✍وَقُل رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا📖 ✍ጌታዬ ሆይ እውቀት ጨምርልኝ በል📖እውቀት የሚቀሰምበት ጉርፕነው::ወደ ቻናላችን እንኳንበሰላም መጡጣ
189
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
-630 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
Repost from 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 ቅድሚያ ለተዉሂድ
➲ትዕግስት
〰〰〰〰
↪️ክፍል አንድ↩️
➖➖➖➖➖➖
➥ #ትዕግስት ከእስልምና ሐይማኖት ደረጃዎች ትልቁና ከፍ ያለ ቦታየሚሰጠው ነው፡፡
➥ትዕግስትን ፣ አላህ ሱበሀኑሁ ወተአላ በቁርኣን ውስጥ በርካታ ቦታዎች ላይ አውስቶታል፡፡
ኢማም አህመድ ራሂመሁሏህ ተአላህ ትዕግስትን አስመልክቶ የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
"ذكر الله الصبر في القرآن الكريم في أكثر من تسعين موضعا"
➥“አላህ ሱበሀነሁ ወተአላ ትዕግስትን ፣ በተከበረው ቁርኣን ፣ ከዘጠና በላይ በሚሆኑ ቦታዎች ላይ አውስቶታል፡፡”
መዳሪጅ አስ ሳሊኪን፡ 1/130
➥ይህ የኢማም አህመድ ንግግር ትዕግስት ፣ ከፍ ያለ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን ፤ ባሮች የታዘዙትን ለመስራት ፣ የተከለከሉትን ለመተው ፤ አላህ በወሰነባቸው መከራ እንዳይቆጩና እንዳያማርሩ በጣም የሚያስፈልጋቸው መሆኑን በግልጽ የሚጠቁም ነው፡፡
➥ትዕግስት ፣ ለባሮች በጣም አስፈላጊ ፣ በማንኛውም ሁኔታቸው የማይነጠል
ጓደኛቸው ሊሆን ይገባል፡፡ ያለትዕግስት የታዘዙትን መስራት አይችሉ ያለትዕግስት
ወንጀልን መራቅ አይችሉም ፤ያለትዕግስት አላህ የወሰነባቸውን ውሳኔ ሳይበሳጩ ወደው መቀበል አይችሉም፡፡ በማንኛውም ሁኔታ በትዕግስት መሸለምን ለሙስሊም ምን በጣም አስፈላጊ አደረገው!
➥በቁርኣን ውስጥ ስለትዕግስት ፣ በተለያየ መልኩ በርካታ ቦታዎች ላይ አላህ ሱበሀነሁ ወተአላ አውስቷል፡፡
➥ ትዕግስትን የሚያዙ ፣ እርሱን መቃረን ክልክል መሆኑን የሚገልጹ ፣ የትዕግስትን ባለቤቶች የሚያወድሱና የሚያሞካሹ ፣ ለትዕግስተኞች ያዘጋጀውን የተነባበረ ምንዳና ያማረ ፍጻሜ የሚያወሱ ለታጋሾች ወሰን የሌለው ብስራትን የሚያወሱ አንቀጾች መጠዋል፡፡
➥ትዕግስተኞችን አላህ እንደሚወዳቸው ፤ በእርዳታው ፣ በጥበቃውና በእገዛው
ከትዕግስተኞች ጋር እንደሆነ ግልጽ አድርጓል፡፡ ይህ ሁሉ ፣ ትዕግስት ደረጃው ላቅ ያለ ፣ ቦታው ከፍ ያለ እንደሆነና እርሱ በጣም አስፈላጊያችን መሆኑን ይጠቁማል፡፡
➥ትዕግስት በርካታ ጎኖች እና ገጽታዎች ያሉት በመሆኑ ስለርሱ ብናወራ ሰፊ
ከመሆኑ የተነሳ ቦታ አይበቃንም፡፡ ታዲያ ንግግራችን በተወሰነ ክፍል ብቻ እንዲገደብ ሆኗል፡፡ እርሱም “ሰዎች በሚያደርሷቸው ስቃዮችና መከራዎች ላይ መታገስ” የሚል ነው፡፡
➥የሰዎች ተፈጥሯዊ ባህሪ እና ስነምግባር የተለያየ በመሆኑ በዚህ ዓለም ሲኖር ከእንግልትና ከመከራ ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡ ታዲያ ሙስሊም በሚገጥሙት መከራዎች እና ፈተናዎች ላይ በትዕግስት ሊዋብና ሊሸለም ይገባዋል፡፡
ኢንሻአላህ
ይቀጥላል ክፍል ሁለት
➢ኢንሻአላህ ትዕግስት የምትለዋን ኪታብ በተከታታይ በፅሁፍ የምናቀርብላችሁ ይሆናል አላህ ሁላችንንም በምናነበውና በምናውቀው ነገር ተጠቃሚዎች ያድርግልን!!
ሺር አድርጉት⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/joinchat/AAAAAFfWT8MnOTBo42gK-w
800
ተጋበዙልኝ
ጣፋጭ ቲላዋ💦✍️
وان_ربك_لهو_العزيز_الرحيم_❤️_محمد_هشامM4A_128K.m4a9.86 KB
1400
ውሀ ምድርን ህያው እንደሚያደርጋት ሁሉ ቁርአንም ቀልብን ህያው ያደርጋታል።
ኢብኑል ቀይም
ከቁርአን ጋር እንኑር...!
=
t.me/https_Asselefya1AUD-20180306-WA0000.mp32.94 MB
1600
03:16
Video unavailable
66.36 MB
710
IMG_20240120_115529_397.jpg2.00 KB
500
ፊትናው በዛ ሀያእ ጠፍቶ
ወጣ ስንል በመንደሩ
ሴትም ወንድም በመኖሩ
እሷም በወንዱ ስታፈጥ
ወንዱም አይቷት ሲያገጥ
ከንፈሯ መስሎ ወጥ በወጥ
ይዟት ሲዞር ጎጥ ለጎጥ
እጁን ትከሻዋ ላይ ማኖሩ
ሲያቅፋት አለማፈሩ
ሳትሆን ለሱ ባለቤቱ
ወይ አይደለች ውድ እህቱ
አልወለዳት ልጁ አይደለች
ያልተፈቀደችለት አጅ ነብይ ነች
እሷም ስቴድ አለማፈሯ
ፊቷን አስመስላው አቧሯ
ቀሚሷን ማሳጠሯ
ብጣሽ ሻርፕ አርጋ ለፀጉሯ
ብቅ ስትል በመንደሩ
የሽቶዋ ሽታ በሰፈሩ
ወንዶትን ሁሉ መጥራቱ
ወደ ሀራም መጎተቱ
ሀያእ አጥታ ልጅቱ
ፈሳድ ሞላው ከቤቱ
ጉዱ ተወርቶ አለማለቁ
የሴት ከወንድ ድብልቁ
በየቦታው መማቀቁ
በየ ሚዲያው መሳሳቁ
ሀያእ ቢጠፋ ከመንደር
ወንጀል ቢበዛ በሀገር
የፀሀዪ እንዲ ማቃጠል
የብርዱ እንዲህ መቆምጠል
በሌላ አይደለም አታማር
ቻለው ምንም ቢመር
ያንተው የኔም ወንጀል
ሲበዛ ይከረፋል
ለመስማትም ይቀፋል
ሲያዩትም ያስከፋል
ከኛአልፎ ለንፁሀኑም ይተርፋል
ተውባ አድራጊ ጠፍቶ
ፈሳድ ባለሙ ተስፋፍቶ
ዛሬ ብትጮህ በደረቁ
ህዝብ እንዲህ ማለቁ
እሬሳ አይቶ መሳቀቁ
ጉድኮ ነው መብዛቱ
የወንጀላችን ማስጠላቱ
ዳኢ ተብዬ ያ ወንዱ
ዘፈን ሙዚቃ በመፍቀዱ
ኢስላማዊ ፊልም ማለቱ
ቢድአውን ማስፋፋቱ
በዲኑ ላይ መጫወቱ
ተውሂድ ሱናን በመርሳቱ
አቤት ምድር ማስጠላቱ
በዚህ ፈሳድ መሞላቱ
ሲያንሰን ነው ፀሀይ ብርዱ
ጠፍቷል ሁሉ መዋደዱ
በዑለሞቻችን ማሾፍ በዝቶ
ቢደአን ስንወድ ሱናን ጠልቶ
እርስበርስ እዝነት ጠፍቶ
ወሬያችን እንቶ ፈንቶ
አይናፋርነት ተጠልቶ
ፊትናው በዛ ሀያእ ጠፍቶ
አይናፋርነት ተጠልቶ
ስቃይ በዛ እዝነት ጠፍቶ። ,
👍 3
4600
Repost from ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)
🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿
በአጥፊዎች መመሳሰል ውጉዝ ነው
~
ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
[مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ]
"በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው።"
📚[ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 3401]
⛔️ሙስሊም የሆነ ሰው ራሱን የማንም ቆሻሻ ባህል ማራገፊያ አያደርግም። ሰው እንዴት የፍቅረኛሞች ቀን (Valentine Day) የሚሉት የዝሙት ማስፋፊያ ልማድ ያስተዋውቃል? ዝሙትኮ በኢስላም ህይወት የሚያስነጥቅ ከባድ ወንጀል ነው። ከቻላችሁ በስርአት አግቡ። ካልሆነ አላህ እስከሚያገራላችሁ ድረስ በተቅዋና በሶብር ጠብቁ። በብልግና ውስጥ የሚፈለግ ደስታ ርክስትና ውርደትን ነው የሚያመጣው።
⛔️ሌላው የሚገርመው ነገር በትምህርት ተቋማት ውስጥ ''የእብድ ቀን (Crazy Day)" ብለው የሚያከብሩ መኖራቸው ነው። ትምህርት ቤቶች ይህንን ነው ለሃገርና ለትውልድ የምታወርሱት? ይሄ አደራን መብላት አይደለም? ወላጆች ሆይ! ይህንና መሰል የተጨመላለቁ ባህሎችን ለልጆች የሚያወርሱ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ልጆቻችሁን አታስተምሩ።
⛔️ከነጮች ከተወረሱ ነውረኛ ባህሎች ውስጥ ሌላው April the Fool የተሰኘው የጅላጅሎች ልማድ ነው። ያልተከሰቱ ሃሰተኛ ነገሮችን በመንገር ሰዎችን በማስደንገጥ ይዝናናሉ። ሰዎች ላይ ከሚፈጠረው ከባድ ድንጋጤ ይልቅ የራሳቸውን ቅፅበታዊ ደስታ ያስቀድማሉ። ውሸት በኢስላም ሐራም ነው። ለቀልድ እያሉ ማቅረቡ እውነታውን አይቀይረውም። ነብያችን ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
[وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ ]
"ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!"
📚[አቡ ዳውድ፣ ነሳኢይ፣ ቲርሚዚይ እና አሕመድ የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒይ “ሐሰን” ብለውታል፡፡]
ውሸቱ ሰዎችን ማስደንገጥ ሲኖርበት ደግሞ ይበልጥ የከፋ ወንጀል ይሆናል። የሌሎችን ብልሹ ባህል በማስፋፋት መልክ ሲቀርብ ደግሞ የበለጠ ፀያፍ ይሆናል።
በጠቅላላው የቀረቡት ምሳሌዎች ብቻ ናቸው። ራሳችንን የሌሎች አጉል ባህል ማራገፊያ ልናደርግ አይገባም። ልጆቻችንንም ከእንዲህ አይነቶቹ ጎጂ ባህሎች ለመጠበቅ ልናነቃ ይገባል።
IbnuMunewor
https://telegram.me/ibnukedir
ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)
የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ (ከሰዎች መካከል የመልካም በር ከፋች የሆኑና የመጥፎ በር ዘጊዎች የሆኑ አሉ ፤ እንዲሁም ከሰዎች መካከል የሸር በር ከፋች የሆኑና የመልካም በር ዘጊ የሆኑ አሉ። አላህ የመልካም በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ጡባ’ አለለት ፤ አላህ የመጥፎ በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ወይል’ አለለት።) [ኢብኑ ማጃህ (237) ዘግበውታል።
4000
Repost from ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)
🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿
የፈጅር ሰላት ሱና በሦስት ነገሮች ይለያል……
💎አንደኛው፦
ከሁሉም ሱንናዎች በላጭ ነው። ነብዩﷺ
«ركعتا الفجر خير من الدنيا وما فيها»
«የፈጅር ሁለት ረካዓዎች ከዱንያና በውስጧ ካለው ነገር ሁሉ በላጭ ናቸው።» ብለዋል።
💎ሁለተኛው፦
ጉዞም ላይ ይሁን ሀገር ላይ ተኩኖ ይሰገዳሉ። በተቃራኒው የሌላ ሰላት ሱናዎች ጉዞ ላይ ተኩኖ አይሰገዱም።
💎ሦስተኛው፦
የተለየ የተገደበ የሆነ ሱራ ይቀራባቸዋል። እሱም በመጀመሪያው ረከዓ
📖 "قل يا أيها الكافرون"
እና: በሁለተኛው ረከዓ
📖"قل هو الله أحد"
ነው።
/ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አላህ ይዘንላቸው/
(شرح بلوغ المرام / ج4 / ص151).
🔻 ለፈጅር የምትሞላው አላርም ላይ 4 ደቂቃ ብቻ አሻሽለህ ብትሞላ «ከዱንያ እና ከያዘችው ነገር በአጠቃላይ የሚበልጥ» ኸይር ማግኘት ትችላለህ።
Copy
https://telegram.me/ibnukedir
ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)
የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ (ከሰዎች መካከል የመልካም በር ከፋች የሆኑና የመጥፎ በር ዘጊዎች የሆኑ አሉ ፤ እንዲሁም ከሰዎች መካከል የሸር በር ከፋች የሆኑና የመልካም በር ዘጊ የሆኑ አሉ። አላህ የመልካም በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ጡባ’ አለለት ፤ አላህ የመጥፎ በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ወይል’ አለለት።) [ኢብኑ ማጃህ (237) ዘግበውታል።
2910
Elige un Plan Diferente
Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.