es
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Canal cerrado
1 148
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
-1930 días
Archivo de publicaciones
photo content
+4

የተፈሪ መኮነን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ የመረብ ኳስ ቡድን ዋንጫ አነሳ። ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም 15ኛዉን የቴ/ሙ ሳምንት ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ስራ እና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት እየተካሄደ በነበረዉ ስፖርታዊ ዉድድር የተፈሪ መኮነን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ የሰራተኞች የመረብ ኳስ ቡድን ዋንጫ አንስቷል። በዛሬዉ ዕለት በጃንሜዳ ሁለገብ የስፖርት ማዘወተሪያ በተካሄደዉ የፍጻሜ ጨዋታ የተፈሪ መኮነን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ የመረብ ኳስ ቡድን የካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅን 2 ለ 0 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ  የዋንጫ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል። ጠንካራ ተፎካካሪዎች በነበሩበት በዚህ ዉድድር የተፈሪ መኮነን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ የመረብ ኳስ ቡድን በጥሎ ማለፍ አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለዋንጫ ጨዋታ የደረሰ ሲሆን በፍጹም የጨዋታ የበላይነት የካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅን በማሸነፍ ዋንጫዉን የግሉ አድርጓል ሲሉ መረጃዉን የሰጡን የቡድኑ አስተባባሪ አቶ አለባቸዉ ዘዉዱ ገልጸዋል ። የኮሙኒኬሽን ክፍላችን ለኮሌጃችን የመረብ ኳስ ቡድን ተጨዋቾች እንደዚሁም ለሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በተገኘዉ ድል እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን ። የተፈሪ መኮነን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

photo content

photo content
+3

የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ ኮሌጅ የስነ ምግባር እና ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት የተለያዪ ተግባራትን እያከናወነ ነዉ። ሰኔ 04 ቀን 2017  ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስነ ምግባር እና ፀረ - ሙስና ኮሚሽን የቂርቆስ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የስነ ምግባር እና ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ በመገኘት የተማሪዎች የክበባት እንቅስቃሴን ጎበኘ። በልምድ ልዉዉጡ የክበባት ፣ የቢሮ አደረጃጀት ፣ የሰራተኛዉ እና የአስተዳደሩ መልካም ግንኙነት ፣ የበጀት አጠቃቀም እና የመሳሰሉት ጉዳዮች የተጎበኙ ሲሆን የቂርቆስ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የስነ ምግባር እና ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ቆይታቸዉ የተሻለ ተሞክሮ እንዳገኙ ለማወቅ ተችሏል። በተያየዘም የኮሌጃችን የስነ ምግባር እና ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስነ ምግባር እና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር የስራ ላይ ስነ ምግባር (code of conducts) ስልጠና አዘጋጀ። ስልጠናዉ የተሰጠው ለተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኞች ሲሆን አላማዉም የስራ ላይ ስነምግባርን ግንዛቤ በመፍጠር ለዉጤታማነት መትጋት ነዉ ሲሉ መረጃዉን የሰጡን አቶ መከታዉ ሹመት የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስነምግባር እና ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት ተወካይ ለክፍላችን ገልጸዋል ። ስልጠናው በነቃ ተሳትፎ የተካሄደ ሲሆን የሰራተኛዉን የግንዛቤ አድማስ እንዳሰፋ ተገልጿል። በቀጣይ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስነ ምግባር እና ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት ተከታታይ ስልጠናዎችን እንደሚያዘጋጅ ተገልጿል። የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content

ግንቦት 3/2017 ዓ.ም ከድጋፍ ሰጪ/የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር ውይይት ተካሄደ። የበቃ ሲቪል ሰርቫንት በሚል ርዕስ ትኩረቱን ያደረገው ውይይት በከተማችን ያለውን የልማት እንቅስቃሴ ፣ የአገልግሎት
+5
ግንቦት 3/2017 ዓ.ም ከድጋፍ ሰጪ/የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር  ውይይት                             ተካሄደ። የበቃ ሲቪል ሰርቫንት በሚል ርዕስ ትኩረቱን ያደረገው ውይይት በከተማችን ያለውን የልማት እንቅስቃሴ ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የሲቪል ሰርቫንቱን አስተዋጽኦ የዳሰሰ ሲሆን አሁናዊ ሁኔታውን በመገምገም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫውን አመላክቷል ። ትኩረት ያሻቸዋል የተባሉ ጉዳዮችን ደግሞ የፈፃሚውን አቅም ብቃት መገንባት፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን መጠቀም ፣ ብልሹ አሰራርን እና ሌብነትን አጥብቆ መታገል፣ ጠንካራ የተጠያቂነትን ስርዐት ማጎልበት ፣ ብቃትንና ውጤትን መሠረት ያደረገ የደረጃ እድገትን መተግበር፣ የእውቅናና ሽልማትን ስርዓትን አጠናክሮ መቀጠል እንደዚሁም የዲገጂታልና አንድ  ማዕከል አገልግሎትን ተግባራዊ ማድረግ መሆናቸውን ማብራሪያውን የሰጡት ዶ/ር ጀማሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ በቴሌቪዥን መስኮት ተናግረዋል። - ሰራተኛው በከተማ አስተዳደሩ የተጀመሩ የልማት ስራዎች አንዲጠናቀቁ የራሱ አስተዋጽኦ ማድረግ። -በግልጸኝነትና በፍትሃዊነት ማገልገል -በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣን አገልግሎት መስጠት። - መንግስትም የበቃ ሲቪል ሰርቪስ እንዲፈጠር ይሰራል ። በመጨረሻም ከቤቱ ለተነሱ ሐሳብ አስተያየትና ጥያቄ  በአወያዮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል ።   የISO ምዘናን አሰመልክቶ አቅጣጫ ተሰጥቷል።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የእግር ኳስ  ቡድን አሸነፈ። ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም 15ኛዉን የቴ /ሙ ሳምንት ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ባዘጋጀዉ ስፖርታዊ ዉድድር በዛሬዉ እለት በምስራቅ አጠቃላይ ፖ/ቴ /ኮሌጅ ሜዳ በተደረገዉ የእግር ኳስ ጨዋታ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ቡድን የአቃቂ ፖ/ቴ/ኮሌጅ አቻዉን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ዉጤት አሸንፏል። ለተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ቡድን ሚኪያስ አደፍርስ  ሁለት ጎል ሲያስቆጥር ፣  ስመኝ ሚዲቅሳ ፣ መስከረም መስኩ እና ሀብታሙ ተፈራ  ደግሞ የቀሩትን  ጎሎች   አስቆጥረዋል። በተያያዘ ዜና የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች የእግር ኳስ ቡድን ከአቃቂ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች የእግር ኳስ ቡድን ጋር ባደረገዉ ጨዋታ 8 ለ 1 በሆነ ሰፊ ዉጤት ተሸንፏል። በቀጣይ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የሰራተኞች የእግር ኳስ ቡድን ከምስራቅ አጠቃላይ ፖ/ቴ /ኮሌጅ ጋር የሚጫወት ሲሆን የኮሌጁ ስፖርት አፍቃሪያን በእለቱ በመገኘት ቡድን እንዲያበረታቱ መረጃዉን ለክፍላችን የሰጡት የቡድኑ አስተባባሪ አቶ ሸዋንዳኝ እሸቴ  ጥሪ አስተላልፈዋል ። የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የእግር ኳስ  ቡድን አሸነፈ። ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም """"""======="""""""" 15ኛዉን የቴ /ሙ ሳምንት ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ባዘጋጀዉ ስፖርታዊ ዉድድር በዛሬዉ እለት በምስራቅ አጠቃላይ ፖ/ቴ /ኮሌጅ ሜዳ በተደረገዉ የእግር ኳስ ጨዋታ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ቡድን የአቃቂ ፖ/ቴ/ኮሌጅ አቻዉን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ዉጤት አሸንፏል። ለተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ቡድን ሚኪያስ አደፍርስ  ሁለት ሀለት ጎል ሲያስቆጥር ፣  ስመኝ ሚዲቅሳ ፣ መስከረም መስኩ እና ሀብታሙ ተፈራ  ደግሞ የቀሩትን  ጎሎች   አስቆጥረዋል። በተያያዘ ዜና የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች የእግር ኳስ ቡድን ከአቃቂ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች የእግር ኳስ ቡድን ጋር ባደረገዉ ጨዋታ 8 ለ 1 በሆነ ሰፊ ዉጤት ተሸንፏል። በቀጣይ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የሰራተኞች የእግር ኳስ ቡድን ከምስራቅ አጠቃላይ ፖ/ቴ /ኮሌጅ ጋር የሚጫወት ሲሆን የኮሌጁ ስፖርት አፍቃሪያን በእለቱ በመገኘት ቡድናቸዉን እንዲያበረታቱ መረጃዉን ለክፍላችን የሰጡት የቡድኑ አስተባባሪ አቶ ሸዋንዳኝ እሸቴ  ጥሪ አስተላልፈዋል ። ጌታቸዉ ወርቁ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content
+1

ግንቦት 26/2017ዓ.ም ከካምፓኒ ባለቤቶች እና ኢንተርፕራይዝ ተወካዮች ጋር  የምክክር መድረክ ተካሄደ። በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የውይይት መድረኩን ዓላማ በመግለጽ መድረኩን ለአቅራቢው አቶ ሙሉጌታ ጋሻው አስተላልፈዋል ። አቅራቢው የትብብር ስልጠና ምንነት፣ የትብብር ስልጠና ሞዳሊቲ፣የትብብር ስልጠና አስፈላጊነት፣በትብብር ስልጠና ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች  ፣ የትብብር ስልጠና ለኢንደስትሪው ፣ለሠልጣኙ እና ለኮሌጁ ያለው ጠቀሜታ እንዲሁም የትብብር ስልጠና አይነቶች በሰፊው ቀርቧል። በመቀጠልም በቀረበው ገለጻ  መነሻነት ኢንደስትሪው ላይ ካለው አቀባበልና ግንዛቤ ከቤቱ ሃሳብ አስተያየት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል ። በቀጣይ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የኢንደስትሪ አሰልጣኞችን በማሰልጠን የጋራ ተጠቃሚነትን በማጎልበት ላይ ተጠናክሮ እንደሚሰራ ተጠቁሟል። ድርጅቶቹ የኮሌጁን ሰልጣኞች ተቀብለው በማሰልጠን ለነበራቸው አስተዋጽኦ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። በመጨረሻም በተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ጉብኝት ተደርጎ የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን