Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Ir al canal en Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Chat us! Buy ads: https://telega.io/c/consite
Mostrar más3 596
Suscriptores
-524 horas
-157 días
+130 días
Archivo de publicaciones
👉ለጨረታ ማስከበሪያ ከመድን የሚቀርቡ ዋስትናዎች (Conditional Bond) ከዚህ በኋላ ተቀባይነት አይኖራቸውም።
💫ስራ ተቋራጮች ለውል ማስከበሪያ ከመድን የሚያቀርቡት ዋስትና Unconditional መሆን ይጠበቅበታል።
📌 በነባሩ የፌደራል ግዥ መመሪያ በግንባታ ስራ ለተሰማሩ የሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የመድን ዋስትና (Conditional Insurance Bonds) ለጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም አዲሱ መመሪያ ይህንን አማራጭ አላካተተም።
📌 ለውል ማስከበሪያ ደግሞ ከአገር ውስጥ የግንባታ ዘርፍ ሥራ ተቋራጮች ወይም መድሐኒት እና የሕክምና መሣሪያዎች አምራች ድርጅቶች ለሚፈጸም ግዥ ከታወቀ የመድን ድርጅት የሚቀርብ በሁኔታ ላይ ተመሠረተ የመድን ዋስትና ቢያቀርቡ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም በአዲሱ የግዥ መመሪያ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ መሆን እንዳለበት ተመላክቷል።
N.B. የሃገር ውስጥ መድን ድርጅቶች በብሄራዊ ባንክ በኩል በተሰጣቸው መመሪያ መሰረት በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና (Unconditional) መስጠት የማይችሉ ከመሆኑ አንጻር ይህ እንዴት ተፈጻሚ ሊሆን እንደሚችል ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው።
📌 የአገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች እንዲሁም የመድሀኒት እና ሕክምና መሳሪያ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሁኔታ ላይ የተመሰረተ (conditional) የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና ከታወቀ የመድን ድርጅት ሊያቀርቡ እንደሚችሉ የሚገልፀው አንቀፅ ባለበት ፀንቷል።
BATCODA-Technical Specification.pdf3.07 KB
🔵 ተቋራጮችና የተቋራጭ አማካሪዎች ምዘና እና ደረጃ ይወጣላቸዋል ተባለ
ከተያዘዉ ዓመት ጀምሮ ዉጤታማና ተወዳዳሪ የሆኑ ተቋራጮችና አማካሪዎች እንዲሁም የመንግስት ፕሮጀክቶች ባለቤቶችን ለመለየት እንዲቻል ምዘናና ደረጃ ይወጣላቸዋል ተብሏል፡፡
‹‹የሃገር ዉስጥ የግንባታ ኢንደስትሪ ዘርፍ ተፎካካሪነት እና ምዘና ›› በተሰኘ መንገድ ነዉ ተመዝነዉ ደረጃ እንደሚሰጣቸዉ የተገለጸዉ፡፡
