es
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Ir al canal en Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Mostrar más
3 502
Suscriptores
+424 horas
+87 días
+10830 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ 7ተኛ መደበኛ ጉባኤ ለቀጣይ አራት ዓመታት ሲኖዶሱን የሚመሩ መሪዎችን በመምረጥ በስኬት ተጠናቋል። በዚህም መሠረት፥ 1. ቄስ ጋምቤላ ሉአል ፕሬዚዳንት 2. ቄስ ሞሰስ ኦዝ ምክትል ፕሬዚዳንትና 3. አቶ ጴጥሮስ ቾርኮል አቃቤ እንዋይ በመሆን ተመርጠዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የተመረጠቱትን አዳዲስ የሲኖዶሱ መሪዎች ቃለ መሃላ አስገብተዋል። የአገልግሎት ጊዜውን የጨረሰውን አመራር በማመስገን በቅርብ ሆኖ አዲሱን የአመራር ቡድን እንዲግፍ አሳስበዋል። ጉባኤውንም የምስራቅ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ ኚግዎ ኦሞድና የሲኖዶሱ አመራሮች፣ በጋምቤላ የአንግሊካን ቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው አንግዶች ተገኝተው ተካፍለዋል።

A Jithɛth cɛ jɛ lar ɛ thuɔ̱k bä lätdɛ lät a thil pek...! የ7ኛው የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ ጉባኤ ማጠቃለያ የህብረት ዝማሬ በኑኤር ቋንቋ። "ኦ ኢየሱስ ፈቃድህን ልፈጽም ቃል ገብቻለሁ..." The 7th West Gambela Betel Synod Convention closing song in Nuer Language. "Oh, Jesus, I have promised to do your wills..."

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ 7ተኛውን የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ ጉባኤን ለመካፈል ጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ገብተዋል። የጋምቤላ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የሲኖዶሱ ኘሬዚዳንት ቄስ ጀምስ ጋዴት፣ የሲኖዶሱ ማኔጅመንት፣ ምዕመናንና የመንግሥት ተወካዮች ተቀብለዋቸዋል። ከእርሳቸውም ጋር የቤተ ክርስቲያኒቱ የቤቴል ሲኖዶሶች ህብረት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስተባባሪ ቄስ ዶ/ር ተፈሪ በርኬሳ በጋምቤላ የተገኙ ሲሆን መሪዎቹም ከምዕመናንም ጋር በጋራ የጌታን ዕራት ተካፍለው ለምዕመናን ሰላምታ አቅርበዋል። ሐምሌ 23 ቀን 2017 ጋምቤላ

የቤተ ክርስቲያን አንድነት ሥነ-መለኮት (The Theology of Church Unity) በሚል ርዕስ ሥልጠና በአዶላ ከተማ ተሰጠ * * * * * * በአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ ከበርካታ ሰበኮችና ማኀበራነ ምዕመናን ለተወጣጡ ቁጥራቸው ከ1,300 በላይ ለሚሆኑ ወንጌላዊያን፣ ቄሶችና የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ሥልጠናው ተሰጥቷል። አንድ ሙሉ ቀን የወሰደውን ይህንን ሥልጠና የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌልና ቲኦሎጂ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል ሰጥተውታል። በሲኖዶሱም ባሳለፍነው ዕሁድ የቅስና ሃላፊነት ለተቀበሉት አገልጋዮች የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶለሳ ባሳለፍነው ሳምንት የቅድመ ቅስና ስልጠና ለእጩ ቀሳውስቱና ለትዳር አጋሮቻቸው ሰጥተዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በሁለቱም ሥልጠናዎች ላይ ተገኝተው ለአገልጋዮቹ ጠቃሚ መልዕቶችን አስተላልፈዋል።

ለቃሉ እና ቁዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ለ31 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል * * * * * * የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አዶላ ገናሌ ሲኖዶስ በተካሄደ የቀሳውስት ምደባ ሥነ-ሥርዓት የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃልና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ ለ31 አገልጋዮች በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱም የወንጌል እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማር ለእጩ ቀሳውስቱና ለምዕመናን የማበረታቻ ቃል አስተላልፈዋል። በስፍራውም ምዕመናን፣ የእጩ ቀሳውስት ቤተሰቦች፣ የሲኖዶሱ አገልጋዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ለእጩ ቀሳውስቱም እጅ በመጫን ስአገልግሎታቸው ሥኬት ተፀልዮላቸዋል። በአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ እየተካሄደ ስላለው ሰፊ የወንጌል አገልግሎት እና ወደ ማሳው አገልግሎት ስለተጨመሩ ቀሳውስት የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን። ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም አዶላ ወዩ፣ ምስራቅ ጉጂ _ _ _ _ _ _ Wendmagen Youth H Office: Tajaajila Sagalee Waaqayyoo fi Dhoksaalee Qulqulluutiif Tajaajiltootni 31 Lubummaan Muudaman. * * * * * * Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaa, Sinoodoosii Adoolaa Gannaaleetti sagantaa eebbaa fi rammaddii lubootaatiin, tajaajila Sagalee Waaqayyoo fi Dhoksaalee Qulqulluutiif tajaajiltoota 31'f Pirezidaantii Waldattii kan ta'an Luba Dr. Yoonaas Yiggazuutiin itti gaafatamni lubummaa kennameera. Daarektara Qajeelcha Tajaajila Wangeelaa fi Ti'ooloojii Waldattii kan ta'an Lubni Dr. Lalisaa Daani'eel Sagalee Waaqayyoo barsiisuudhaan, luboota kaadhimamtootaaf gorsa kennaniiru. Sagantaa kanarratti, amantootni, maatiin luboota kaadhimamtootaa, tajaajiltootni sinoodoosichaa fi keessummootni waamichi godhameef adda addaa argamaniiru. Luboota ramaddiin keennameefis harka irra kaa'uun kadhannaan godhameera. Sinoodoosii Adoolaa Gannaaleetti hojii Wangeelaa bal'aa hojjatamaa jiruuf, tajaajila Wangeelaatiif tajaajiltoota dabalamaa jiranuuf Waaqayyoof galanni haa ta'u! Adoolessa 20, 2017 Adoolaa Woyyuu, Gujii Bahaa