5killo Jem'a official Channel
Ir al canal en Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Mostrar más1 159
Suscriptores
-124 horas
Sin datos7 días
-130 días
Archivo de publicaciones
+1
በአባጅፋር ሀገር ጅማ የሚገኘው የጅማ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው፦
"ይህ ጉዳይ መቆየቱ እና አለመፈታቱ በአስተዳደሩ ዘንድ መፍትሔ ለማበጀት ፍላጎት እና ቁርጠኝነት እንደሌለ የሚያመላክት ሲሆን፤ በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ያነጣጠረ ስልታዊ መድልዎ እንዳለ ያሳያል። በሀገሪቱ በተደረጉ ረጅም ጥረቶች ውስጥ ዋና ሚና የነበረው ይህ ዩኒቨርስቲ ፤ ለሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ዘላቂ መፍትሔ ማግኘት ሳይችል መቆየቱ እና ከመፍትሔ ይልቅ መከልከልን እርምጃ አድርጎ መውሰዱ ከባድ ተቋማዊ ድክመትን ያሳያል።" - በማለት የተጠቀሰ ሲሆን መመሪያው ተሻሽሎ ዘላቂ መፍትሔ ይሰጥ ዘንድ ተጠይቋል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። ለሁሉም ይደርስ ዘንድም አሰራጩት። ከጀሰዲን ዋሂድ ሲኮን እንዲህ ነው። ቀጣይ እርምጃስ ምን ይሆን? ከየትስ ይሆን?
©aaumsu
@fivekjemaa
የሴቶች ወር _ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ !
የሙስሊም ሴቶችን መብት የሚጋፋ መመሪያ በማውጣት ሕይዎታቸውን ያከበደው በዶክተር ሳሙኤል ፕሬዚዳንትነት የሚመራው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሴቶች በዩኒቨርስቲው ስላላቸው ቆይታ፣ ስኬት እና ራዕይ የሚያወራ ፅሁፍ በፌስቡክ ፔጁ ለቋል። እናንተም ግቡና ሊያዩት ስላልፈለጉት የሙስሊም ተማሪዎች ቆይታ፣ ስቃይ እና እንግልት ንገሯቸው። እየጠየቅን ስላለው ፍትሕም በአደባባይ ጠይቁ።
ሊንኩ https://www.facebook.com/100064311447035/posts/pfbid0EaqHa1kG1XMbjgMY5nZpRo5yiRzQCANp6U6y1d9BxBAF1i8n7PJRLFkh6unppxDZl/ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
📌አላህ ዘንድ ተወዳጅ ለመሆን ለሰዎች ትረፍ!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿أحبُّ الناسِ إلى اللهِ أنْفَعُهُمْ لِلنّاسِ، وأحبُّ الأعمالِ إلى اللهِ عزَّ وجلَّ سُرُورٌ يدْخِلُهُ على مسلمٍ، أوْ يكْشِفُ عنهُ كُرْبَةً، أوْ يقْضِي عنهُ دَيْنًا، أوْ تَطْرُدُ عنهُ جُوعًا﴾
“ከሰዎች አላህ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑት ለሰዎች የሚጠቅሙት ናቸው። አላህ ዘንድ ተወዳጅ ተግባር ማለት በሙስሊም ውስጥ የምታሰገባው ደስታ፣ ወይም ከሱ ላይ የምትገፈው ጭንቅ፣ ወይም ለሱ እዳውን መክፈልህ፣ ወይም ከሱ ላይ ርሃብን ማባረርህ ነው።”
📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ፡ 906
#ስለመንገዱ
💭ከተራነት ምንወጣበት! በኛ ተራነት ደግሞ ላስናቅነው ውዱ እስልምናችን ክብሩን ምንመልስበት ጊዜው መች ይሆን?!
የ ሂጃብሽ ••
የ እስልምናሽ •••
የ ተማሪነትሽ ዋጋስ ስንት ይሁን ??!
የ ጉዞው ርዝመቱ..
ያንቺ አበርክቶስ ምን ያክል ይሁን !??
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مَا لَكُمْ إِذَا قِيلَ لَكُمُ ٱنفِرُوا۟ فِى سَبِيلِ ٱللَّهِ ٱثَّاقَلْتُمْ إِلَى ٱلْأَرْضِ ۚ أَرَضِيتُم بِٱلْحَيَوٰةِ ٱلدُّنْيَا مِنَ ٱلْـَٔاخِرَةِ ۚ فَمَا مَتَٰعُ ٱلْحَيَوٰةِ ٱلدُّنْيَا فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ إِلَّا قَلِيلٌ
እናንተ ያመናችሁ ሆይ!
በአላህ መንገድ (ለመታገል) ውጡ በተባላችሁ ጊዜ ወደ ምድር የምትወዘፉት ለእናንተ ምን አላችሁ ••
"የቅርቢቱን ሕይወት ከመጨረሻይቱ ይበልጥ ወደዳችሁን ?!!"
የቅርቢቱም ሕይወት ጥቅም በመጨረሻይቱ (አንጻር) ጥቂት እንጂ አይደለም!!
በ ዛሬው ስብስባችን ምናነሳቸው ጥያቄዎች፣ ምንዳስሳቸው ሃሳቦች ይሆናሉ ኢንሻአላህ !!
ዛሬ ከ አስር ቦሃል በ ሶስቱ campus እህቶች ስብስብ !!!!✨✨
#ስለመንገዱ
✨✨ውድ እህቴ!!! ✨✨
ለመሆኑ አሁን ላይ የክብር መገለጫሽ የሆነውን ሂጃብ ለብሰሽ ስትንቀሳቀሺ ቀደምቶቻችን የከፈሉት መስዋእትነትና ዋጋ ምን ያህል እንደሆነ አስተውለሽ ታውቂያለሽ ??!
🍂የትግል ጉዞ ረጅም፣ ጥልቅ፣ አስደሳች፣ አሳዛኝ፣ ብዙ ብዙ ነገሮችን የያዘ ነው። እና አሁን ላለንበት ቀደምቶቻችን: ውድ አባቶቻችን የሚገባቸውን : ከሚገባቸው በላይ የሆነንም መስዋእትነት ከፍለዋል።
ልጅ የአባቱን ፋና ተከታይ ነው!!
እኛም ይህን የሂጃብ ጉዞ ሙሉ ለማድረግ የኒቃብ ትግላችን ላይ ያሉ ገራሚ፣ አሳዛኝ፣ አስደሳች፣ ብዙ ብዙ የሆኑ ገጠመኞችን ልናጋራሽ ወደናል🥰
🗯ለ 4ኪሎ, 5ኪሎ እና 6ኪሎ ውድ እህቶች የተዘጋጀ ልዩ መድረክ 🗯
ውዶችዬ ! እነሆ ለእናንተ ለውድ እህቶቻችን ስለኒቃብ፣ ስለሂጃብ እና ስለሄድንበት እንዲሁም ስላለው ትግል ልናወጋችሁ ቀጠሮ ያዝን!።
~ በዚህ ቀጠሮ ላይ ያለፍንባቸውን እያንዳንዱ መንገዶችን እንቃኛለን!
~ በእነዚህ መንገዶች ላይ የገጠሙን ችግሮችን እናወሳለን!
~ ስለ ወደፊታችንም እናቅዳለን!
እንዲሁም ከሙተነቂብ መንደራችንንም በአካል እንሰማለን🥰
🍁በዚህ ፕሮግራም ላይ የእናንተ ድምጾች ዋጋ አላቸው። ጥያቄዎች ይመለሳሉ፤ ሀሳቦች ይገለጻሉ። ውይይቶች በነጻነት ይካሄዳሉ።
🪸ታዲያ ይህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ስለሂጃብ፣ ስለኒቃብ እንዲሁም ስለ ትግሉ ያለንን ቦታ ማሳየት ከኛ አይጠበቅምን!? ስለኒቃብ: ስለሂጃብ፣ ስለ ኢስላም ከፊት አለሁኝ እኔ: እመራለሁኝ የምትዪ እህት በዚህ ፕሮግራም ላይ አትገኝምን?! መቅረቱስ ዘበት ነው ግን እንደው ታረፍጂ ይሁን?! አሚራዎቻችን ስላለፉበት መንገድ በሚገልጹልን ፕሮግራም ላይ ያንቺ ድርሻ የቱ ጋር ይሆን?!!
እመኚኝ እንኳን መቅረት ማርፈድ ያስቆጫል!!😉
"መች ነው???".....ቆይ ቀስ ልነግርሽ እኮ ነው😌....ለነገሩ ልክ ነሽ ልብሽን ሰቀልኩታ!☺️
በይ እንግዲህ...ዛሬ ከ አስር ሰላት ቦሀላ እንድንገናኝ !!
+1
የወሎ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጥያቄ አለን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አፄ ዮሐንስ "ክርስትናን ያልተቀበለ ሙስሊም ከሀገር ይጥፋ!" - የሚልን አዋጅ ባስነገረ ጊዜ የወሎ ሙስሊሞች "እስልምናን ክደን ከምንኖር ሞት ይሻለናል።" - በማለት ነበር ቦሩሜዳ ላይ ስለእስልምናቸው ሲሉ መስዋዕት የሆኑት፤ አላህ በጀነተል-ፊርደውስ ይቀበላቸውና። ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ኒቃብ የሚለብስ ተማሪ ከዩኒቨርስቲ አይገባም በማለት መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎም የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ኒቃባችንን ሳናወልቅ ትምህርታችንን እንማራለን ከሚል አቋም ፀንተው የሚደርስባቸውን ጭቆና ተቋቁመው መቀመጣቸው ይታወቃል። ይህንንም በደል የወሎ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ከዚያው ከወሎ ከሸይኽ ጦልሓ ጀዕፈር ሀገር ሆነው ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጥያቄ አለን በማለት ተቃውመዋል።
ኒቃብ ማንነት ነው፤ ማንነት ደግሞ ስጋት ሊባል አይችልም!
ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጥያቄ አለን፤ መልስም እንፈልጋለን!
ጥያቄው የእኛም ነው!!!
የሚልን መልዕክት አስተላልፈዋል። እንደ አንድ አካል፤ እንደ አንድ ኡማ መቆም ማለት ይህ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from 5killo Jem'a official Channel
🔈 Applied Mathematics I Tutorial Announcement🔈
Based on the poll results, the majority of freshmen have chosen Thursday for the Applied Mathematics I tutorial.
🗓 Day: Thursday, April 23, 2026.
⏰ Time: 10:20 LT
📍 Venue: To be announced
This session is prepared to support you in strengthening your understanding and building confidence in the course.
Come prepared, bring your questions, and make the most out of this opportunity!
May Allah put barakah in our time and knowledge.
©Academic sector
ከሰዒድ አል‐አንሷሪ (ﷺ) ተይዞ፡ አንድ ሰው ወደ ነቢዩ (ﷺ) ዘንድ በመምጣት ይምከሩኝ አላቸው። እንዲህ አሉት፦
﴿أُوصيكَ أن تَستَحيَ مِنَ اللهِ تعالى، كما تَستَحي مِن الرَّجلِ الصّالِحِ مِن قومِكَ﴾
“ልክ ከህዝቦችህ ውስጥ ጥሩ የሚባልን ሰው ሐያዓ እንደምታደርገው (እንደምታከብረው) የላቀውን አላህንም ሐያዓ እንድታደርገው (በድብቅም በግልፅም ትዕዛዙንና ክልከላውን እንድታከብር) እመክርሃለው።”
📚 ሶሂህ አልጃሚ፡ 2541
Repost from AAU - Muslim Students Union
መልዕክታችን አጭር ነው
"በእምነቷ ምክንያት ከትምህርት ልትታገድ የሚገባ ተማሪ መኖር የለባትም!" - በማሌዢያ አልቡኻሪ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች መልዕክት ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጎን መሆናቸውን ዳግም የገለፁ ሲሆን ጥያቄው የእኛም ነው ብለዋል።
ደጋግመን እንዳልነው ጥያቄው የሁላችንም ነው። እነርሱ እንዳሉት ደግሞ "ኒቃቧንም ትለብሳለች! ትምህርቷንም ትማራለች!!"
መልዕክቱን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አድርሱልን ብለዋልና ይደርሳቸው ዘንድ በደንብ አሰራጩት። በኢንተርናሽናል ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ያለ ተማሪዎች በምን መልኩ እየተማሩ እንዳሉ ግንዛቤ እና ልምድ ይውሰዱ፤ ከዚሁ ከሀገራችን ሄደው እየተማሩ ያሉ ተማሪዎችንም ከልብ የመነጨ መልዕከት ያድምጡ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በአዲስ አበባ ከተማ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ የቀረበ ዝርዝር መግለጫ።
ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የሕዝበ ሙስሊሙ ማንነት እና ክብር መገለጫ የሆነውን ኒቃብ የሚከለክልን መመሪያ በማውጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ለ19 ወራት ያክል የመብት ጥሰት ሲፈፀም እንደቆየ የአደባባይ ሐቅ ነው። ክልከላው ከሴኩላሪዝም ጋር በተያያዘ ፤ ከደህንነት እና ፀጥታ ጋር በተገናኘ ፤ በመማር ማስተማር ወቅት በመምህር እና ተማሪ ጋር ሊኖር ከሚገባ ግንኙነት ጋር በተገናኘ ከመሆኑም ባሻገር ለዚህ ሲባል በሕገ- መንግስቱ የፀደቁ የነፃነት መብቶችን መገደብ እንደሚችሉ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በተለያየ ጊዜ ራሳቸው ዶክተር ሳሙኤል እንደገለፁም እሙን ነው።
በመመሪያው የሰፈረው እና እርሳቸው በተናገሯቸው ንግግሮች ውስጥ የተቀመጡት ምክንያቶች የሌለን ነገር በመፍጠር ስጋት ለማድረግ ከመሞከራቸው ባሻገር ከሕግ፣ አመክንዮ፣ ኢትዮጵያዊ እሴቶች እና ተለምዷዊ አሰራሮች ያፈነገጡ መሆናቸውን በተደጋጋሚ እየገለፅን አስቸኳይ ማስተካከያዎች ተደርገው መመሪያው እንዲሻሻል እና በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው በደል ይቆም ዘንድ ስንጠይቅም ነበር። ጥያቄውን ባቀረብን ወቅት የተፈጠረውን ችግር በውይይት ለመፍታት እርሳቸው ባሉበት መንገድ የተጀመረ ቢሆንም መፍትሔ ሊመጣ በተቃረበበት ወቅት ግን እንደ ሙስሊም ተማሪ የውይይቱ አካል የነበሩትን ተወካዮች አናውቃችሁም በማለት የውይይቱ በር መዘጋቱ ይታወሳል። ከዚያም ቡሃላ ደብዳቤዎችን አንቀበልም ብሎ ከመመለስ ጀምሮ የተቀበሉት ደብዳቤ ላይ ስርዝ አድርጎ አናውቃችሁም የሚልን ፅሁፍ ፅፎ እስከመመለስ ተደርሶ ነበር።
በእነዚህ ሂደቶች ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ በሕገ- መንግስቱ የፀደቁትን የሐይማኖት ነፃነት እና እኩልነት መብትን በመጣስ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት፣ ክብር፣ እምነት እና ማንነት የሚጣረስ እና የሚጎዳ መመሪያ ስለወጣ በውይይት ይሻሻል፤ በመመሪያው ምክንያት እንግልት ለደረሰባቸው ተማሪዎች ፍትሕ ይፅና ቢሆንም የውይይትን በር ዘግተው እስካሁን አሉ። በተለያዩ ጊዜያቶች በነበሩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ከአዲስ አበባ የፀጥታ ክፍል እና የብልፅግና ሀላፊዎች ጋር በነበረን ውይይት እነርሱ ባሉበት ከዶክተር ሳሙኤል ጋር ውይይት እንደሚደረግ የገለፁልን ቢሆንም፤ በሰዓቱም እራሳቸው ዶክተር ሳሙኤል ለውይይት እንደሚቀርቡ እንደገለፁላቸው ቢያስቀምጡልንም ቀኑ ሲደርስ ግን እምቢ ብለዋል በሚል ምክንያት ውይይቱ ሳይደረግ ቀርቷል።
የፌደራል መጅሊስ ችግሩ ከተፈጠረ ከ19 ወራት ቡሃላ ከዶክተር ሳሙኤል እና ከሌሎች አመራሮች ጋር ተወያይቶ ችግር እንደማይፈጠር በቃል እንደተገለፀላቸው በፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በኩል የተገለፀ ቢሆንም እስካሁን ከነበሩት ሁኔታዎች፤ ከተፈጠሩ ችግሮች፤ የዩኒቨርስቲያችን ፕሬዚዳንት ብለውታል እየተባለ ካልተፈፀሙ ቃሎች አንፃር የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ልዑክም በዚያው ዕለት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም እና ከመጅሊሱ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረገው ስብሰባ "ብቸኛው እና የመጨረሻው መፍትሔ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ አድልዎ የሚፈጽመው መመሪያ እንዲሻሻል ማድረግ ብቻ ነው" የሚለውን ጽኑ አቋሙን በግልጽ አስቀምጧል። በዚህም መሰረት በመጅሊሱ እና በህብረቱ ተወካዮች መካከል በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ስምምነት ተደርሷል፦
1ኛ፦ ዩኒቨርስቲው ያወጣው ጨቋኝ መመሪያ በቶሎ እንዲስተካከል መጅሊሱ በቁርጠኝነት እንዲሰራ
2ኛ፦ መመሪያው ከወጣበት ጊዜ አንስቶ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የፈፀሙ የዩኒቨርስቲው አካላት በሕግ አግባብ ይጠየቁ ዘንድ መጅሊስ እና ህብረቱ በቅንጅት እንዲሰሩ።
3ኛ፦ ከዩኒቨርስቲው ጋር ያለው ግንኙነት ይቀጥል ዘንድ ከመጅሊሱ የሚወከሉ ተወካዮች ከተማሪዎች ጋር በመሆን ከዩኒቨርስቲው ጋር እንደሚወያዩ
4ኛ፦ በሀገርአቀፍ ደረጃ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ በመጅሊስ ከተቋቋመው 17 ኮሚቴ ጋር ተማሪዎች በቅርበት እንዲሰሩ
ይህ በእንዲህ እንዳለ እስካሁን ባለው ሂደት የተፈጠሩ ችግሮችን በማረም እና ማስተካከል ረገድ ከዩኒቨርስቲው አመራሮች በኩል ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳልተደረገ ለማሳወቅ እንወዳለን። በተቃራኒው ግን በሚያዚያ 12 / 2018 ዓ.ል ዩኒቨርስቲው ችግሮችን ለመፍታት ፍቃደኛ ነኝ ባለበት ቀን ችግራቸውን በማስረዳት መፍትሔ ፍለጋ ከተማሪዎች ዲን ጽ/ቤት የሄዱ 13 ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን አግባብነት የሌለውን ምላሽ በመስጠት መልሷቸዋል። በዚህ ውስጥ ከዩኒቨርስቲው አመራሮች በኩል የተፈጠሩትን ችግሮች በውይይት እና ቁርጠኝነት ለመፍታት ቅንነት እንደሌለ መረዳት እንችላለን። ስለሆነም ለ19 ወራት ያክል ሕገ- መንግስታዊ መብቶችን በመጣስ በወጣ መመሪያ ምክንያት ሲፈፀሙ የነበሩ የመብት ጥሰቶች እንዳልተፈቱ እና መፍትሔ እንዳልመጣ ሁሉም አካል ሊያውቅ ይገባል። ዘላቂ መፍትሔ በአጭር ሰዓት መጥቶ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ያበቃ ዘንድ ሁላችሁም በያላችሁበት በዱዓ ታስታውሱን ዘንድ አደራችን ነው። ስለሆነም፦
ለፌደራል መጅሊስ፦ የተጀመረውን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ አጠናክሮ በመቀጠል በጥቂት ቀናት ውስጥ አስተማማኝ መቋጫ እንዲሰጠው ኃላፊነቱን እንዲወጣ በድጋሚ እንጠይቃለን።
ለመንግስት ተቋማት፦ ከዚህ በፊት የችግሩን ጥልቀት ገልፀን የመፍትሔ አካል ይሆኑ ዘንድ በደብዳቤ ያሳወቅናቸው የሰላም ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና ሌሎች ተቋማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እናሳስባለን።
ለሚዲያ ተቋማት (EBC, Fana, AMN, NBC ወዘተ)፦ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እየደረሰባቸው ስላለው በደል በመግለፅ ድምፃቸውን ለሕዝቡ በማድረስ የሚዲያ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ተሰባስበው በመሄድ የጠየቋችሁ የሚዲያ አካላት እስካሁን ላሳያችሁት ዳተኝነት ራሳችሁን እንድትፈትሹና ለፍትሕ እና ለእውነት ድምጽ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ጥያቄው የሁላችንም ነው!
ጥያቄ አለን!!
ፍትሐዊ መልስም እንፈልጋለን !!!
©aaumsu
@fivekjemaa
በአቡሳላህ የYoutube ቻናል!
እየደረሰ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት በሰፊው ተዳስሷል። https://youtu.be/sFKCw3f34yk?si=xfvvqiuADzmgt2-P ግቡና ተከታተሉ። ተደራሽ ይሆንም ዘንድ Share አድርጉ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
©aaumsu
@fivekjemaa
+1
የመዳ ወላቡ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት አስመልክቶ የአቋም መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው በሙስሊም ተማሪዎች ላይ አድልዎ የሚፈጥረው መመሪያ መውጣቱን ተከትሎ የደረሰው እንግልት አግባብነት እንደሌለው በመግለፅ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ በማየት እና ጣልቃ በመግባት የሐይማኖት ነፃነት መብትን ያስከብር ዘንድ ጠይቋል።
፨ ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ተማሪዎች ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው። ጥያቄው በሰብዓዊ መብቶች መረጋገጥ የሚያምን ሰብዓዊ ፍጡር ሁሉ ነው። ስለእስልምና ብዙ በተከፈለበት ባሌ ከሚገኘው መዳወላቡ ዩኒቨርስቲ ጀመዓ መግለጫም የተረዳነው ይህንን ነው። የአንድ ሙስሊም ጉዳይ የሁሉም ሙስሊም ነውና በዚህ ልክ እንድንቆም ሆነናል። አልሐምዱሊላህ!
ጥያቄያችን ጨቋኙ መማሪያ ይሻሻል ነው። ጥያቄያችን መመሪያው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለ19 ወራት ያክል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እንግልት የፈፀመው በዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው የዩኒቨርስቲው አመራር በሕግ አግባብ ይጠየቅ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
AAU፦ ኒቃብሽን አውልቂ
ተማሪዋ፦ አላወልቅም። ለምን አውልቂ እንዳልክ ግን ጥያቄ አለኝ!!
ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን ተከትሎ የሙስሊሞች ማንነት እና ክብር የሆነውን ኒቃብ ከመማር ማስተማር እና አገልግሎት ጋር ይጋጫል በማለት ይከለከል ዘንድ መመሪያ አውጥተው ላለፉት 19 ወራት ያክል በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ ግፍ እና በደል ተፈፅሟል።
ኒቃቢስት ተማሪዎችም ባለፉት 19 ወራት ውስጥ የደረሰባቸውን በደል በሙባረክ ፖድካስት በዝርዝር አቅርበዋል። ግቡና ተመልከቱት። ድምጿ ይሰማ ዘንድም ለሁሉም አሰራጩት።
ሊንኩ https://youtu.be/CuafDziz2ss?si=OIJeGNwIgQWhpxOW ነው።
ጥያቄያችን ለዚህች ልጅ እምባ መፍሰስ መሠረቱን የጣለው መመሪያ ይሻሻል ነው። ጥያቄያችን ለዚህች ተማሪ እምባ መፍሰስ ምክንያት የሆነው የዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ አመራር ተጠያቂ ይሁን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