🔷 የከተማና መሰረተ ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፤የኮንስትራክሺን ዘርፍ የአፈጻጸም ደረጃ ለማሻሻልና የዘርፉን ጤናማነት እንዲሁም ብቃት ያለዉ ተወዳዳሪ የኮንስትራክሺን ኢንደስትሪ እንዲሆን እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
🔷 የኮንስትራክሺን ኢንደስትሪ ምክርቤትን ጨምሮ የሚመለከታቸዉ የዘርፉ ተዋናዮች በግልም ሆነ ባማህበር ያሉ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን አስተዋጾ እንዲያበረክቱ ሚኒስትሯ ጠይቀዋል፡፡
🔷 ዘርፉ ግዙፍ ካፒታል የሚፈልግ፤በሃገርም ሆነ በዉጭ የሚመረቱ ግብዓቶችን የሚጠቀም፤ከፍተኛ የሆነ የሰለጠነ የሰዉ ሃይል የሚያስፈልገዉ፤ቴክኖሎጂዎችን የሚጠቀም እንደመሆኑ መጠን ከፍተኛ ትኩረትን ይፈልጋልም ሲሉም ሚኒስትሯ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
🔷 በዚህም በተቋራጮች እና በተቋራጭ አማካሪዎች ምዘናና ደረጃ እንደሚወጣ እንዲሁም ዉጤቱ ልህዝብ ይገለጻል ያሉት ሚኒስትሯ በሂደቱ ዉጤታማ የሆኑ ባለሙያዎች እዉቅና እና በጨረታ ወቅት የተለየ እድል የሚያገኙበት ሁኔታ ይመቻችላቸዋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡
🔷 በሚቀጥሉት ጥቂት አመታትም ቢያንስ ወደ 20 ለሚጠጉ ዉጤታማ የግንባታ ተቋራጮችና አማካሪዎች በየዓመቱ የሚደረገዉን ግምገማና የደረጃ ሊየታን መሰረት በማድረግ በዉጭ ገበያ ላይ ሃገርን ወክለዉ ተወዳዳሪ ሆነዉ እንዲሰሩ ድጋፍ ይደረግላቸዋል ብለዋል፡፡
🔷 በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዉ አጠቃላይ በፕሮጀክቶች አካሄድ ላይ ያለዉን ዉስብስብ ችግር የሚለይ መፍትሄ የሚሰጥ ማእቀፍ ፤‹‹ኢዝ ኦፍ ዱይንግ ቢዝነስ ኢን ኮንስትራክሺን ሴክተር›› ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል፡፡
🔷 አሁን ባለዉ አካሄድ ዘርፉ በአሳሳቢ ደረጃላይ ይገኛል ያሉት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፤ዘርፉን ለማሻሻል ይደረጉ የነበሩ ጥረቶች በተበታተነ መንገድ በመሆኑ፤የዘርፉ ተዋናዮች ለዘርፉ እድገት የበኩላቸዉን አበርክቶ እንዳያደርጉ ችግር ሆኖ መቆቱን አንስተዋል፡፡
🔷 ሆኖም ዘርፉን ለማሳደግ አሁን ለሚደረገዉ ጥረት ዉጤታማነት እነዚህ ስራዎች በፖሊሲ እና ህጋዊ ማእቀፍ ኖሯቸዉ አፈጻተማቸዉ ወጥ እንዲሆን ቀድሞ የነበረዉ አሰራር በአዲስ ተቀይሮ በስራ ላይ እንደሚዉልም አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልነበረ ኮንስትራክሺን ኢንዱስትሪ አዋጂ በስራ ላይ ከሚገኘዉ የህንጻ አዋጅ ጋር ተቀናጂቶ፤ ኢንደስትሪዉንና የዘርፉን ስራዎች ዘመኑን በዋጀ መልኩ በማካተት በአጭር ጊዜ ዉስጥ በስራ ላይ ይዉላል ሲሉም ተናግረዋል፡፡
(107.8)
👉የቤት ገበያችን ወቅታዊ የቁጥሮች ወሬ ( ከትልቅ ፎቅ የረዘመ )
📜የሪል እስቴት ኢንቨስትመንትና ግብይት በጥናት በሚመሰረቱ ገላጭ የቁጥር ቀመር ውጤቶች ላይ ተመስርቶ የሚደረግ ነው። ነገር ግን በሀገራችን በየወቅቱ በዘርፉ ያሉትን መረጃዎች አሰናድቶ ገላጭ ቁጥሮችን የሚያሳውቅ ተቋም ስለሌለን ብዙዎች ከኢንቨስትመንትና ግብይት ማሳያ ቁጥሮች ይልቅ ዲዛይንና የቢዝነስ ስትራቴጂ በመኮራረጅ ወይም ተመሳሳይ ባለሙያዎችን በመጋራት ተመሳሳይ ዲዛይንና ግንባታ የግብይት አካሄድንም በመከተል ተመሳሳይ ስህተት እየሰሩ ተመሳሳይ ኪሳራና የመሸጥ ችግር ሲደርስባቸው ቤት ፈላጊዎችም በአቅማቸው ሊገዙት የሚችል የቤት የአማራጭ እጦት እንዲገጥማቸው ሆኗል።
