ኮሌጅ ተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎች የስራ ፈጣራ ባህል ግንባታ ስልጠና እንዲሁም የማይንድ ሴት ስልጠና በመውሰድ ከተቀጣሪነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲያዘነብሉ የማነቃቂያ ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡
በዳይሬክቶሬቱ የስራ ፈጣሪነት ባለሞያ የሆኑት ወ/ሮ ውልታ ትልቅሰው እንደተናገሩት ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ስልጠና አጠናቀው ሲወጡ በግልም ሆነ ተደራጅተው የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ ትኩረት የተሰጠው እና የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለኢንደስትሪ ውስጥ ባለሙያዎች የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠን ስነ ዘዴ/ Industry Trainers Methodology / ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፤
በዚህም ስልጠና ውጤትን መሰረት ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና በንድፈ ሃሳብ እና በተግባር የተደገፈ እንደመሆኑ ስልጠናው በቴ/ሙ/ት/ስ ተቋማት ውስጥ እና በኢንደስትሪው ውስጥ በሁለትዮሽ/ በትብብር ይሰጣል፤ ለዚህም በኢንደስትሪው ውስጥ ይህንን ስልጠና የሚሰጥ የኢንደስትሪ ባለሙያ ለማፍራት ታሳቢ ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ላይ ግንዛቤ በመስጠት፣ በ OBT Delivery System፣ Occupational Standard፣ Session Plan፣ Delivery Methods፣ TTLM፤ Plan and Conduct Assessment ሞጁልን በመሰልጠን ላይ ይገኛሉ፤
በመሆኑም ቢሮው ከዚህ ቀደም ከዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር ባደረገው የጋራ ዕቅድ/MoU/ ስምምነት መሰረት ከ2016 ጀምሮ ኮሌጆች ለትብብር ስልጠና መስጫነት የመረጡአቸው ዘርፍ መስሪያ ቤት እና ኢንደስትሪዎች ውስጥ የሚሰሩ ቴክኒካል ባለሙያዎችን በማካተት ስልጠናው ለ5 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቂያ በሚኖራቸው ምዘና መሰረት ብቁ የሆኑትን ሰርቲፋይ በማድረግ በኢንደስትሪ ውስጥ የትብብር ስልጠናን የሚሰጡ የኢንደስትሪ ውስጥ አሰልጣኞች ይሆናሉ፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም የተቀበላቸውን አዳዲስ ሰልጣኞች ለ5 ቀናት ስለ ቴክኒክና ሙያ ያላቸውን የግንዛቤ ለውጥ እንዲያመጡ ታስቦ ሲሰጥ የነበረው የህይወት ክህሎትና የማይንድ ሴት ስልጠናዎችን በዛሬው እለት አጠናቀቀ፡፡
በስልጠናው ሂደት ላይ መግለጫ የሰጡት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን እንደገለጹት ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ኮሌጃችን በኢትዮጵያ ከሚገኙ ኮሌጆች መካከል አንጋፋው ኮሌጅ ነው ስለዚህ በዚህ ኮሌጅ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች ለኢንዱስትሪው የሚጠቅሙ በመካከለኛ ደረጀጃ የሰለጠኑ የሰው ኃይን ከማፍራት በዘለለ የራሳቸውን ስራ ፈጥረው ለራሳቸወው ብሎም ለሃገር የሚጠቅሙ ባለሞያዎችን እያፈራ ይገኛል ያሉ ሲሆን አያይዘውም በኮሌጁ ውስጥ የሚኖራቸው ቆይታ የተሳካና የሚፈልጉትን እውቀትና ክህሎትን እንደሚያገኙ እተማመናለሁ ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግራቸውም በዚህ የህይወት ክህሎት ስልጠና አዲስ ወደ ኮሌጁ የተቀላቀሉ ሰልጣኞቻችን ከዚህ በፊት ስለ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ያላቸውን ግንዛቤ የለወጠና በተለይም ሃርድ ኮርስ ላይ ያለውን የተማሪ እጥረትን ለመቅረፍ እንደ ጥሩ አጋጣሚ የሚጠቅም ሲሆን በዚህም ብዙ ሰልጣኞች ከሶፍት ኮርስ ወደ ሃርድ ኮርስ የትምህርት አይነቶች እንዲያዘነብሉ እድል አመቻችቷል ብለዋል፡፡ አያይዘውም በዚህ ስልጠና ላይ ለተሳተፉ መምህራን ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ለተማሪዎችም መልካም የስልጠና ዘመን እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡
በተያያዘ ዘገባም የህይወት ክህሎት ስልጠና ለሰለጠኑ ሰልጣኞች ኢንዱስትሪው ምን ያክል የሰው ሃይል እንደሚፈልግ የሚያስገነዝብ የትምህርታዊ ጉብኝቶችን ያከናወነ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላም ሰልጣኖች በኮሌጁ ውስጥ የሚኖራቸው ቆይታ ከስልጠና በዘለለ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ተቀጥረው እንዲሁም የራሳቸውን ስራ ፈጥረው መስራት የሚችሉበትን እውቀት እንዳገኙ ተናግረዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 05/04/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን የዝግጅት ምዕራፍ ሥራዎችን የሚመለከት የመስክ ምልከታ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና በስሩ በሚገኙ ተቋማት ላይ ማካሄድ ጀመረ።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በዛሬው ዕለት በአስተዳደሩ ቢሮ በመገኘት ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ማድረግ የጀመረ ሲሆን የሱፐርቪዥኑ ዋንኛ አላማም የፌደራል፣ የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ተቋማዊ የዕቅድ አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ በተግባር ለማረጋገጥና ችግሮቹን በመለየት የማረም እና የማስተካከል ስራ ለመስራት እንዲሁም አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እንደሆነም ነው የተገለፀው።
በዚህም የሱፐርቪዥን ቡድኑ ባዘጋጀው ቼክሊስት መሰረት በዛሬው ዕለት ከድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የማኔጅመንት አባላት ጋር በመሆን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን ከዚህም ባለፈ ቡድኑ ቢሮው ከአገልግሎት አሰጣጥ እና ከሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች አንፃር ያለበትን ደረጃ በተግባር ተመልክቷል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ ከዛሬ ጀምሮ በቀጣይ ቀናት በቢሮው ስር በሚገኙ ተቋማት በአካል በመገኘት ድጋፋዊ ሱፐርቪዥኑን የሚያደርግ ሲሆን በመጨረሻም ቡድኑ በቆይታው በተግባር የተመለከታቸውን የሥራ አፈፃፀሞች መሰረት በማድረግ ግብረመልስ ይሰጣል ተብሎም ይጠበቃል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 3/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች እና የግል ኮሌጆች ላይ ኢንስፔክሽን በማካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ።
በዚህም ኢንስፔክሽን ኮሌጆች የሚሰጡትን ትምህርትና ስልጠና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተሰጠ ስለመሆኑ በማረጋገጥ የሚታዩ ችግሮችን በአጭር ጊዜ በማስተካከል እርማት እንዲወስዱ ታሳቢ ያደረገ ነው።
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ስለ ኢንስፔክሽኑ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ጥራት ለማምጣት ይህ ለአገራችንና ለከተማችን እድገት አስፈላጊ በመሆኑ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላትና ባለድርሻ አከላት ጋር በጋራና በቅንጅት ሴክተሮችን ባሳተፈ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 1/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሀግብር በኮሌጁ አዳራሽ አከናወነ፡፡
በመርሀግብሩ ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ም/ዲን የሆኑት አቶ ሰልሀዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት በቅድሚያ በምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል የሆነውን ኮሌጃችንን ስለመረጣቸሁ በኮሌጁ ማህበረሰብ ስም አመሰግናለሁ ያሉ ሲሆን አያይዘውም ቴክኒክና ሙያ ማለት የወደቁ ተማሪዎች መሰብሰቢያ ሳይሆን ይልቁንም የእውቀት፣የክህሎትና የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት የሚፈልጉ ወጣቶች የሚማሩበትና በእጃቸው ሰርተው በላባቸው ሀገራቸውን መቀየር የሚፈልጉ ወጣቶች የሚሰባሰቡበት ትልቅ የትምህርትና ስልጠና ማእከል ነው ብለዋል፡፡ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዘመኑን የሚመጥን የትምህርትና ስልጠና ዘዴዎችን እየተጠቀመ ስልጠናዎችን እንደሚሰጥ ይታወቃል ስለዚህ በኮሌጁ ውስጥ በምትቆዩበት ወቅት ስራ ፈጣሪ ብሎም ኢንዱስትሪዎችን አንቀሳቃሽ እንድትሆኑ አድርገን ነው የምናሰለጥነው ብለዋል፡፡አያይዘውም ድሬዳዋ ከተማች የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ነጻ የንግድ ቀጣና እንደመሆኗ መጠን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሰለጠኑ ወጣቶችን በብዛት ይፈለጋሉ ስለዚህ በኢንዱስትሪዎች ተቀጥሮ ለመስራት እንዲሁም የራስን ስራ ፈጥሮ ለመንቀሳቀስ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ መሰልጠን ያስፈልጋል ብለዋል በማስቀጠልም በኮሌጁ ውስጥ የሚኖራችሁ ቆይታ እውቀት፣ክህሎት እንዲሁም መልካም አስተሳሰብ ያላችሁ ወጣቶች የምትሆኑበት እንዲሁም በምታገኙት እውቀትና ክህሎት ደግሞ ከተማችሁን ብሎም ሀገራችሁን የምትጠቅሙ ዜጎች እንደምትሆኑ እተማመናለሁ ያሉ ሲሆን የስልጠና ቆይታችሁም መልካም እንዲሆን መልካም መኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በመርሀግብሩ ላይ በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ ሁሉም የትምህርት ክፍሎች ስለ ትምህርት ክፍሎቻቸው ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በቀጣዩ ቀንም የህይወት ክህሎትና የማይንድ ሴት ስልጠና እንደሚሰጥ በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 29/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
