es
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Ir al canal en Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

Mostrar más
3 584
Suscriptores
Sin datos24 horas
-57 días
+5330 días
Archivo de publicaciones
ግልፅ የ ጨረታ ማስታወቂያ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏
ቁጥር 002/2017 በደቡብ ምዕ/ኢት/ሕ ክልላዊ መንግስት በካፋ ዞን በሺሾ እንዴ ወረዳ የዲንቢራ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት በ2017 በጀት ዓመት አዲስ የመሥሪያ ቤት ግንባታ ሥራ ለማሠራት ስለፈለገ መ/ቤታችን የደረጃ 8 እና ከዚያ በላይ ብቃት ማረጋገጫ ያላቸውን ህጋዊ የግንባታ ሥራ ድርጅቶችን አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት ተጫራቾች /ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች የተዘረዘረሩ መስፈርቶችን ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ 1. የተጨማሪ እሴት ታከስ ተመዝጋቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ 2. የአቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡ 3. የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር/tax payer identification number/ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ 4. የዘመኑን ግብር ስለመከፈላቸው ማስረጃ አያይዞ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ 5. በዘመኑ የታደሰ /የንግድ ሥራ ፍቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ 6. የንግድ ምዝገባ ምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ሆኖ ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ የሥራ ቀናት ክፍት ሆኖ ስለሚቆይ ተጫራቾች የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ውን ሠነድ የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ /ብቻ እየከፈሉ ከሺሾእንዴ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 05 ዘወትር በሥራ ሰዓት‍‌‌‌‍‍‍‍‌‌‍‍‍‌‍‌‍ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ ፡፡ 7. ተጫራቾች የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ውን መወዳደሪያ ቴክኒካልና ፋይናንሻል መረጃዎችን በታሸገ ኤንቨሎፕ ለእያንዳንዱ ሰነድ ቢያንስ 2/ሁለት/ ኮፒ በማድረግ በካፋ ዞን ሺሾእንዴ ወረዳ ፋይ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 05 ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ ሣጥን ውስጥ ያስገባሉ፡፡ 8. እያንዳንዱ ተጫራች የሚያቀርባቸው ሙሉ መረጃዎች ቅጂ ሲደረጉ በሚገባ የሚነበቡ እና ቀድሞ የተሞላው ዋናው ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበትን ግልጽ የሆነ መረጃ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ከስራ ፍቃዳቸውና ከተዛማጅ ውጭ መወዳደር አይቻልም ፡፡ 9. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ ብር 50,000 /ሃምሣ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ብቻ በማድረግ በሺሾ እንዴ ወረዳ ፋይ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ሥም አሠርተው የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ ማስከበሪያ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡ 10.የቀረቡ የመወዳደሪያ ፖስታዎች በ22ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወህጋዊይም ህጋዊ ተወካዮቻቸው በተገኙበት ታሽጎ በታሸገበት ዕለት ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል ለዚህም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካዮቻቸው ያለመገኘት የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ውን የመክፈት ሂደት አያስተጓጉልም:: 11. የጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ መዝጊያና መክፈቻ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡– መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‏ውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡– በስልክ ቁጥር 0476 680 377 በመደወል መረዳት ይቻላል፡፡ በደቡብ ምዕ/ኢት/ሕ/ክልላዊ መንግስት በካፋ ዞን የሺሾ እንዴ ገንዘብ ጽ/ቤት

የደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይ ጠበቆች የ2016 በጀት ዓመት ግብርን አከፋፈል አስመልክቶ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በቀን 27/12/2016 ዓ.ም የፃፈዉ ደብዳቤ lawethiopiacomment

NEW VACANCY
🚧United Real Estate PLC   United Real Estate PLC would like to invite qualified good and interested job seekers to apply for the following vacant positioned   Position 1: Store Keeper   Job Requirement Required Education BA Degree/ Diploma from recognized institutions in purchasing & supplies, procurement, Accounting, Business Management or related fields, introductory computer skills is required Experience 2/4 years in analogous positions, construction work experience is preferable   Qty 2 Place of work Head office   Position 2: Marketing, Sales & Customer Service Head   Job Requirement Required Education MBA/ BA Degree in Marketing, Business Administration, or in a related fields with applicable work experience in marketing or sales  directorial role   Experience 6/8 years total experience & out of which 2/4 years & above in  directorial position respectively, real estate work experience is mandatory   Place of work Head office   Position 3: Site Engineer   Job Requirement Required Education MSC/ BSC/ diploma in civil engineering, Construction management, or in related fields with applicable work experience   Experience 4/ 6/8 years total experience respectively   Qty 2   Place of work Project (Addis Ababa)   Position 4: Office Engineer   Job Requirement   Required Education MSC/ BSC/ diploma in civil engineering, Construction management, or in related fields with applicable work experience   Experience 4/ 6/8 years total experience respectively   Qty 2   Place of work Head office   Position 5: Project Follow up Engineer   Job Requirement Required Education MSC/ BSC/ diploma in civil engineering, Construction management, or in related fields with applicable work experience   Experience 4/ 6/8 years total experience respectively   Qty 2   Place of work Head office   Position 6: Engineering & Contract Administration Head   Job Requirement   Educational MSC/ BSC in civil engineering, Construction management, or in a related field with applicable work experience   Experience 6/ 10 years total experience & out of which 2/ 4 years & above in  directorial position respectively, real estate industry work experience is preferable   Place of work Head office   Position 7: Construction & Operation Head   Job Requirement Educational MSC/ BSC in civil engineering, Construction management, or in a related field with applicable work experience   Experience 6/ 10 years total experience & out of which 2/ 4 years & above in  directorial position independently, real estate industry work experience is preferable   Place of work Head office
How to Apply
Interested applicants who meet the pronounced requirement are invited to submit their updated CV andnon-returnable copy of their credentials along with original documents within 10 (ten) working days of this announcement, at our Head office located on Addis Ababa, Bole sub city, Woreda 03 Bole Atlas road, Desalegn Hotel area, PlatinumPlaza 6th floor, H.No.603.  🚧For more info Telephone +251939680000/ +251903744400 📩you may send your documents via our mail address contactunitedrealestateplc@gmail.com   Incomplete application wo n't be considered  Only short- listed candidates will be contacted.   Deadline: September 5, 2024

የአለማችን ረጅሙ የእንጨት ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ በአሜሪካ ሊገነባ ነው! 🚧በአሜሪካ ዊስኮንሲን ግዛት ውስጥ የሚገነባው 55 ፎቅ ያለው አዲሱ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የዓለማችን ረጅሙ የእ
የአለማችን ረጅሙ የእንጨት ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ በአሜሪካ ሊገነባ ነው!
🚧በአሜሪካ ዊስኮንሲን ግዛት ውስጥ የሚገነባው 55 ፎቅ ያለው አዲሱ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የዓለማችን ረጅሙ የእንጨት ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ይሆናል ተብሏል።

የአለማችን ረጅሙ የእንጨት ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ በአሜሪካ ሊገነባ ነው! 🚧በአሜሪካ ዊስኮንሲን ግዛት ውስጥ የሚገነባው 55 ፎቅ ያለው አዲሱ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የዓለማችን ረጅሙ የእ
የአለማችን ረጅሙ የእንጨት ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ በአሜሪካ ሊገነባ ነው!
🚧በአሜሪካ ዊስኮንሲን ግዛት ውስጥ የሚገነባው 55 ፎቅ ያለው አዲሱ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የዓለማችን ረጅሙ የእንጨት ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ይሆናል ተብሏል።

አንድ ሰው ግንባታውን ሲያከናውን የጎረቤቱን ቤት ቢናድበት ወይም በግንባታ ሥራው የተነሳ የጎረቤቱን ቤት ቢያፈርስ ተጠያቂ ነው። የመፍረስ አደጋ ባይገጥምም እንኳን በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2077 (1) እና (2) መሰረት  አንድ ሕንጻ በሌላው ይዞታ ላይ ያልታሰበ ድንገተኛ ሌላ አደጋ ቢያደርስ የሕንጻው ባለቤት ተጠያቂ (ካሳ ከፋይ) ይሆናል። ይህም ማለት እንዲፈርስ ያደረገውን ቤት በእራሱ ወጪ እንዲጠግን/እንዲሰራ ይገደዳል። ቢሆንም ግን በቁጥር 2079 መሰረት በግንባታ ወቅት (በተለይ ከቁፋሮ ጀምሮ ባሉት የመሰረት ሥራዎች ጊዜ) በሌላ የጎረቤት ሕንጻ ላይ የመፍረስ አደጋ ከመድረሱ በፊት አስቀድሞ ሥጋት ላይ ያለው ክፍል አስፈላጊውን ድጋፍ ወይም ጥንቃቄ እንዲደረግለት ማድረግ ይችላል። “ጎረቤት” የተባለው አካልም ይህ ስጋት ከተሰማው አስቀድሞ ጥንቃቄ እንዲደረግለት የመጠየቅ ሕጋዊ መብት አለው። 🚧ጠቅለል ሲደረግ፦ አንድ የሕንጻ ባለይዞታ በግንባታ ወቅት በጎረቤት ይዞታ ላይ የተገነባን ሕንጻ የመፍረስ ወይም የመሰንጠቅ ጉዳት ቢያደርስ እንዲሁም ሕንጻው በሚገነባበት ወቅትም ይሁን ከተጠናቀቀ በኋላ ከዚያ ሕንጻ ላይ እየወደቁ በሌላው ሕንጻ ወይም ይዞታ ላይ ለሚያደርሱት ጉዳት ተጠያቂ ነው (ፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2080)። የጎረቤት ሕንጻ ቢፈርስ ተጠያቂ የማይሆንበት አግባብ በጎረቤት ይዞታ ወይም ሕንጻ ላይ ጉዳት ቢደርስ የማይጠየቀው በሁለት ምክንያት ነው። [አንደኛው] በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 2078 (1)  መሰረት ጎረቤት የተባለው ባለይዞታ ይዞታውን ግንባታ ለሚያከናውነው ሰው የለቀቀለት እንደሆነ ወይም ግንባታ የሚያከናውነት አካል የራሱን ሕንጻ ለፈረሰበት ጎረቤቱ የሚለቅለት ከሆነ ነው። [ሁለተኛው] “ጎረቤት” የተባለው አካል ሕንጻው የመፍረስ አደጋ እንዳይገጥመው ጥንቃቄ እንዲደረግለት የመጠየቅ መብት የሚኖረው ግን አስቀድሞ የገነባው ሕንጻ በመሬት ውስጥ፣ በመሬት ላይም ይሁን በአየር ላይ አዲስ የሚገነባውን ባለይዞታ የካርታ መስመር ያላለፈ ከሆነ ብቻ ነው። ለምሳሌ፦ አስቀድሞ የገነባው ጎረቤት የመሰረት ግንባታው ወይም ተንጠልጣይ የባልኮኒ ወለል ወደሰው ይዞታ አንድ ሳንቲሜትርም ቢሆን ካለፈ እንዲያስተካክል ወይም እንዲያፈርስ ይገደዳል። አዲስ ግንባታ የሚገነባውም ሰው ጎረቤቱ ወደይዞታው ገብቶ የሰራውን የሕንጻ አካል እንዲያፈርስና እንዲያስተካክል ሳያስጠነቅቅ ማፍረስ የለበትም፣ በፍርድ ቤት በተቆረጠ ቀነ ገደብ እንዲያስተካክል ማሳሰብ ሲኖርበት በዚያ ቀነገደብ ካላስተካከለ ግን ትእዛዝ አስወጥቶ ማስፈረስ/ማፍረስ/ ይችላል

አንድ ሰው ግንባታ እያከናወነ የጎረቤት ቤት ቢፈርስበት የጎረቤቱን ቤት እንዲያሰራ ይገደዳል ወይስ ሌላ የህግ እይታ አለ?👇
አንድ ሰው ግንባታ እያከናወነ የጎረቤት ቤት ቢፈርስበት የጎረቤቱን ቤት እንዲያሰራ ይገደዳል ወይስ ሌላ የህግ እይታ አለ?👇

የግንባታ ውል ሰነድ በግልጽ ማስቀመጥ ያለበት ነጥቦች:- 🚧የፕሮጀክቱን ዲዛይን እና ዝርዝሮች: ➢የፕሮጀክት ባለድርሻ አካላትን ድርሻ፣ መብትና ግዴታ፣ ➢የሚጠበቀውን የግንባታ ጥራት የሚገልጹ ትንታኔ
የግንባታ ውል ሰነድ በግልጽ ማስቀመጥ ያለበት ነጥቦች:-
🚧የፕሮጀክቱን ዲዛይን እና ዝርዝሮች:                                                      ➢የፕሮጀክት ባለድርሻ አካላትን ድርሻ፣ መብትና ግዴታ፣ ➢የሚጠበቀውን የግንባታ ጥራት የሚገልጹ ትንታኔዎች፣ ➢የፕሮጀክቱን ተጠባቂ የጊዜ ሰሌዳዎች፣ ➢የፕሮጀክቱን ዋጋ እና አከፋፈል ሁኔታዎች፣ ➢የደህንነት እና የጤና አጠባበቅ፣ መመሪያዎች፣ ➢ፕሮጀክቱን የሚመለከቱ የሕግ ማእቀፎች ➢የፕሮጀክቱ ባለድርሻ አካላትን ፊርማ እና ማኅተም ➢ፕሮጀክቱ የሚፈልገውን የሰው ኃይል ብቃትና ብዛት ➢ፕሮጀክቱ የሚፈልገው ማሺነሪ አይነትና ብዛት ➢የእያንዳንዱን የሥራ አይነት ዝርዝርና የግንባታ ስነዘዴ ➢የፕሮጀክቱን ባለድርሻ አካላት ዝርዝር መረጃ አንድ የግንባታ ውል ሰነድ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን ዋና ዋና ጭብጥ ጉዳዮች በግልጽ እና በዝርዝር ማስቀመጥ ይኖርበታል። የተወሳሰበ፣ ያልተብራራ እና እርስ በእርሱ የሚጋጭ ሀሳብ ቢኖርበት ግን በሚኖረው የፍርድ ቤት ክርክር ባለድርሻ አካላትን በተናጠል አልያም በጋራ ኪሳራ ላይ ሊጥል ይችላል። ይህ ሁኔታ ደግሞ ፕሮጀክቱን በጤናማ ግንኝነት ለመፈጸም እክል ሊፈጥር ስለሚችል ለጥራት ችግር እና ለጊዜ ብክነት እንዲጋለጥ ያደርገዋል። 

የግንባታ ቦታን ማስረከብ 🚧🏗 የግንባታ ባለቤት (Client) ለግንባታ ሥራ መሰናክል ከሆኑ ነገሮች (ለምሳሌ፦ የካሳ ጥያቄ ከሚያነሱ ሰዎች ቁጥጥር፣ ከመብራት፣ ከውሃ፣ ከቴሌ ግንባታዎችና መሣሪያዎ
የግንባታ ቦታን ማስረከብ 🚧🏗
የግንባታ ባለቤት (Client) ለግንባታ ሥራ መሰናክል ከሆኑ ነገሮች (ለምሳሌ፦ የካሳ ጥያቄ ከሚያነሱ ሰዎች ቁጥጥር፣ ከመብራት፣ ከውሃ፣ ከቴሌ ግንባታዎችና መሣሪያዎች) በማጽዳት ወይም ነጻ በማድረግ ዝግጁ የሆነ የግንባታ ቦታን ለሥራ ተቋራጩ (Contractor) የማስረከብ ሕጋዊ ኃላፊነት አለበት። ባለቤቱ የግንባታ ቦታውን ምክንያታዊ በሆነ ጊዜ ውስጥ ለሥራ ተቋራጩ ካላስረከበ የግንባታ ማስረከቢያ ጊዜ መራዘም/መዘግየት/ ላይ ለሚያስከትለው ኪሳራ ወይም ወጪ ኃላፊነቱን እንደሚወስድ የሕንጻ ግንባታ ደንቦች (Standard Building Contract with quantities) በአንቀጽ 2.4 እና 2.24 ስር የሰፈረ ድንጋጌ ነው።

• • • በመጨረሻም በተለምዶ አሠራር አንዳንድ ሥር የሰደዱ ግንዛቤዎችና የአሠራር መዛባቶችን በሚመለከት የተወሰኑ ነጥቦች ማጤን ያስፈልጋል
ሀ) አርኪቴክቶችን በሚመለከት
1) የአርኪቴክት ቢሮዎች አራቱን የአርኪቴክት ክህሎቶች ሳያሟሉ ሲቀሩ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚደርስ፤ 2) የአርኪቴክት የሙያ ክፍያ፥ ለባለሞያዎች በሚከፈል ደሞዝ ላይ ተመስርቶ ሳለ ብቁና ተፈላጊውን የባለሞያዎች ቁጥር ባለማሳተፍ የጥራትና የጊዜ መጓተት ማስከተል እንደሚከሰት፤ 3) ከሥራ ተቋራጮች ጋር የባላንጣነትና የበላይነት መንፈስ የማሳየት ዝንባሌ ማንፀባረቅ ያለመግባባት እንዲሰፍን እንደሚያደርግ፤ የታየባቸው አጋጣሚዎች ጥቂት አይደሉም።
ለ) በፕሮጀክት ባለቤት በኩል
1) በአርኪቴክቱ በኩል የሚመደብ የሥራ ተቆጣጣሪና በባለቤቱ በተመደበው የፕሮጀክት ኃላፊ (የጽ/ቤቱ) መካከል ያለውን ልዩነት በውል ያለመረዳት፤ 2) በአንድ ጊዜ የሚሄዱ ሁለት ውሎች ቢኖሩም፥ በግንባታው ውል ላይ ያሉት ወገኖች ሁለት ብቻ (ባለቤቱና ሥራ ተቋራጩ) መሆናቸውን፥ አርኪቴክቱም በግንባታው ውል የተሰጠውን ተግባር ብቻ እንደሚወጣ አለማጤን፤ 3) የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ኃላፊ በሁለቱም ውሎች የተሰጠውን ተግባር እንደሌለ፥ በቴክኒክ ረገድ በተለይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፥ ነገር ግን አርኪቴክቱም ሆነ ሥራ ተቋራጩ ሥራቸውን በሚገባ ስለመሥራታቸው ለባለቤቱ ሪፖርት ሊያቀርብ እንደሚችል፤ 4) በልዩ ልዩ ወገኖችና ተዋናዮች የሥራ ኃላፊነት መደራረብ የግጭትና ያለመግባባ መንስዔ እንደሆነ፤በተደጋጋሚ ይታያሉ።
ሐ) ያለመግባባትን ለማስወገድ
1) ወደ ክስ መሄድ ከፍተኛ ወጪና የሥራ መስተጓጎል እንደሚያስከትል፤ 2) የተመረጠው ያለመግባባትን የማስወገጃ ዘዴ በግንባታ ወቅት አጁዲኬተር እንዲሰየም ማድረግ መሆኑ፤ በተግባር የታየ ነው፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የተነሱትን ሃሳቦች በዝርዝር መተንተንና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ጋር በሚደረግ ውይይት ማዳበር የአርኪቴክቶች ሚና እንደሚሆን በማሰብ ሲቀርብ፤ በተከታይ የአስተያየት መስጫ ጽሑፎች እንደሚዳብር ተስፋ በማድረግ ነው።

የቀጠለ.. . የፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ዋና ሥራዎች የፕሮጀክቱን ቦታ በእጅ ማድረግ፣ አርኪቴክት መምረጥና ፣ሥራ ተቋራጭ መቅጠር ናቸው። ከነዚህ ሦስት ሥራዎች ውስጥ የመጀመሪያው የፕሮጀክት ጽ/ቤት ከመቋቋሙ በፊት ተከናውኖ የሚገኝበት አጋጣሚ ቢኖርም፤ የቦታውን የይዞታ ሰነዶችንና ተያያዥ መረጃዎችን ተቀብሎ ማደራጀት የማይቀር ተግባር ነው። ለሕንፃው ዲዛይን አርኪቴክት የሚመረጡ ሥራ ከቀዳሚ ሥራዎች ውስጥ በጥንቃቄ መከናወን ያለበት ተግባር ነው። ምክንያቱም የሚመረጠው አርኪቴክት ዲዛይኑን ከማዘጋጀት በተጨማሪ የግንባታውን ሥራ የሚቆጣጠርና የባለሃብቱ ዋና አማካሪ በመሆኑ ነው፡፡ በእርግጥ ባለሃብቱ ራሱ አርኪቴክቱን ከመምረጥ ጀምሮ ሌሎች ልዩ አዋቂ ለሚያስፈልጋቸው ሥራዎች በየጊዜው የተለያዩ አማካሪዎች ተወዳድረው የሚመርጡበትን ሰነድ ዝግጅትና የአመራረጡን ሂደት ይከታተላል። ሥራ ተቋራጭ የመቅጠር ሂደትን በዋነኛነት የሚያከናውነው አርኪቴክቱ ቢሆንም የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅበታል። ለግንባታው በአርኪቴክቱ የተዘጋጀውን ሰነድ የተሟላና በጥራት የተዘጋጀ መሆኑ እንዲረጋገጥ ማድረግና ይዘቱም የባለሃብቱን ጥቅም ያስጠበቀ መሆኑን ተመልክቶ ሃሳብ የመስጠት ሚናም ይኖረዋል። በዚህ ወቅት የፕሮጀክቱን ጽ/ቤት የሚመራው ኃላፊ በሳል የምሕንድስና ባለሙያ መሆን ይኖርበታል። ይህም ካልተቻለ በመካከለኛ ደረጃ የሚገኝ የምሕንድስና ባለሙያ መድቦ በጊዜያዊ በሳል አማካሪ እንዲደገፍ ማድረግም ይቻላል። በግንባታው ወቅት የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ በግንባታው ቦታ ላይ ወይም በአቅራቢያ ባለ ሕንፃ ላይ ቢሆን አመቺ ይሆናል። ከሌሎች ፕሮጀክቶች ተሞክሮ ባለሃብቱ ስላሰበው ፕሮጀክት አንዳንድ መረጃዎች ሊኖሩት ይችላሉ። ነገር ግን በእንደዚህ ዓይነት መረጃዎች ብቻ እየተመሩ ረጅም ርቀት መሄድ ከፍተኛ ጉዳት ሊኖረው ስለሚችል ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉት ግብዓቶች በገንዘብ፤ በጊዜና በሌላም ረገድ በዝርዝር ተለይተው መታወቅ ይኖርባቸውል። ይህንንም ለማድረግ እስከሙሉ የአዋጪነት ጥናት ማከናወን የሚደርስ ቅድመ ዝግጅት ያስፈልጋል። በተለይም ፕሮጀክቱ በባንክ ብድር የሚከናወን ከሆነ የግንባታውን ብቻ ሳይሆን ሙሉ የፕሮጀክት ወጪውን ያካተተ ጥናት ቢሆን ይሻላል። ይህንንም ሥራ አማካሪ አስመርጦና ተከታትሎ ማስፈፀም ከሦስቱ ዋና ዋና ሥራዎች ቀጥሎ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የሚያተኩርበት ይሆናል። በራስ አቅም ሊገነባ ይችላል፤ ስለዚህም የአዋጭነት ጥናት አያስፈልግም ቢባል እንኳን፤ በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተዘጋጀ የድርጊት መርኀ ግብርና የበጀት ዝርዝር ሊኖር ይገባል። አንድ 625 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ፕሮጀክት እንደምሳሌ በመውሰድ በጊዜና በወጪ ረገድ የሚያስፈልገውን ግብዓት የሚያሳይ ጠቋሚ መረጃ ከዚህ በታች የተመለከተውን ሊመስል ይችላል። አብዛኛውን ጊዜ የፕሮጀክት ሃሳብ ይዘው የተነሱ ባለሃብቶችን የሚያነጋግር ሰው፤ የራሳቸውን መኖሪያ ቤት የሚሠሩትን ጨምሮ፤ ፕሮጀክታቸውን እንዴት ባነሰ ጊዜ ሊገነቡ እንዳቀዱና ወጪያቸውም ምን ያህል አነስተኛ እንደሚሆን ያላቸውን ስሜት ሊገነዘብ ይችላል። እውነታውን ግን የነሱ ፕሮጀክት ከሌሎች ፕሮጀክቶች ሊለይ የሚችልበት አጋጣሚ የሌለ መሆኑ ነው። ከላይ የቀረበው ግርድፍ ዝርዝርም በአገሪቱ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከእውነታው የተቀራረበ ቢሆንም ወዲያውኑ ተቀባይነት ባያገኝም በሂደት ልዩ ክትትል ተደርጎ እንኳን የተሻለ ውጤት ለማስገኘት አዳጋች ነው።

ግዙፍ የሕንፃ ፕሮጀክቶች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ወጪ የሚጠይቁና በአማካይ ከአራት ዓመት ያላነሰ ግዜ የሚወስዱ እንደመሆናቸው መነሻ ሃሳብ ብቻ ይዞ በራስ አከናዋኝነት አንድ ባለሀብት በቀጥታ ሊተገብራቸው የሚችሉ አይደሉም። ፕሮጀክቱ የሚያርፍበትን ቦታ በእጅ ከማስገባት ጀምሮ ግንባታው ተጠናቅቆ የሕንፃ አስተዳደር ሥርዓት እስኪዘረጋለት ድረስ የብዙ ተዋናዮች ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው። የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ዓለም አቀፋዊ ትክል አሠራር፤ የግዙፍ የሕንፃ ፕሮጀክቶችን ይዘት ያጤነና መደበኛ የቴክኒክ ሰነዶቹም ይህንኑ ለማስተናገድ በሚችል መንገድ የተዘጋጁ ስለሆነ የባለሃብቶችን ሃሳብ ከግብ ለማድረስ የሚረዳ ነው። ባለሃብቶችም ሥራውን በግል አቅም ከመሞከር ወይም በተለምዶ ከሚከናወን ወጥነትና የሙያ ጥራት ከጎደለው አሠራር ይልቅ ሙያዊ መሠረትና የተፈተነ ሂደት ያለውን ዓለም አቀፋዊ ትክል አሠራር እንዲከተሉ ይመከራል። የፕሮጀክት ሃሳብ ያለው ባለሃብት በመጀመሪያ ማድረግ ያለበት የፕሮጀክት ጽ/ቤት ማቋቋም ነው። ይህ የፕሮጀክት ጽ/ቤት እንደ ፕሮጀክቱ የክንውን ደረጃ የሚያስፈልጉት ሠራተኞች ብዛትና የሙያ ስብጥር ሊለያይ ይችላል። በአንድ ጉዳይ አስፈፃሚ ተጀምሮ ወደ ግንባታ ሥራ ሲቃረብ በምሕንድስና ባለሙያ የሚመራና አስፈላጊ የአስተዳደርና የፋይናንስ ሰራተኞች የሚመደቡለት እስከመሆን ሊደርስ ይችላል። የፕሮጀክቱ ባለቤት ግለሰብ ባለሃብት እንኳን ቢሆን ከሌላ ሥራው ለይቶ ፕሮጀክቱን ነጥሎ እንዲመራ ማድረግ በጥብቅ ይመከራል። ባለቤቱ የአክስዮን ማኅበር፣የመንግስት ድርጅት ወይም ሌላ ዓይነት ተቋም ከሆነ ደግሞ የተቋቋመበት ዓላማ ከፕሮጀክቱ ህልውና ጋር የተያያዘ ቢሆንም እንኳን ራሱን የቻለ የፕሮጀክት ጽ/ቤት ከሌለው የሥራ መወሳሰብ እንደሚደርስበት የታወቀ ነው። የፕሮጀክት ጽ/ቤት የቀን ተቀን ክትትል የሚደረግበትና ማንኛውም ፕሮጀክቱን የሚመለከቱ ሰነዶች በጥንቃቄ የሚያዙበት እንዲሆን ይጠበቃል። በተደራቢ ሥራነት፤ በኮሚቴ አማካይነት ወይም በያዝ ለቀቅ የሚሠራ መሆን የለበትም።

የፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ዋና ሥራዎች የፕሮጀክቱን ቦታ በእጅ ማድረግ፣ አርኪቴክት መምረጥና ፣ሥራ ተቋራጭ መቅጠር ናቸው። ከነዚህ ሦስት ሥራዎች ውስጥ የመጀመሪያው የፕሮጀክት ጽ/ቤት ከመቋቋሙ በፊት ተከናውኖ የሚገኝበት አጋጣሚ ቢኖርም፤ የቦታውን የይዞታ ሰነዶችንና ተያያዥ መረጃዎችን ተቀብሎ ማደራጀት የማይቀር ተግባር ነው። ለሕንፃው ዲዛይን አርኪቴክት የሚመረጡ ሥራ ከቀዳሚ ሥራዎች ውስጥ በጥንቃቄ መከናወን ያለበት ተግባር ነው። ምክንያቱም የሚመረጠው አርኪቴክት ዲዛይኑን ከማዘጋጀት በተጨማሪ የግንባታውን ሥራ የሚቆጣጠርና የባለሃብቱ ዋና አማካሪ በመሆኑ ነው፡፡ በእርግጥ ባለሃብቱ ራሱ አርኪቴክቱን ከመምረጥ ጀምሮ ሌሎች ልዩ አዋቂ ለሚያስፈልጋቸው ሥራዎች በየጊዜው የተለያዩ አማካሪዎች ተወዳድረው የሚመርጡበትን ሰነድ ዝግጅትና የአመራረጡን ሂደት ይከታተላል። ሥራ ተቋራጭ የመቅጠር ሂደትን በዋነኛነት የሚያከናውነው አርኪቴክቱ ቢሆንም የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅበታል። ለግንባታው በአርኪቴክቱ የተዘጋጀውን ሰነድ የተሟላና በጥራት የተዘጋጀ መሆኑ እንዲረጋገጥ ማድረግና ይዘቱም የባለሃብቱን ጥቅም ያስጠበቀ መሆኑን ተመልክቶ ሃሳብ የመስጠት ሚናም ይኖረዋል። በዚህ ወቅት የፕሮጀክቱን ጽ/ቤት የሚመራው ኃላፊ በሳል የምሕንድስና ባለሙያ መሆን ይኖርበታል። ይህም ካልተቻለ በመካከለኛ ደረጃ የሚገኝ የምሕንድስና ባለሙያ መድቦ በጊዜያዊ በሳል አማካሪ እንዲደገፍ ማድረግም ይቻላል። በግንባታው ወቅት የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ በግንባታው ቦታ ላይ ወይም በአቅራቢያ ባለ ሕንፃ ላይ ቢሆን አመቺ ይሆናል። ከሌሎች ፕሮጀክቶች ተሞክሮ ባለሃብቱ ስላሰበው ፕሮጀክት አንዳንድ መረጃዎች ሊኖሩት ይችላሉ። ነገር ግን በእንደዚህ ዓይነት መረጃዎች ብቻ እየተመሩ ረጅም ርቀት መሄድ ከፍተኛ ጉዳት ሊኖረው ስለሚችል ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉት ግብዓቶች በገንዘብ፤ በጊዜና በሌላም ረገድ በዝርዝር ተለይተው መታወቅ ይኖርባቸውል። ይህንንም ለማድረግ እስከሙሉ የአዋጪነት ጥናት ማከናወን የሚደርስ ቅድመ ዝግጅት ያስፈልጋል። በተለይም ፕሮጀክቱ በባንክ ብድር የሚከናወን ከሆነ የግንባታውን ብቻ ሳይሆን ሙሉ የፕሮጀክት ወጪውን ያካተተ ጥናት ቢሆን ይሻላል። ይህንንም ሥራ አማካሪ አስመርጦና ተከታትሎ ማስፈፀም ከሦስቱ ዋና ዋና ሥራዎች ቀጥሎ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የሚያተኩርበት ይሆናል። በራስ አቅም ሊገነባ ይችላል፤ ስለዚህም የአዋጭነት ጥናት አያስፈልግም ቢባል እንኳን፤ በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተዘጋጀ የድርጊት መርኀ ግብርና የበጀት ዝርዝር ሊኖር ይገባል። አንድ 625 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ፕሮጀክት እንደምሳሌ በመውሰድ በጊዜና በወጪ ረገድ የሚያስፈልገውን ግብዓት የሚያሳይ ጠቋሚ መረጃ ከዚህ በታች የተመለከተውን ሊመስል ይችላል። አብዛኛውን ጊዜ የፕሮጀክት ሃሳብ ይዘው የተነሱ ባለሃብቶችን የሚያነጋግር ሰው፤ የራሳቸውን መኖሪያ ቤት የሚሠሩትን ጨምሮ፤ ፕሮጀክታቸውን እንዴት ባነሰ ጊዜ ሊገነቡ እንዳቀዱና ወጪያቸውም ምን ያህል አነስተኛ እንደሚሆን ያላቸውን ስሜት ሊገነዘብ ይችላል። እውነታውን ግን የነሱ ፕሮጀክት ከሌሎች ፕሮጀክቶች ሊለይ የሚችልበት አጋጣሚ የሌለ መሆኑ ነው። ከላይ የቀረበው ግርድፍ ዝርዝርም በአገሪቱ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከእውነታው የተቀራረበ ቢሆንም ወዲያውኑ ተቀባይነት ባያገኝም በሂደት ልዩ ክትትል ተደርጎ እንኳን የተሻለ ውጤት ለማስገኘት አዳጋች ነው።

Share 1336_2016_የተሻሸሰለው_የመሬት_ካሳ_አዋጅ.pdf

Share የአርክቴክቶች አማካሪ ቢሮ.pdf

Share የኮንስትራክሽን_ንብረት_አቻ_ግመታ.pdf

Share የኮንስትራክሽን_ማኔጅመንት_አማካሪ.pdf