የእኛ ቁጥር የሌለን በመሆኑ ሰሞኑን the ethiopian reporter የወጣው ጽሁፍ ሀገራችን በቤት ውድነት መለኪያ መስፈርት (Housing affordability index) 47.1 በማምጣት ከዓለማችን ለዜጎቿ ቤትን በውድ ዋጋ በማቅረብ ሶስተኛ ደረጃን ማግኘቷ ተገልጾ ጉድ እየተባለ ነው። The reoprter በመረጃ ምንጭነት የጠቀሰው የኑሮ ዘይቤ ጉዳዮችን በቋሚነት የሚተነትነው NUMBEO በከተሞች ደረጃ ባወጣው የ2025 ግማሽ ዓመት ወቅታዊ ሪፖርት ላይ መዲናችን አዲስ አበባን የቤት ዋጋን ለአመታዊ የቤተሰብ ገቢ (price to income ratio ) ስሌት 55.8 በማምጣት ከዓለም ላይ ለዜጎቿ ውድ ቤት በማቅረብ ቀዳሚዋ ያደርጋታል።
የቁጥሩን ተአማኒነት ለማረጋገጥ ትልሳቢ ያደረጋቸውን መነሻዎች ተመልክቼ ከወቅታዊ የሀገራችን ገበያ አንጻር ለማመሳከር ሞክሬ የሚከተለውን አስተያየት አክዬበት ሌሎች ገላጭ ቁጥሮችንም ለማብራራት ሞክሬያለሁ እነሆ:-
የ NUMBEO ታሳቢዎች
፩) ወርሃዊ የኪራይ ዋጋ በ USD
1) ባለ አንድ መኝታ አፖርትመንት በከተማ መሃል 721.195
2) ባለ አንድ መኝታ በከተማ ዳርቻ 477.50
3) ባለ 3 መኝታ በከተማ መሃል 1831.50
4) ባለ 3 መኝታ በከተማ ዳርቻ 971.50
፪) የአፓርትመንት ቤቶች መግዣ ዋጋ በካሬሜትር በ USD
1) በከተማ መሃል .... 2545.70
2) በከተማ ዳርቻ .... 1826.75
፫) ወርሃዊ ደመወዝና የቤት ብድር ወለድ
1) የተጣራ መካከለኛ የወር ገቢ ...196.00 USD
2) የቤት ብድር ወለድ (%) .... 17.67USD
የNUMBEO መረጃዎችን ስንፈትሻቸው የቤቶች ዋጋ ተብሎ ለከተማችን ዳርቻ የተወሰደው የተጋነነ ሆኖ እናገኘዋለን።በወቅታዊ ገበያ በከተማ ዳርቻ ያሉ አፓርትመንት ቤቶች አማካኝ ዋጋ ከ 1000USD
በላይ አይዘልቅም።
ለማነጻጸሪያነት በአፍሪካ ደረጃ የሪል እስቴት ኢንቨስትመንት መረጃዎችን የሚተነትነው www.theafricanvestor.com ከሳምንት በፊት ባሰራጨው መረጃ መሰረት የአዲስ አበባ የአፓርትመንት ቤቶች ወቅታዊ አማካይ ዋጋ ከ 1500- 1680USD/Sqm እንደሆነ ይገልጽልናል።
ወቅታዊ ሁኔታዎችን ስናገናዝብ የ theafricanvestor የዋጋ ግምት የተሻለ ገላጭ ሆኖ እናገኘዋለን።
በNUMBEO ታሳቢዎች የተሰሉ የዘርፉ አመላካች ቁጥሮችና ገለጻዎቻቸው
****
፩) የዋጋ ና ገቢ ንጽጽር ( Price to Income ratio) 55.77 ( ከተማችንን ከዓለም ለዜጎቿ በውድ በማቅረብ በአንደኝነት ያስቀምጣታል) ።
የ theafricanvestor መረጃዎች የNEMBEO የዋጋ ለገቢ ስሌት ላይ ብንጠቀም ስሌቱ 42.85 ይሆናል። በዚህም በተሻሻለ ስሌትም ቢሆን ሀገራችን አንደኝነቷን አስጠብቃ ለዜጎቿ ቤት መግዛት እጅግ አዳጋች (Extremely unaffordable )የሆነባት ያደርጋታል።
ይህ ቁጥር ጤናማ ሆኖ ዜጎች ቤት እንዲኖራቸው የሚሆነው የproce to income ratio ከ 5 ያነሰ እንዲሆን ይጠበቃል። ለዚህም የቤት ዋጋ እንዲቀንስ የሚያደርጉና የዜጎችን ገቢ የሚያሳድጉ ተግባራት ሊሰሩ ይገባል።
፪) Mortgage as percentage income ( የቤት ብድርን ከገቢ ጋር ንጽጽር)
በNEMBEO ታሳቢዎች መሰረት ይህ ምጣኔ 1015.73% ሲሆን ይህ ቁጥር መካከለኛ ገቢ አላቸው የሚባሉ ዜጎች በሃያ ዓመታት የሚከፈል ብድር ቢያገኙ ሊከፍሉ እንደማይችሉ የሚያሳይ ያለውን የቤት ዋጋ ውድነትና የብድር ወለድ ውድነት ነው።ይህ ቁጥር ከ 28-35 እንዳይበልጥ ይመከራል።
፫) Loan affordability index ( የዜጎች የመበደር አቅም መለኪያ).... 0.1
ይህ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን ለብድር ብቁ መሆን ለማሳየት የሚሰራ ስሌት ሲሆን አማካይ የወር ደመወዝን ከአማካይ የቤት ዋጋ ጋር በማካፈል በመቶኛ የሚገለጽ ቁጥር ሲሆን ቁጥሩ ከፍ ሲል የመበደር አቅም ከፍ ማለቱን ያሳያል።
በዚህ ስሌት መሰረት የእኛ ቤት ለግዛት የመበደር አቅም እጅግ የማይቻል ( Severe Housing Crisis ) መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን በገበያ ውስጥ ካሉት ቤቶች ውስጥ 10% የሚሆኑት ብቻ ገዢ ሊያገኙ እንደሚችሉ የሚያስረዳም ነው።
፬) Price to Rent Ratio ( በግዢና በኪራይ መካከል ያለ ንጽጽር)
በከተማ መሃል ...13.03
በከተማ ዳርቻ .... 16.56
ይህ ቤት መግዣና አመታዊ የኪራይ ዋጋን በማካፈል የሚገኝ ቁጥር ሲሆን የከተማ መሃሉ ከመግዛት ይልቅ መከራየት የተሻለ እንደሆነ ሲያሳይ በከተማ ዳርቻ ከመከራየት መግዛት የተሻለ እንደሆነ ያሳያል።
፭) Gross Rental Income ( ጠቅላላ ዓመታዊ የኪራይ ገቢን ከቤት መግዣ ዋጋ ጋር የሚደረግ ንጽጽር)
በከተማ መሃል ....7.67%
በከተማ ዳርቻ .... 6.04%
ይህ ስሌት ገዝተው ለማከራየት ለሚያስቡ የሚጠቅም ሲሆን ቁጥሩ ከ 6% ከበለጠ ለቤት ገዝቶ አከራዮች ጥሩ እንደሆነ ይገልጻል።
በዚህም መሰረት ቤት ገዝቶ ለማከራየት በከተማ መሃል ያለው ወቅታዊ ገበያ ከከተማ ዳርቻ የተሻለ እንደሆነ ያሳያል።
ስናጠቃልለው ወቅታዊው የቤት
ኢንቨስትመንትና ገበያ ነገር እንዲህ ሊባል ይችላል
፩) ለቤት ገዢዎች :- በጣም ለጥቂቶች ካልሆነ የማይቻል መሆኑን ያሳያል።
፪) አልሚዎች:- የቤት ገዢዎችን አቅም ያገናዘቡ ቤቶችን በጥናት ላይ ተመስርተው መገንባት እንዳለባቸውና በተመሳሳይ ሁኔታ ከቀጠሉ አይተውትም ሰምተውትም የማያውቁት የቁም ኪሳራ ሊደርስባቸው እንደሚችል አስበው ባሉበት ደረጃ ቆም ብለው መከለስ ያለባቸው ከልሰው ለገበያው የሚመጥኑ ቤቶች መገንባት እንዳለባቸው ያሳስባል።
፫) መንግስት :- በቀመር ውጤት የተገለጹት ቁጥሮች እንዲሻሻሉ የሚያደርጉ የመሬት አቅርቦትን በቅናሽ ( በነጻ) በማቅረብ፣ ከቀረጥ ነጻ መብቶችን በመፍቀድ፣ ከቤት ግብይት ጋር የተያያዙ ቀረጦችን በመተው፣ ለቤት አልሚዎችም ለቤት ገዢዎችም የሚሆን ብድር እጅግ አነስተኛ በሆነ ብድር እንዲቀርብ በማድረግ፣ የዜጎች ገቢን ሊያሳድጉ የሚችሉ የኢንቨስትመንትና የስራ ዕድሎችን በማስፋት ...
፬) ቤት ገዝተው ማከራየት ለሚያስቡ :- የከተማ መሃል ቤቶች የተሻለ ( 7.67%) ገቢ ሊያስገኙላቸው ስለሚችሉ ከተማ መሃል ላይ ትኩረት ቢያደርጉ ይመከራሉ።
ኢ/ር ደሳለኝ ከበደ
የሪል ስቴት ቢዝነስ አማካሪ
@etconp
+9
🧱New Point Bricks factory 🧱新点砖厂*✨ 🧱Our Bricks:- Tough,Don't decay, warp or twist, resistance to water & harsh soils, don't fade....🧱🧱👉🧱🧱🧱 ጥራት ያላቸውን እና ለተለያዩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የቀይ ሸክላ (ጡቦችን) እናመርታለን።
🧱 ለሙሉ የቤት ግንባታ፣
🧱ለባንክ ቤት ካዝና፣
🧱 ለግቢ አጥር ማጠሪያ፣
🧱 ለመንገድ ዳር ጠርዞች፣
🧱 ለሆቴሎች፣ሬስቶራንት፣እና ካፌዎች ማሳመሪያ ፣
🧱 ለx-ray ክፍሎች፣
🧱 ለፍሳሽ ማንዋሎች፣
🧱 ለኪችን ሲንክ ማስቀመጫ ፣
🧱 ለሻወር ገንዳ ማሰቀመጫ፣
🧱 የPBC ፍሳሽ ማስወገጃ ለመሸፈን፣
🧱 ለአበባ መትከያ
🧱 ለብረት ማቅለጫ ፈርኒስ፣
🧱 ለፒዛ ኦቭን፣
🧱 ለምድጃ፣
🧱 ለቆሻሻ ማቃጠያ......🧱🧱. Join Telegram channel https://t.me/+d8A-rQlF5p5lZThk for more information contact 🧱📲👉0912854327&0902378888 thank you 谢谢
በአለማችን ላይ ዌብሳይት በደንብ ከሚጠቀሙ ሀምሳ ሀገራት መሀከል የኢትዮጵያ ስም የለም!🏗- ሌላው የሚገርመው በአለማችን ላይ 2 መቶ ሚሊዮን የሚሆኑ አክቲቭ ዌብሳይቶች አሉ ። እና ይህን ያህል ቁጥር ካለው የአለማችን ዌብሳይቶች ውስጥ በኢትዮጵያ ያለው የተመዘገበ ዌብሳይት ቁጥር ግን ከ18 እስከ 25 ሺህ ብቻ እንደሆነ ይገመታል ። - እንግዲህ በአለም አቀፍ ደረጃ በየአንድ ሰአቱ 4 ሺህ አዳዲስ ዌብሳይቶች በሚከፈቱበት ወቅት ላይ. . የኛ ሀገር የድረገፅ ተጠቃሚዎች ሰላሳ ