es
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Canal cerrado
1 148
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
-1930 días
Archivo de publicaciones
photo content
+9

ግንቦት19 /2017ዓ.ም የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። ለምዘና የተቀመጡት በፊኒሺንግ ትምህርት መስክ የደረጃ 4 ተመራቂ ሠልጣኞች ሲሆኑ ቁጥራቸው 4 ነው ። ምዘናው የቲዎሪ እ
+5
ግንቦት19 /2017ዓ.ም     የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ የተቋም                     ምዘና አካሄደ። ለምዘና የተቀመጡት በፊኒሺንግ ትምህርት መስክ የደረጃ 4 ተመራቂ ሠልጣኞች ሲሆኑ ቁጥራቸው 4  ነው ። ምዘናው የቲዎሪ እና የተግባር ን አጣምሮ የያዘ ሲሆን በምዘናው ብቁ ሆነው የተገኙ ሠልጣኞች ስልጠናቸውን አጠናቃቂዎች ሲሆኑ ብቁ ያልሆኑ ሰልጣኞች ክፍተታቸውን መሠረት ያደረገ ስልጠና በመስጠትና በማብቃት ዳግም ለምዘና ይቀመጣሉ በማለት መረጃውን ያጋሩን የስልጠና ዘርፉ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ያለምወርቅ በቀለ ናቸው።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት 18 /2017ዓ.ም የኮሌጁ ኤስቴቲክ  ስልጠና ዘርፍ ሞዴል ምዘና ለማዘጋጀት ውይይት አካሄደ ። ተፈሪ መኰንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ  እንደ ሃገርም ሆነ በከተማችን ብቸኛ በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሚያሰለጥን ኰሌጅ ነው። ይሁን እንጂ እስከ አሁን ድረስ በዘርፉ የብቃት ምዘና አሃድ ያልተዘጋጀለት በመሆኑ ይህን ችግር ለመቅረፍና ሰልጣኞች በስታንዳርዱ መሠረት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ሞዴል የምዘናው  በዘርፉ አሠልጣኞች እንዲዘጋጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት አሰልጣኞች በየዘርፋቸው ደረጃውን የጠበቀ  ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጁ ከስምምነት ተደርሷል ። ምዘና የሚዘጋጅላቸው ዘርፎች ቲያትር፣ስነ-ቅብ፣እግርኳስ እና የሙዚቃ መሳሪያ የሰልጠና መስኮች ናቸው ። የተቀሩት ስልጠና የሚሰጥባቸው መስኮች ኪነ-ቅርጽ፣  ግራፊክስ እና ቮካል በተመሳሳይ በቀጣይ እንደሚዘጋጅላቸው የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዊንታና ንጉሴ መረጃውን አጋርተውናል ። ዘርፉ እስከ አሁን ድረስ የምዘና ቱል ያልተዘጋጀለት በመሆኑ አሠልጣኞቹም ሆነ ሠልጣኞች ምዘና ሳይመዘኑ የቆዩ ቢሆንም ይህንን ለማስተካከል ይረዳ ዘንድ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በሰጠው አቅጣጫ የደረጃ 4 የተቋም ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጁ ከስልጠና ዘርፉ አሰልጣኞች ጋር ውይይት ተካሂዷል። ውይይቱን የመሩት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በተሰጠን አቅጣጫ መሠረት በጥራት እና በተቀመጠለት ጊዜ  ማጠናቀቅ እና መመዘን አለብን ብለዋል።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት 21/2017ዓ.ም በኢትዮ ኮደር የኦን ላይን ስልጠና ሂደት ሰፊ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ በሃገር ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶበት እየተሰራበት ያለውን ኢትዮ ኮደር የኦ
+5
