es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 067
Suscriptores
-224 horas
-67 días
+430 días
Archivo de publicaciones
100 ሺህ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ይፋ ሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር “ብቃት” የተሰኘ 100 ሺህ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴ
+3
100 ሺህ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ይፋ ሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር “ብቃት” የተሰኘ 100 ሺህ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ የወጣቶችን የሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር “ብቃት'” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራምን በ11 ከተሞች ሲተገብር ቆይቷል፡፡ አሁን ላይም ይህንን የሥራ ዕድል ወደ 27 ከተሞች በማስፋት 100 ሺህ ተጨማሪ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው ይፋ ያደረገው፡፡ ፕሮግራሙ በዓለም ባንክ 52 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ በሚቀጥሉት 2 ዓመታት የሚተገበር ሲሆን÷ ከ18 እስከ 29 የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴዔታ ሰለሞን ሶካን ጨምሮ የክልሎች የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ©️ኤፍ ኤም ሲ

በድሬዳዋ ባለፉት አመታት ለነዋሪዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር የተሰሩ ተግባራት ውጤታማ ናቸው  - ኢዜአ አማርኛ https://share.google/2jfdzOukM3qR6esJp

በአፍሪካ ደረጃ ለሚደረገው የካይዘን ውድድር የተመረጠው አንጋፋው የምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል የሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳ
+9
በአፍሪካ ደረጃ ለሚደረገው የካይዘን ውድድር የተመረጠው አንጋፋው የምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል የሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳብ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትና ወቅታዊ አፈፃፀም ላይ በዚህ አመት ባሳየው ምርጥ ተሞክሮ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 13 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ አንዱ በመሆን ለአፍሪካ የካይዘን ውድድር ተመርጧል፡፡ ከዚህ በፊት የሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድር አካል በሆነውና ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በተካሄደው ምዘና በኮሌጁ የስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ፤ ብክነትን ከመቀነስ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነትን ከማሻሻል አኳያ በተቀመጡ መመዘኛዎች የተከናወኑ ተግባራትን ለገምጋሚው ቡድን በበቂ ሁኔታ ያስረዳ በመሆኑና የሚሰራቸው ስራዎች ከራስ አልፎ ለሌሎችም ተቋማት ጭምር የሚተርፍ በመሆኑ ለዚህ በአፍሪካ ደረጃ እንዲወዳደሩ ከተመረጡ 13 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል አንዱ በመሆን በትናንትናው እለት ለአወዳዳሪው አካል የኮሌጁን አፈጻጸም በበይነ መረብ አቅርቧል፡፡ በዚህም መሰረት በኮሌጁ የካይዘን ትግበራ አጠቃላይ የአፈፃፀም እንዲሁም ከ8ቱ የውጤት አመላካች አኳያ የተገኙ ውጤቶችን በገለጻው ወቅት ለገምጋሚ ቡድኑ በበይነ መረብ ማስረዳት ተችሏል:: በዚህ አንጋፋ ኮሌጁ ያለው በትምህርትና ስልጠና፣በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለኢንተርፕራይዞች እና ኢንዱስትሪዎች የማሻገር ተሞክሮዎች ከራስ አልፎ ለሌሎችም የሚተርፍ እንደመሆኑ መጠን በኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም በጋራ እንጠቀም ሃገራችንንም ወደተሸለ ልማት እንውሰድ፡፡ "ዛሬን እናሻሽል፤ ብክነትን እንቀንስ፤ ጥራትና ፍጥነትን እንጨምር፤ ነገን እንገንባ"!! የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ በተከናወነው የተቀናጀ ርብርብ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል..የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት መደበኛ ጉባኤውን በዛሬው እለት አካሂዷል። በጉባኤውም ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያካሄዱት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር እንደገለጹት በአስተዳደሩ የስራ ዕድል በመፍጠር የዜጎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎች የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ድህነትን ለመቀነስ ፍትሀዊ እድገት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በአስተዳደሩ በባለፉት ዓመታት በስራ እድል ፈጠራ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን ፣በተለይም በበጀት ዓመቱ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ በተደረገው የተቀናጀ ርብርብ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውም በበኩላቸው ዘላቂና አስተማማኝ የስራ ዕድል በመፍጠር የዜጎች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት ቢሮው በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በበጀት ዓመቱም በግብርና፣ በኢንድስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆኑን አስታውቀዋል። በጉባኤውም የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ ማጠቃለያም ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ተሳታፊዎች ላነሷቸው ሀሳብ አስተያየት ምላሽ እና ማብራሪያ እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ሰጥተው የእለቱን ጉባኤውን አጠናቋል። ©️DGC ሰኔ 5/2018

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀምሯል #DGC ሰኔ 5/2018 ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በስራ እድል ፈጠራ በበጀት አመቱ የተሰሩ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ግምገማ ያደርጋል። በመድረኩም የየድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የካቢኔ አባላት፣ የምክር ቤቱ አባላት፣የዘርፉ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኘተዋል። *********** Yaa'iin Idilee Mana Marii Carraa Hojii Uumuu Biiroo Hojiifi Ogummaa Bulchinsa Dirree Dhawaa Gaggeeffamaati Jira. Waltajjii Kanarratti Kabajamoo Kantibaa Bulchinsa Dirree Dhawaa Obbo Kadiir Juhaar, dabalatee Miseensonni Kaabinee Bulchinsaa, Hoggantoonni Olaanoo Bulchinsaa, Gaggeessitoonni Aanaalee Bulchinsaafi daayreektoerrtonnifi ogeeyyiin Biiroo Carraa Hojiifi Ogmmaa,fi Dhaabbilee Leenjiifi Ogummaa Bulchinsa Dirree Dhawaarraa Argamaniiti jiran. Biiroon Dhimmoota Komunikeeshinii Bulchinsa Dirree Dhawaa Odeeffannoowwan jiran hordofuun kan isin biraan gahu ta'a. *********** #Warka Waxaa hada socda oo bilabamay kalfadhiga caadiga ah ee golaha shaqo abuurka ee 2018,oo soo aggasimay xafiska Shaqada iyo xirfadaha ee is Maamulka Diridhaba. Golaha ayaa dib u eegi doona warbixinta hirgalinta qorshayaasha la hirgaliyay sanad miisaaniyeedka ee loogu talagalay abuurista shaqada si loo hubiyo faa'iidada wadajirka ah ee muwaadiniinta. Duqa Magaalada Diridhaba , mudane Kkadir Juhar, xubnaha golaha kabineedka, hoggaaminta dagmooyinka qaybaha iyo marti sharaaf kale ayaa goob joog ka ahaa madashaa kalfadhigii

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር የትምህርትና ስልጠና ተደራሽነትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተገለጸ።   በአስተዳደሩ አራቱም የገጠር ወረዳዎች የቴክኒክና ሙያ (TVET) ተንቀሳቃሽ ስልጠና በአምስት ሙያዎች ማለትም በከብት፣ በበግ፣ በፍየል፣ በዶሮ እና በንብ እርባታ ማሰልጠኛ ሞጁሎችን  በኦሮምኛ ቋንቋ የተተረጎሙትን  በመከለስ ወደፊት ሞጁሎቹን  በፓይለት ፕሮግራም በመፈተሸ ማስተካከያ በማድረግ ለስልጠና እንዲውሉ የሚመቻች ይሆናል፡፡   በዚህም በአስተዳደሩ ገጠር ተደራሽ ያልሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ ሥራ ፈላጊ ወጣቶች እና የአርብቶ አደር ማህበረሰቦች በተደራሽነት ረገድ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን በመቅረፍ በተለይም የገጠር ወጣቶች በቀላሉ እንዲጠቀሙ ተጨማሪ የስልጠና ማዕከላት፣ የሞባይል ስልጠና ፕሮግራሞች እና የቅርንጫፍ ስልጠና  ማዕከላት እተመቻቹ ይገኛሉ ።   የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጀት አመቱ የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀሪፖርት ለኮሌጁ ቦርድ ቀርቦ ተገመገመ፡፡ የተቋሙ የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ኮሌጁ ባለፉት 9 ወራት ያከናወናቸውን ቁልፍ ተግባራት እንዲሁም የተመዘገቡ ውጤቶችን በማካተት ለቦርዱ ሪፖርት አቅርበው ገለፃ ያደረጉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊከናወኑ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ለቦርድ አባላቱ በዝርዝር አመላክተዋል፡: በመድረኩ የቀረበውን አፈፃፀም ሪፖርት መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ግብረ- መልሳቸውን የሰጡበት ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው የስራ እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል:: ቦርዱ በኮሌጁ በነበረው ቆይታ በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ አማካኝነት በተቋሙ የተሰሩ የዳታ ማዕከል(Data Center) ፣ የኔትወርክ መሰረተ ልማት ዝርጋታንና የተገኙ ውጤቶች ተዘዋውረው ምልከታ አድርገዋል:: በተጨማሪም የኮሌጁን አለም አቀፋዊ ግንኙነት በማጠናከሩ ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበት በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ የተሰራውን የተቋሙን ድህረ-ገፅ(Website) ለቦርድ አባላት ቀርቦ ምልከታን አግኝቷል:: በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርትና በተከናወኑ የለውጥ ስራዎች ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያን በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/share/19wDiZAD7x/?mibextid=wwXIfr በቴሌግራም -https://t.me/EIPC2001 በቲክቶክ -https://www.tiktok.com/@ethioitaly2001?_t=ZM-90MxIrBN8qe&_r=1 በዌብሳይት - https://ethioitalypolytechniccollege.com/

🌏✈️ የውጪ ሀገር የስራ ማስታወቂያ 🚀 በህጋዊ የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በተለያዩ ዘርፎች የሰው ኃይል ይፈለጋል። የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ውጪ ሀገር ለመስራት የሚፈልጉ አመልካቾች እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን። 🚧 የሞያ ዘርፎች፦ 🔹የጥበቃ ሰራተኛ 🔹ፅዳት ሰራተኛ 🔹አጠቃላይ ረዳት 🔹የሲቪል ግንባታ ረዳት 🔹የኮንስትራክሽን ዕለታዊ ሰራተኛ / ረዳት 🔹ኤሌክትሪሻን / የኤሌክትሪክ ባለሙያ 🔹ቧንቧ ሰራተኛ / የቧንቧ ባለሙያ 🔹የኤር ኮንዲሽነር ባለሙያ 🔹ብየዳ ሰራተኛ / የብየዳ ባለሙያ 🔹የእሳት አደጋ መከላከያ ባለሙያ 🔹ግንብ ሰራተኛ / የድንጋይና ጡብ ግንባታ ባለሙያ 🔹ቀለም ቀቢ 🔹ምርጋትና ልስን ሰራተኛ 🔹የጂፕሰም ባለሙያ 🔹የፎርምወርክ አናጺ / የማገር አናጺ 🔹የአሉሚኒየም ስራ ባለሙያ 🔹ላሚኔተር / የላሜራ ስራ ባለሙያ 🔹ማጠናቀቂያ ስራ ባለሙያ 🔹የብረት መዋቅር ሰራተኛ 🔹ስካፎልዲንግ ሰራተኛ 🔹ሪገር እና ምልክት ሰጪ 🔹የመጋዘን እቃ አሰናጅ 🔹የፋብሪካ ሰራተኛ 🔹የጭነት አውራጅና ጫኝ ሰራተኛ 🔹የሞተር/ሳይክል አሽከርካሪ 🔹የሲቪል ፎርማን / የሳይት ተቆጣጣሪ 🔹የሲቪል ረዳት ፎርማን / የቡድን መሪ ✅ ለመመዝገብ Labor ID ካሎት ይህን https://forms.lmis.gov.et/uae-new-2/ ማስፈንጠሪያ ተጠቅመው መመዝገብ። Labor ID ከሌሎት የሚከተሉትን ሂደቶች ይከተሉ፦ 1. በ lmis.gov.et ይመዝገቡ። 2. በአቅራቢያዎ ባለ የአንድ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ ይስጡ እና የሰራተኛነት መለያ ቁጥር (Labor ID) ይያዙ። 3. Labor ID ካገኙ በኋላ በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ ገብተው መረጃዎትን በትክክል ሞልተው ያመልክቱ።

E-LMIS የርቀት (Remote) የሥራ ዕድሎችን የሚያገኙበትን ዕድል አመቻችቶልዎታል። የዲጂታሉ ዓለም የሥራ ዕድሎች በከፍተኛ ሁኔታ እየደጉ ነው። አሁን ላይ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ከሀገር ሳይወጡ
E-LMIS የርቀት (Remote) የሥራ ዕድሎችን የሚያገኙበትን ዕድል አመቻችቶልዎታል። የዲጂታሉ ዓለም የሥራ ዕድሎች በከፍተኛ ሁኔታ እየደጉ ነው። አሁን ላይ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ከሀገር ሳይወጡና ድንበር ሳይገድባቸው ዓለም አቀፍ የሥራ አማራጮችን E-LMIS ላይ ማግኘት ይችላሉ። እንደ Data entry, IT support ያሉ ክህሎቶችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ሙያዎች ባለቤት ከሆኑ ቤትዎ ሆነው ዶላር ለመሥራት ብሎም አለም አቀፍ ተከፋይ ለመሆን ላፕቶፕዎ(Laptop) ብቻ በቂ ነው። ዛሬውኑ ይጀምሩ፦ ወደ E-LMIS ፖርታል በመግባት የርቀት(Remote) እና የፍሪላንስ (Freelance) የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ ይሁኑ ! We can/ይቻላል ! #RemoteWork #FreelanceJobs #DigitalJobs #ይቻላል

ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ባለፉት ሳምንታት በOnline እና በተግባር ተደግፎ ሲሰጥ የቆየው የInnovative Pedagogy ስልጠና ተጠቀቀ:: ስልጠናው በመጀመርያ ዙር በኮሌጁ 20 ለሚሆኑ አሰልጣኝ መምህራን መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን ይህ የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት እንዲሁም በፌደራል TVET ኢንስቲትዩት ባለሞያዎች አማካኝነት ሲሰጥ የቆየ የ15 ቀን የOnline እና የ5 ቀን ተግባራዊ ስልጠናን ያካተተ እንደነበርም ተገልፇል:: ባለፉት ሳምንታት የInnovative Pedagogy ስልጠናውን ሲከታተሉ የቆዩት የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እንደገለፁት ያገኙት ስልጠና ወቅቱን ያማከለና ዲጂታላይዜሽን ላይ ያተኮረ በመሆኑ የስልጠና አሰጣጥ ሂደታቸውን ምቹና ቀልጣፋ በማድረግ ከሰልጣኝ ተማሪዎች ጋር ያላቸውን ተግባቦት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሻገሩም ባሻገር በዘርፉ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ የሚረዳ የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ እንደሆነም ሀሳባቸውን አካፍለዋል:: የInnovative Pedagogy ስልጠናውን በፕሮጀክቱ ትግበራ የትኩረት ዘርፍ በሆኑት የኮሌጁ የማኑፋክቸሪንግ፣ የኤሌክትሪክ እና የአውቶሞቲቭ ዲፓርትመንቶች ላይ ለሚገኙ 20 አሰልጣኝ መምህራን ሲሰጥ መቆየቱን የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ የዚህ ስልጠና አላማም የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች አለም የደረሰበትን የዲጂታልይዜሽን የስልጠና አሰጣጥ ስነ-ዘዴ ጋር አብረው እንዲጏዙ ለማስቻል እንደሆነ አስታውቀው ከዚህ ስልጠና በተጨማሪም ራስን በየጊዜው ማሻሻል እንደሚገባም ገልፀዋል:: በስልጠናው ማጠቃለያ የInnovative Pedagogy ስልጠናውን ወስደው ያጠናቀቁ አሰልጣኝ መምህራን በዲጂታላይዜሽን የስልጠና ስነ-ዘዴው በመታገዝ በቀጣይ ስልጠና የሚሰጡበትን የአሰራር ሂደት በመድረኩ ያቀረቡ ሲሆን በዚህ መነሻነትም ለቀጣይ የስልጠና ዘመን ከወዲሁ በቂ ዝግጅቶች ተደርገውበት ዲጂታል የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴው ስራ ላይ እንደሚውልም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ላለፉት አመታት ሲተገብር የቆየውን የVQEP/Green Energy TVET Project Phase II ፕሮጀክት አጠናቆ የማጠቃለያ መድረክ አካሄደ:: ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት በአስተዳደራችን ለመጀመርያ ጊዜ ከ130 በላይ ወጣቶችን አዲስና ተፈላጊ በሆነ የሙያ ዘርፍ(Solar PV Installation & Maintenance) ላይ አሰልጥኖ ወደ ስራ እንዲገቡ ያደረገ ፕሮጀክት መሆኑን ያስታወሱት የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ ፕሮጀክቱ በስልጠናው ዘርፍ ለፈጠረው አቅም ፣በከተማና በገጠር ላከናወነው የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የSolar ኢነርጂን ተደራሽ በማድረግ የGreen TVTን በተግባር እንድናሳይ ላከናወናቸው ተግባራት በቢሮውና በአስተዳደሩ ስም ምስጋና አቅርበዋል:: ADRA Ethiopia በሀገሪቱ ብዙ ቦታዎች ላይ ይንቀሳቀስ የነበረ ቢሆንም ድሬዳዋን ተደራሽ ያደረገው በዚህ ፕሮጀክት መሆኑን ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ከዚህ በፊት ያልነበሩ እንቅስቃሴዎችና ብዙ በረከቶችንም ወደ ተቋማች ይዞልን የመጣ ፕሮጀክት ነው ያሉ ሲሆን በGreen Energy ላይ ግንባር ቀደም ሆነን እንድንሰራ ፈር የቀደደልን ልዩ ፕሮጀክት ነውም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ፕሮጀክቱ ያስቀመጠውን ግብ በመምታት ረገድ ጥሩ የሚባል አፈፃፀም እንደነበረው አስታውሰው ፕሮጀክት የራሱ የጊዜ ገደብ ያለው በመሆኑ ዛሬ ማጠቃለያ ብናደርግም በቀጣይ በጋራ የምንሰራቸው በርካታ ስራዎች በመኖራቸው እንደ ተቋም ደስተኞች ነንም ብለዋል:: የADRA Ethiopia ፕሮጀክት በ120 ሀገሮች ውስጥ ቢሮ ከፍቶ የሚቀሳቀስ ግብረ ሰናይ ድርጅት እንደሆነ ያስታወሱት የፕሮጀክቱ ዋና ዳይሬክቶር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ላለፉት 43 አመታትም በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ላይ ሰው ተኮር ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀው በውቢቷ ድሬዳዋ በነበረው የፕሮጀክቱ ሂደትና የተመዘገበው ውጤት እጅግ የሚያኮራና የአስተዳደሩንም ሆነ የኮሌጁን አመራሮች ቁርጠኝነት የተመለከቱበት እንደነበርም ገልፀዋል:: በማጠቃለያ መድረክ ላይ የADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ያከናወናቸውን ቁልፍ ተግባራትና ያስመዘገባቸውን አመርቂ ውጤቶች በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለባለድርሻ አካላት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ ሂደት ላይ በኮሌጁ ጥናት በማድረግ የመጣውን ለውጥ የሚገመግም ሰነድም በመድረኩ ቀርቦ ገለፃ ተደርጎበታል:: በመጨረሻም የፕሮጀክቱ አመራሮች ከስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ከኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እጅ ላበረከቱት አስተዋፅኦ የእውቅና ሰርተፊኬትና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል:: ADRA Ethiopia ከጀርመን የልማት ትብብር ተቋም(BMZ) እና በADRA Germany በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ከጥቅምት 2015 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ከሌሎች ቁልፍ ባለ ድርሻ አካላት በመተባበር ሲተገበር የነበረው የVQEP/Green Energy TVET Project Phase II ፕሮጀክት በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ በዛሬ እለት ፍፃሜውን አድርጏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