es
Feedback
Joint vision success academy 1-8

Joint vision success academy 1-8

Ir al canal en Telegram
845
Suscriptores
-224 horas
-27 días
-630 días
Archivo de publicaciones
የ2019 ዓ.ም የወላጅ መልእክት.docx0.23 KB

ቀን:- ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጉዳዩ:- የተማሪ ትራንስፖርት ይመለከታል። በትራንስፖርት ጉዳይ መረጃ የምትፈልጉ ወላጆች በዚህ ስልክ በመደወል መረጃ መግኘት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን። 👉091 205 3876 ቴዲ                                  ት/ቤቱ

የ2019 ዓ/ም ከጀማሪ እስከ 8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች የመፅሐፍ ዋጋ ዝርዝር
የ2019 ዓ/ም ከጀማሪ እስከ 8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች የመፅሐፍ ዋጋ ዝርዝር

Good News and Congratulations from Joint Vision Success Academy! 🎉🎉🎉🎉🎉🌸🌸🌸 Dear Parents and Legal Guardians of our school community, Congratulations! 🏆🎉👏 First and foremost, our entire school community gives thanks to the Almighty for bringing us to this great day. 🙏🙏🙏🙏🙏 Our 2018 E.C. ( 2025/26) University Entrance Examination, Grade 12 national exam candidates worked tirelessly day and night to achieve highly impressive results. Among the students who took the exam, 78% have passed to university with excellent scores. The rest 22% will join remedial class. Our school’s highest score is 540 out of 600, achieved by student Eyosiyas Girma. Thank you, you made us proud! 👌👏👏👏 This grand success is the result of: The immense effort of our students The continuous support of our teachers The unreserved guidance and follow-up of our parents The success of our students is the fruit of your hard work and a source of pride. Therefore, the entire Joint Vision Success Academy community wishes to say congratulations to you, and congratulations to us all, for this brilliant achievement! We sincerely wish our children a beautiful and highly successful journey in their upcoming higher education and future endeavors. 💫🌾👏👏👏👏👏🌾🌾🌾🌾 Our cooperation for knowledge; our vision for success. Joint Vision Success Academy Kabajamtoota Maatii/Guddistoota Barattoota Mana Barumsaa Keenyaa፤ Congratulations!!! 🏆🏆🏆🏆🏆🎉🎉🎉🎉🎉👏🌾🌾 Dursa hundi hawaasni mana barumsaa keenyaa guyyaa guddaa kanaaf nu geesseef Uumama galateeffata. 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 Qormaanni Biyyaalessaa Kutaa 12ffaa Bara 2018 barattoonni keenya halkan fi guyyaa cimanii hojjechuun bu'aa baay'ee gaarii galmeessaniiru. Barattoota qoraman keessaa 78% ta'an qabxii gaariin gara Yuunivarsiitiitti darban. Qabxiin mana barumsaa keenya olaanaan 540/600 yeroo ta'u, barataa Iyoosyaas Girmaatiin galmeeffame. Galatoomaa, itti gammaduu qabdu! 👌👌👌👌👌👌👌👌👌👌 Milkaa'inni guddaan kun kan argame: Carraaqqii olaanaa barattoota keenyaatiin, Deeggarsa walitti fufaa barsiisotaatiin, fi Deeggarsaafi hordoffii maatii isa hin dhumneen dha. Milkaa'inni barattoota keenyaa bu'aa hojii keessaniifi boonsaa keessaniis. Kanaafuu, bu'aa miidhagaa galmeeffameef hawaasni mana barumsaa Joint Vision Success Academy hundi "Baga gammaddan, baga nuuf gammade" jechuu ni barbaada. Jireenyi barnoota olaanaa fuulduraafi imalli borii ijoollee keenyaa caalaatti miidhagaafi milkaa'aa akka ta'u garaa guututti hawwina. 💫💫💫💫💫🌾🌾🌾🌾👏👏👏👏 Tumsi keenya Beekumsaaf፤ Mul'anni keenya Milkaa'inaaf። Joint Vision Success Academy የእንኳን ደስ አላችሁ የምስራች መልዕክት ከጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ! ክቡራን የትምህርት ቤታችን ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች፤ Congratulations!!! 🏆🏆🏆🏆🏆🎉🎉🎉🎉🎉👏🌾🌾 በመጀመሪያ መላው የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ ለዚህ ታላቅ ቀን ስላደረሰን ፈጣሪን ያመሰግናል። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ማጠናቀቂያ ፈተና ተማሪዎቻችን ሌት ተቀን በትጋት አጣምረው በመስራት እጅግ በጣም አመርቂ ውጤት አስመዝግበዋል።  ከተፈተኑት ተማሪዎች መካከል 78% ተማሪዎቻችን ወደ ዩኒቨርሲቲ በጥሩ ውጤት ያለፉ ሲሆን የቀሩት ደግሞ በሪሚድያል ይካተታሉ። የት/ቤታችን ከፍተኛ ውጤት 540/600 በተማሪ ኢዮስያስ ግርማ ነው። እናመሰግናለን ኮርቶንባሀል!!!👌👌👌👌👌👌👌👌👌👌 ይህ ታላቅ ስኬት የተገኘው፦ በተማሪዎቻችን ከፍተኛ ጥረት ፥ የመምህራን ተከታታይ እገዛ እና ባልተቆጠበ የወላጅ ድጋፍ እና ክትትል ነው። የተማሪዎቻችን ስኬት የእናንተም የስራችሁ ፍሬ እና ኩራት ነው። በመሆኑም ለተመዘገበው ደማቅ ውጤት መላው የጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ፤ ደስ አለን ለማለት ይወዳል። የልጆቻችን ቀጣይ የከፍተኛ ትምህርት ህይወት እና የወደፊት ጉዟቸው ይበልጥ ያማረና የተሳካ እንዲሆን ከልብ እንመኛለን። 💫💫💫💫💫🌾🌾🌾🌾👏👏👏👏    ትብብራችን ለእውቀት፤ ራዕያችን ለስኬት። ጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ

Repost from Yeka Education
🥏" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት 🥏የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ው
🥏" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት 🥏የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። 🥏በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች  ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። 🥏በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል። 🎾ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የ
+1
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች  ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል። ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

የቅድመ መደበኛ እና የአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ የተማሪ መፅሐፍ ስለመጣ ከሐሙስ ፣ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም ጀምራችሁ ከ አንደኛ ደረጃ ግቢ ግዢ መፈፀም ትጅላላችሁ። የመፃህፍት አጠቃላይ ዋጋ በየክፍሉ ነገ እንለጥፋለን።

ለ እስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501 ኛው የነብዩ ሙሃመድ የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ🙏 መልካም በአል ይሁንላችሁ!
ለ እስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501 ኛው የነብዩ ሙሃመድ  የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ🙏 መልካም በአል ይሁንላችሁ!

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል።
ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው። ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው። ቲክቫህ
ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው። ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል። ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚ
+1
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል። ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

በጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ90 ቀን ዕቅድ አንዱ አካል የሆነውን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክረምት ትምህርታቸውን ማጠናቀቂያ የማጠ
+8
በጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ90 ቀን ዕቅድ አንዱ አካል የሆነውን  የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክረምት ትምህርታቸውን ማጠናቀቂያ የማጠቃለያ ፈተና ሲፈተኑ።

በጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ90 ቀን ዕቅድ አንዱ አካል የሆነውን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክረምት ትምህርታቸውን ማጠናቀቂያ የማጠ
በጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ90 ቀን ዕቅድ አንዱ አካል የሆነውን  የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክረምት ትምህርታቸውን ማጠናቀቂያ የማጠቃለያ ፈተና ሲፈተኑ።

Summer exam schedule
Summer exam schedule

የ2018 ዓ.ም የክረምት ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ማክሰኞ ፣ ነሐሴ 12 እና ሐሙስ 14/2018 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን በዚህ መርሐግብር እንድትዘጋጁ በትህትና እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ:- 👉 ረቡዕ፣ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም ትምህርት ዝግ ሲሆን ዓርብ፣ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም ደግም የፈተና ወረቀት ለተማሪዎች ይመለሳል። ት/ቤቱ

የሁለተኛ ደረጃ የተማሪዎች ምዝገባ ሙሉ በሙሉ የጨረስን መሆኑ እናሳውቃለን።              ት/ቤቱ

ጎበዝ ተማሪ የመሆን ዋና ዋና አበይት ነጥቦች ጎበዝ እና ውጤታማ ተማሪ መሆን ድንገት የሚመጣ አጋጣሚ ሳይሆን፣ የትክክለኛ ልማዶች፣ የጽናት እና የጥሩ ስልት ውጤት ነው። ​በጥናት እና በተግባር የተረጋገጡ ጎበዝ ተማሪ የመሆን ዋና ዋና ሚስጥሮች የሚከተሉት ናቸው። ​1. የማጠናት ስልትን ማሻሻል (Smart Study)በሰንጠረዥ ማናት (Time Blocking): ዋና ዋና የሚባሉትን አበይት ነጥቦች እጥር ምጥን ባለ መልኩ ለይቶ ማውጣት በየቀኑ ለጥናት የሚሆን የተወሰነ ሰዓት መመደብ፤ በጥናት መካከልም አጭር የዕረፍት ጊዜ መውሰድ(ለምሳሌ፦ 25 ደቂቃ አጥንቶ ለ5 ደቂቃ) ማረፍ። ​ንቁ ተሳትፎ (Active Recall): ማንበብ ብቻ በቂ አይደለም። ያነበብነውን መጽሐፍ ዘግተን "ምን ተረዳሁ?" ብለን ራሳችንን መጠየቅ፣ ወይም ማስታወሻ ሳናይ ራስን መፈትን። ​ለሌላ ሰው ማስረዳት (Feynman Technique): ያጠናነውን ርዕስ ለጓደኛችን ወይም ለራሳችን በቀላል ቋንቋ ለማስረዳትም ሆነ ለመረዳት መሞክር። ጽንሰ-ሐሳቡን ምን ያህል ጠልቀን መረዳታችንን ለማወቅ የተሻለው መንገድ ይህ ነው። ​2. ክፍል ውስጥ ንቁ መሆንከፊት መቀመጥና ማስታወሻ መያዝ: ባብዛኛው የምንረዳው ክፍል ውስጥ እንደመሆኑ መጠን አስተማሪው የሚናገረውን/የሚያስረዳውን  በአጭር በአጭሩ መያዝ። ​ጥያቄ መጠየቅ: ያልገባንን ነገር ወዲያውኑ አስተማሪያችንን ወይም ጓደኞቻችንን ጠይቀን መረዳትና የሚጠየቁ ጥያቄዎችን አለማከማቸት። ​3. ጊዜን በአግባቡ መያዝ (Time Management)ዛሬ የሚሰራውን ለነገ አለማስተላለፍ: የቤት ሥራዎችን፣አሳይመንቶችንና እና ፕሮጀክቶችን በተሰጠው ቀን መጀመርና ሰርቶ ማጠናቀቅ ከፈተና በፊት የሚፈጠርን ጭንቀት ይቀርፋል። ​ቅደም ተከተል ማውጣት: አስቸጋሪ ወይም ትኩረት የሚሹ ትምህርቶችን አእምሯችን ሳይደክም ጠዋት ወይም በጥናታችን መጀመሪያ ላይ ማጠናቀቅ። ቤተ መፅሀፍ ገብተን የምናነብበትን ጊዜ፣ የተለያዩ ትምህርቶችን መለማመጃ/መዘጋጃ ጥያቄዎችን የምንሰራበትን ጊዜ መመጠን ይኖርብናል። ​4. የአኗኗር ዘይቤ እና የአእምሮ ዝግጅትበቂ እንቅልፍ ማግኘት: አእምሮ ያጠናውን ነገር መዝግቦ የሚይዘው እና የሚያድሰው በእንቅልፍ ወቅት ነው (በቀን ከ7–8 ሰዓት እንቅልፍ አስፈላጊ ነው)። ​ጤናማ ምግብ እና እንቅስቃሴ: የተመጣጠነ ምግብ መመገብና አካላዊ ጤንነት ለንቁ አእምሮ መሰረት ናቸው። ​አዎንታዊ አስተሳሰብ (Growth Mindset): "አልችልም" ከማለት ይልቅ "በደንብካጠናሁና ከተለማመድኩ እችላለሁ" የሚል እምነት ሊኖረን ይገባል። በአጠቃላይ ጎበዝ ተማሪ ማለት በቀን 24 ሰዓት የሚያጠና ሳይሆን፣የሚያጠናበትን ሰዓት በአግባቡና በትኩረት የሚጠቀም ነው።

ቀን፡ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም አስቸኳይ መልዕክት ለ ወላጆች፡- 🔕🔔🔔🔔🔔🔕📣📣📣📣 ከሰኞ፣ ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ ተማሪዎች ስለምንቀበል ዘግይተው የሚመጡ ነባር ተማሪዎች የክፍል ምጣኔ ቢሞላ ት/ቤቱ ሐላፍነት የማይወስድ ሲሆን፤ እስከ ቅበላ አቅም ድረስ የነባር ተማሪዎች ምዝገባ በአንድ ተማሪ በቀን 30 ብር ቅጣት የሚያስቀጣ በመሆኑ፣ እስከ አሁን ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች ቀድማችሁ እንድታስመዘግቡ ከወዲሁ እናሳስባለን።                                                  ት/ቤቱ Date: August 3, 2026 Urgent Message to Parents: We will start accepting new students on Monday, August 10, 2026. Therefore, the school will not take responsibility for returning students who arrive late if the class capacity is full. Furthermore, until the enrollment capacity is reached, registration for returning students will incur a late penalty of 30 Birr per day per student. We strongly advise parents who have not yet registered their children to do so in advance.                                                   The School

The four pillars of education (አራቱ የትምህርት አምዶች) 📚📚📚📚 ✍️ 1. ለማወቅ መማር ✍️  2. ለመሥራት መማር ✍️ 3. አብሮ ለመኖር መማር ✍️ 4. ለመሆን መማር 📚 የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) በጃክ ዴለርስ በሚመራው ኮሚሽን አማካኝነት የዘረጋቸው  አራቱ የትምህርት አምዶች (Four Pillars of Education) ለ21ኛው ክፍለ ዘመን ትምህርት መሠረት ናቸው። 👉  እነዚህ አምዶች ትምህርት ዕውቀትን ብቻ ሳይሆን፣ ክህሎትንና ስብዕናን ማዳበር እንዳለበት ያመለክታሉ።(Skill plus Attitude) ✍️ 1. ለማወቅ መማር (Learning to Know) ይህ አምድ ትኩረት የሚያደርገው መሠረታዊ ዕውቀትን ከማግኘት ባለፈ፣ እንዴት መማር እንዳለብን መማር (Learning how to learn) ላይ ነው። 🎯 ዋና ዓላማ 🕯 ተማሪዎች ዓለምን እንዲረዱ፣ የማወቅ ጉጉታቸውን እንዲያሳድጉ እና የማስታወስ፣ የማሰብ እንዲሁም የማተኮር ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ ማስቻል።   🔑 ቁልፍ ነጥብ 👉 ዕውቀት በየጊዜው ስለሚለወጥ፣ አንድ ተማሪ በራሱ አዳዲስ መረጃዎችን የመፈለግና የመረዳት ፍላጎት እንዲኖረው ማድረግ ነው። ✍️  2. ለመሥራት መማር (Learning to Do) ዕውቀትን ወደ ተግባር መለወጥ ላይ ያተኩራል። ይህም ተማሪዎች የተማሩትን ነገር በተግባራዊ ሕይወታቸውና በሥራ ዓለም ላይ እንዲጠቀሙበት ያዘጋጃቸዋል። 🎯ዋና ዓላማ 🕯የሙያ ክህሎትን ማዳበር ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ችግር ፈቺነት፣ ከሰዎች ጋር በቡድን የመሥራት ብቃት እና በሥራ ላይ የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን የመቋቋም ችሎታን ማዳበር ነው።   🔑 ቁልፍ ነጥብ 👉 በአሁኑ ዘመን "ለመሥራት መማር" ሲባል በእጅ ከሚሠራ ሥራ (Manual Labor) ባለፈ፣ መረጃን የመተንተንና የፈጠራ ሥራዎችን የመሥራት ብቃትን ይጨምራል። ✍️ 3. አብሮ ለመኖር መማር (Learning to Live Together) ይህ አምድ በዘመናዊው ዓለም ውስጥ እጅግ አስፈላጊው እንደሆነ ይታመናል። ትኩረቱም በሰዎች መካከል ሰላምን፣ መቻቻልንና መግባባትን መፍጠር ነው። 🎯ዋና ዓላማ 🕯 የሌሎችን ታሪክ፣ ባህልና እሴት ማክበር፣ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እና የጋራ ግቦችን ለማሳካት በጋራ መሥራትን መልመድ ነው።   🔑 ቁልፍ ነጥብ 👉 በትምህርት ቤት ውስጥ የሚከናወኑ የቡድን ሥራዎችና ውይይቶች ለዚህ አምድ ተግባራዊነት ትልቅ ድርሻ አላቸው። ✍️ 4. ለመሆን መማር (Learning to Be) ይህ አምድ የሰውን ልጅ ሁለንተናዊ ዕድገት (Physical, Intellectual, Emotional, and Spiritual) የሚመለከት ነው። 🎯ዋና ዓላማ 🕯 እያንዳንዱ ግለሰብ የራሱ የሆነ ነፃነት፣ የማመዛዘን ችሎታ፣ የሥነ-ምግባር ጥንካሬ እና ኃላፊነት እንዲኖረው ማድረግ ነው። 🔑 ቁልፍ ነጥብ 👉  ትምህርት የአንድን ሰው የተደበቀ ተሰጥኦ (Potential) አውጥቶ ለራሱና ለማኅበረሰቡ የሚጠቅም ሙሉ ሰው እንዲሆን መርዳት አለበት። ባጭሩ፦ ✍️✍️✍️✍️ እነዚህ አራቱ አምዶች እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ናቸው። ለማወቅ መማር  መሣሪያ ሲሆን፣ ለመሥራት መማር  ተግባር ነው፣ አብሮ ለመኖር መማር ማኅበራዊ መሠረት ሲሆን፣ ለመሆን መማር ደግሞ የሦስቱም የመጨረሻ ውጤት ወይም ድምር ነው። @Lifelong learner 🎯📌👇 Bloom's taxonomies of education 1.Cognitive domain (Knowledge/HEAD) 2.Affective domain (Attitude /HEART) 3.Psychomotor domain (Skill/HAND)