ግንቦት 21/2017ዓ.ም በኢትዮ ኮደር የኦን ላይን ስልጠና ሂደት ሰፊ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ  በሃገር ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶበት እየተሰራበት ያለውን ኢትዮ ኮደር የኦን ላይን ስልጠና የማጠናከሪያ መድረክ ተካሄደ። ሠልጣኞች ይህ በሃገር ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶበት እየተሰራ ያለው ኢትዮ ኮደር የኦን ላይን ስልጠና በኮሌጅ ደረጃ እስከ አሁን  በሠልጣኞች እየተተገበረ ያለውን መረጃ የተገለጸላቸው ሲሆን ስልጠናው  በአራቱም ዘርፎች አሊያም በመረጡት ዘርፍ በመሠልጠን የተለያዩ ተጨማሪ ስራዎችን ለማከናወን እና ተጨማሪ ስራ ለመፍጠር ዝግጁ መሆን እንደሚገባቸው ሰፊ ገለፃ ተደርጓል። በተያያዘም ሠልጣኞች  ከቀረቡት ዘርፎች በመረጡት መስክ በያዙት ስማርት ስልክ የማስጀመር  መርሀ ግብር  ተካሂዷል። ስማርት ስልክ ለሌላቸው ሠልጣኞች  በአይስቲ ስልጠና ዘርፍ በተዘጋጀው  ሾፕ ስልጠናውን መጀመር እንደሚችሉ የስልጠናንና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን  አቶ ደመላሽ ተስፋዪ ጠቁመዋል ። በተመሳሳይ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ስልጠናው በጥብቅ ዲሲፕሊን እንደሚመራ በመግለጽ ሠልጣኞ በመረጡት ዘርፍ  እንዲከታተሉ  መረጃውን አጋርተዋል።                       ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት 18 /2017ዓ.ም የኮሌጁ ኤስቴቲክ  ስልጠና ዘርፍ ሞዴል ምዘና ለማዘጋጀት ውይይት አካሄደ ። ተፈሪ መኰንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ  እንደ ሃገርም ሆነ በከተማችን ብቸኛ በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሚያሰለጥን ኰሌጅ ነው። ይሁን እንጂ እስከ አሁን ድረስ በዘርፉ የብቃት ምዘና አሃድ ያልተዘጋጀለት በመሆኑ ይህን ችግር ለመቅረፍና ሰልጣኞች በስታንዳርዱ መሠረት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ሞዴል የምዘናው  በዘርፉ አሠልጣኞች እንዲዘጋጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት አሰልጣኞች በየዘርፋቸው ደረጃውን የጠበቀ  ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጁ ከስምምነት ተደርሷል ። ምዘና የሚዘጋጅላቸው ዘርፎች ቲያትር፣ስነ-ቅብ፣እግርኳስ እና የሙዚቃ መሳሪያ የሰልጠና መስኮች ናቸው ። የተቀሩት ስልጠና የሚሰጥባቸው መስኮች ኪነ-ቅርጽ፣  ግራፊክስ እና ቮካል በተመሳሳይ በቀጣይ እንደሚዘጋጅላቸው የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዊንታና ንጉሴ መረጃውን አጋርተውናል ። ዘርፉ እስከ አሁን ድረስ የምዘና ቱል ያልተዘጋጀለት በመሆኑ አሠልጣኞቹም ሆነ ሠልጣኞች ምዘና ሳይመዘኑ የቆዩ ቢሆንም ይህንን ለማስተካከል ይረዳ ዘንድ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በሰጠው አቅጣጫ የደረጃ 4 የተቋም ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጁ ከስልጠና ዘርፉ አሰልጣኞች ጋር ውይይት ተካሂዷል። ውይይቱን የመሩት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በተሰጠን አቅጣጫ መሠረት በጥራት እና በተቀመጠለት ጊዜ  ማጠናቀቅ እና መመዘን አለብን ብለዋል።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

photo content

ግንቦት /2017ዓ.ም ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኰሌጅን የማስተዋወቅ ሥራ ተካሄደ። የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ስራ ዓለም ለመሸጋገር ይረዳቸው ዘንድ ስልጠና መውሰድ የሚኖረውን ጠቀሜታ ቢረዱም የት ቦታ እና ምን ዓይነት ስልጠና የሚለው ላይ ያላቸውን ተግዳሮት ለመቅረፍ እንዲችሉ ኰሌጃችን የሚሰጣቸውን የስልጠና ዘርፎች እና የስልጠና አሠጣጡን እንደዚሁም መሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶችን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተከናውኗል። ይህ የግንዛቤ መፍጠር ስራየተከናወነው በደጃዝማች ወንድይራድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲሆን STEP የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ባዘጋጀው የኤግዚቢሽን ፕሮግራም ነው ። በአንድ ወንጪፍ ሁለት ወፍ እንደሚባለው በኰሌጁ ስለሚሰጠው ስልጠና ከማስተዋወቅ በተጨማሪ በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ስልጠና ዘርፍ  ሶስት ቴክኖሎጂዎችን በኤግዚቢሽኑ አቅርበው ለመጎብኘት እድል አግኝተዋል ። አንደኛው የፈጠራ ስራ የግብርና ስራን የሚያግዝ በእርሻ መሬት ላይ እርጥበት ካለ ተጨማሪ ውኃ ወደ ሰብሉ እንዳይሄድና እርጥበት ከሌለ ደግሞ ሰብሉ ውኃ እንዲያገኝ የሚረዳ ቴክኖሎጂ እንደሆነ የፈጠሩት ባለሙያዎች ይናገራሉ ። ሁለተኛው ቴክኖሎጂ በኢንደስትሪዎች ስራዎችን ለማቅለል የሚረዳ ብልሽትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳ ጠቋሚ መሆኑን የሰሩት ባለሙያዎች ይናገራሉ ።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት /2017ዓ.ም ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኰሌጅን የማስተዋወቅ ሥራ ተካሄደ። የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ስራ ዓለም ለመሸጋገር ይረዳቸው ዘንድ ስልጠና መውሰድ የሚኖረውን ጠቀሜታ ቢረዱም የት ቦታ እና ምን ዓይነት ስልጠና የሚለው ላይ ያላቸውን ተግዳሮት ለመቅረፍ እንዲችሉ ኰሌጃችን የሚሰጣቸውን የስልጠና ዘርፎች እና የስልጠና አሠጣጡን እንደዚሁም መሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶችን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተከናውኗል። ይህ የግንዛቤ መፍጠር ስራየተከናወነው በደጃዝማች ወንድይራድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲሆን STEP የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ባዘጋጀው የኤግዚቢሽን ፕሮግራም ነው ። በአንድ ወንጪፍ ሁለት ወፍ እንደሚባለው በኰሌጁ ስለሚሰጠው ስልጠና ከማስተዋወቅ በተጨማሪ በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ስልጠና ዘርፍ  ሁለት ቴክኖሎጂዎችን በኤግዚቢሽኑ አቅርበው ለመጎብኘት እድል አግኝተዋል ። አንደኛው የፈጠራ ስራ የግብርና ስራን የሚያግዝ በእርሻ መሬት ላይ እርጥበት ካለ ተጨማሪ ውኃ ወደ ሰብሉ እንዳይሄድና እርጥበት ከሌለ ደግሞ ሰብሉ ውኃ እንዲያገኝ የሚረዳ ቴክኖሎጂ እንደሆነ የፈጠሩት ባለሙያዎች ይናገራሉ ። ሁለተኛው ቴክኖሎጂ በኢንደስትሪዎች ስራዎችን ለማቅለል የሚረዳ ብልሽትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳ ጠቋሚ መሆኑን የሰሩት ባለሙያዎች ይናገራሉ ።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት /2017ዓ.ም ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኰሌጅን የማስተዋወቅ ሥራ ተካሄደ። የ3ኛ ደረጃ ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ስራ ዓለም ለመሸጋገር ይረዳቸው ዘንድ ስልጠና መውሰድ የሚኖረውን ጠቀሜታ ቢረዱም የት ቦታ እና ምን ዓይነት ስልጠና የሚለው ላይ ያላቸውን ተግዳሮት ለመቅረፍ እንዲችሉ ኰሌጃችን የሚሰጣቸውን የስልጠና ዘርፎች እና የስልጠና አሠጣጡን እንደዚሁም መሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶችን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተከናውኗል። ይህ የግንዛቤ መፍጠር ስራየተከናወነው በደጃዝማች ወንድይራድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲሆን STEP የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ባዘጋጀው የኤግዚቢሽን ፕሮግራም ነው ። በአንድ ወንጪፍ ሁለት ወፍ እንደሚባለው በኰሌጁ ስለሚሰጠው ስልጠና ከማስተዋወቅ በተጨማሪ በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ስልጠና ዘርፍ  ሁለት ቴክኖሎጂዎችን በኤግዚቢሽኑ አቅርበው ለመጎብኘት እድል አግኝተዋል ። አንደኛው የፈጠራ ስራ የግብርና ስራን የሚያግዝ በእርሻ መሬት ላይ እርጥበት ካለ ተጨማሪ ውኃ ወደ ሰብሉ እንዳይሄድና እርጥበት ከሌለ ደግሞ ሰብሉ ውኃ እንዲያገኝ የሚረዳ ቴክኖሎጂ እንደሆነ የፈጠሩት ባለሙያዎች ይናገራሉ ። ሁለተኛው ቴክኖሎጂ በኢንደስትሪዎች ስራዎችን ለማቅለል የሚረዳ ብልሽትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳ ጠቋሚ መሆኑን የሰሩት ባለሙያዎች ይናገራሉ ።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+4

ግንቦት 15/2017 ዓ.ም ከመደበኛ የስልጠና ሰዓት ውጪ በሚሰጡ ስልጠናዎች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ። ዜጎች/ስልጠና ፈላጊዎች አመቺ በሆነ የሥልጠና ሰዓት ደረጃቸውን ለማሻሻልም ሆነ የሞያ ባለቤት እንዲ
+2
ግንቦት 15/2017 ዓ.ም ከመደበኛ የስልጠና ሰዓት ውጪ በሚሰጡ ስልጠናዎች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ። ዜጎች/ስልጠና ፈላጊዎች አመቺ በሆነ የሥልጠና ሰዓት ደረጃቸውን ለማሻሻልም ሆነ የሞያ ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን አማራጭ በማስፋት በማታው መርሐ ግብር እና በቅዳሜና እሁድ ስልጠናወችን የሚከታተሉ መሆኑ ይታወቃል። በነዚህ መርሃ ግብሮች የሚሰጡ ስልጠናዎች በተገቢው ሁኔታና ጥራት መሠጠቱን ለመከታተል የሚያስችሉ የተለያዩ ስልቶች የተቀመጡ ቢሆንም በቀጥታ ስልጠናውን ከሚሠጡ እና ከሚከታተሉ አካላት ማለትም አሠልጣኞች እና አስተባባሪዎች ጋር የጋራ ውይይት ማድረግ አንዱ ስልት በመሆኑ ውይይት ተካሂዷል ። በውይይቱ ለስራው አለመሳለጥ ምክንያት ናቸው የተባሉ አንዳንድ ርእሰ ጉዳዮችን በማንሳት ተሳታፊዎች ተወያይተዋል ። ጉዳዮችም በዋናነት ከሠልጣኞች፣ ከአሠለጣጠን ሥርዓት፣ ከአገልግሎት ክፍያ እና ተቋማዊ አሠራር ላይ ያተኮሩ እንደነበር ግንዛቤ ተወስደዋል። የዘርፉ አስተባባሪ አቶ ገዙ ኤጄሬና ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ከተሳታፊዎች ለተነሱት የመረጃ አያያዝ ፣የክፍያ ሁኔታ፣ የመንግስት ግብር ፣ የሠልጣኞች የመግቢያ ሰዓት ና የስልጠና ጥራት ጥያቄዎች በአጭር፣በመካከለኛ እና በረዥም ግዜ የሚፈቱ መሆናቸውን በማብራራት እንደየሁኔታው ምላሽ እንደሚያገኙ ገልፀዋል።              ኮሙኒኬሽን ቡድን

+3
ግንቦት 14/2015ዓ.ም አካዳሚክ ኮሚሽን እና ማኔጅመንት አባላት የጋራ የውይይት መድረክ አካሄዱ። በከተማ ደረጃ በነበረው ግምገማ የኮሌጁን እንቅስቃሴ ገምግሞ ውጤቱን አስቀምጠዋል። በዚህ ግምገማ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል ። ኮሌጁ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን ቁልፍና አበይት ተግባራት በአጠቃላይ ከKPI አንጻር  በየዘርፉ የተመዘገበው ውጤት  ተገምግሟል። በተጨማሪም የቀጣይ ስራዎች ትኩረት  ክፍተቶችን በመሙላት እና በተለዩት ተግባራት ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ ተሰጥቷል። በውይይቱ ከቤቱ የተለያዩ ሃሳብ አስተያየቶች ተሰጥተው በጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። መጨረሻም የኮሌጁ GMF ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ ወ/ሮ እታገኝ ውብሸት  ኢትዮጵያ አዘጋጅ በሆነችበት 3ኛው የምስራቅ አፍሪካ የብየዳ ውድድር ላይ ተሳትፋ አሸናፊ ሆና የሃገሯንም የኮሌጁንም ስም በማስጠራቷ ኮሌጁ እንኳን ደስ ያለሽ እንኳን ደስ ያለን ብሏታል ።             ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት 14/2017ዓ.ም የኮሌጃችን ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ በዘርፉ ተቋማዊ ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጅ ተመረጠ ። ሰልጣኞች በስታንዳርዱ መሠረት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከስልጠና
+4
ግንቦት 14/2017ዓ.ም የኮሌጃችን ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ         በዘርፉ ተቋማዊ ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጅ ተመረጠ ። ሰልጣኞች በስታንዳርዱ መሠረት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከስልጠናው ባሻገር የምዘናው ዝግጅት ወሳኝ መሆኑ እሙን ነው ። ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የነበረው ሰልጣኞችን ደረጃ በደረጃ የመመዘን እና ብቃታቸው ተረጋግጦ ወደሚቀጥለው ደረጃ እንዲሸጋገሩ የማድረግ ሂደት ለሀገር አቀፉ ምዘና ውጤታማነት እንዲረዳም  በማጠቃለያው በከተማ አቀፍ ሞዴል ምዘና ሲታገዝ ቆይተዋል ። የምዘና ውጤትን የበለጠ ለማሳደግ እንዲረዳ ከነበረው አሠራር በተጨማሪ በኮሌጆች የየስልጠና ዘርፉን ሞዴል ሆልስቲክ ምዘና አዘጋጅቶ ሰልጣኞችን መመዘን አስፈላጊ ሆኖ ተገኝተዋል። ይህ ምዘና ሠልጣኞች ለሀገር አቀፉ ምዘና ያደረጉትን ዝግጅት ለማወቅ እና  የስነ ልቦና ዝግጅት እንዲያደርጉ ለማስቻል ታሳቢ ተደርጎ እንደሚሰጥም ለማወቅ ተችሏል። በመሆኑም የተፈሪ መኰንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘርፉ በሁሉም ኮሌጆች ለሚመዘኑ ተመራቂ ሠልጣኞች የሚሆን የተቋም ሞዴል ምዘና እንዲያዘጋጅ በተሠጠው አቅጣጫ መሠረት ከስልጠና ዘርፉ አሰልጣኞች ጋር ውይይት አካሂዷል። ስልጠና ዘርፉ የመጣውን እድል በደስታ ተቀብሎ ስራውን በአግባቡ ለማከናወን ቢሟሉልን ያላቸውን ማቴሪያሎችን በዝርዝር አቅርበዋል ። በውይይቱ ማጠቃለያ የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ጥያቄውን በአወንታ ተቀብለው ለቀጣዩ ከተማ አቀፍ ሞዴል ምዘና ዝግጅት ተመረጭ እንድንሆንም ጭምር ጥሩ ዝግጅት እንደሚደረግ እምነታቸው የፀና እንደሆነ ይገልጸዋል ።                ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት 14/2017ዓ.ም የኮሌጁ የሠልጣኞች ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ክበብ አባላት የልምድ ልውውጥ አካሄዱ ። የኮሌጃችን የሠልጣኞች ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ክበብ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ቢ
+5
ግንቦት 14/2017ዓ.ም የኮሌጁ የሠልጣኞች ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ክበብ አባላት የልምድ ልውውጥ አካሄዱ ። የኮሌጃችን የሠልጣኞች ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ክበብ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ቢሆንም ለተሻለ የክበቡ እንቅስቃሴ እና ፍሬያማ ተሳትፎ ለማድረግ እንዲረዳው ልምድ መቅሰምን እና ማጋራትን ታሳቢ በማድረግ የተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ጎብኝተዋል። በዚህ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት የተወሰዱት መልካም ተመኩሮዎች እንደመሚከተለው ተዘርዝረዋል። [  ] ሠልጣኞች ዩኒፎርም የመልበስ ግዴታ እንዳለባቸው እና ትግበራው በክበቡ አባለት ክትትል እንደሚደረግበት፣ [  ] ሰንደቅ ዓላማ የመስቀል ስነ-ስርዓት በጋራ እንደሚከናወን፣ [  ] የክበቡ አባላት የተለየ ዩኒፎርም እንደሚጠቀሙ፣ [  ] በስርዓተ ጾታ ላይ ትኩረት ሰጥተው አንደሚሠሩ እና ባልተቆራረጠ ሁኔታ ስራዎችን እንደሚገመግሙ የሚሉትን ያካትታል። በመጨረሻም ከልምድ ልውውጡ የተገኙ እነኝህን ተግባራት እንደ ኮሌጁ ነባራዊ ሁኔታ ለመተግበር ያስችል ዘንድ ከስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች በቅርበት ተመካክረው እንደሚሰሩ አስተባባሪው አቶ መከታው ሹመት መረጃውን አጋርተውናል ።              ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት 13 ቀን 2017ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮሌጅን ጎበኙ። በጉለሌ ክፍለ ከተማ ከሚገኙ 2 ትምህርት ቤቶች ድል በር 2ኛ ደረጃት ት/ቤት እና እቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ትምህርት የሚማሩ ተማሪዎች በተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝቱ የቴክስታይል ጋርመንት ፣ እንጨትና ብረታ ብረት  እና  የስነ ጥበብትምህርት ክፍልን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ የታቀደው እና የተመቻቸውና በኮሌጁ የስልጠናና አከዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ሲሆን በመጋቢት 9/2017ዓ.ም በተደረሰው የጋራ ስምምነት መሠረት ባለሙያዎች  ወደ ትምህርት ቤቶቹ በመሄድ ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሂዷል ከዚሁ ጋር ተያያዥ የሆነው ተማሪዎቹ በግንዛቤ መፍጠሪያው ያደመጡትን በተግባር ኮሌጁ ላይ ስልጠና ዘርፎች ላይ ጉብኝት በማድረግ ተማሪዎቹ ስለ ቴ/ሙያ የተሟላ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል። ተማሪዎች ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት ቴክኒክና ሙያ ሲባል በዚህ ልክ የተደራጀ እና በተለያየ ዘርፍ እንደሚያሰለጥን ግንዛቤው እንዳልነበራቸው በመግለጽ አሁን በተገለጸላቸውና  እና በተለይ ባዩት ነገር በመደነቅ በቀጣይ ኮሌጁን ተቀላቅለው ለመሰልጠን እንዳነሳሳቸው እና ባዩት ነገር እንደተደሰቱ ተናግረዋል።  የድልበር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ደግሞ ጉብኝቱ በጣም ጥሩ ነው ከጠበቅኩት በላይ ሆኖ አግኝቼዋለሁኝ በቀጣይ ለሚኖረኝ ምርጫ አቅጣጫ የሚሰጥም ነው ብሏል። በተመሳሳይ አስተያየታቸውን የሰጠጡት በድል በር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር እና አስተባባሪ መምህር ----------  ኮሌጁ ከንግግር ባለፈ ቃሉን በተግባር ያሳየበት ጉብኝት በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክት አስተላልፈዋል። በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዋ/ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ትምህርታዊ ጉብኝቱ በትምህርት ተቋማት ያለዉን ግንኙነት ከማዳበሩ በተጨማሪ ተማሪዎች ወደፊት በምን ሙያ መሰልጠን እንዳለባቸው፣ መክሊታቸው ምን እንደሆነ ከወዲሁ ለመፈተሽ የሚያስችላቸው ነዉ ብለዋል። በተጨማሪም ተማሪዎቹ ከማትሪክ በኋላ ባላቸው ትርፍ ግዜ ሁሉ በኮሌጁ ተገኝተው አጫጭር ስልጠናን እንዲሰለጥኑ ሊመቻችላቸው እንደሚችልም ተጠቁሟል ።              የኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

ግንቦት12 /2016ዓ.ም የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። ለምዘና የተቀመጡት በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ በ Hardwar and Networking service 4
+4
ግንቦት12 /2016ዓ.ም የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ የተቋም                    ምዘና አካሄደ። ለምዘና የተቀመጡት በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ በ Hardwar and Networking service 41 እና በዳታ ቤዝ 72 የደረጃ 4 ሠልጣኞች  ከደረጃ 1 ወደ ደረጃ 2 ለመሸጋገር  የሚያስችላቸውን የተቋም ውስጥ ምዘና የተመዘኑ ሲሆን ምዘናው በስልጠና ክፍሉ ተዘጋጅቶና በስልጠና ዘርፉ ጸድቆ የሚሰጥ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ምዘናው በቲዎሪ እና የተግባር ምዘናን አጣምሮ የሚሰጥ ሲሆን በምዘናው ብቁ ሆነው የተገኙ ሠልጣኞች ወደቀጣዩ ደረጃ የሚሸጋገሩ ሲሆን ብቁ ያልሆኑ ሰልጣኞችን ክፍተታቸውን መሠረት ያደረገ ስልጠና በመስጠትና በማብቃት ዳግም ለምዘና እንደሚቀመጡ ለማወቅ ተችሏል። ለምዘና ከተቀመጡ 111 ተመዛኞች  95.7% ቱ  ምዘናውን በብቃት አጠናቀ ወደሚቀጥለው ደረጃ መሸጋገራቸውን የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዋ ወ /ሮ ዘውዲቱ ፀጋዬ መረጃውን አጋርተውናል።                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content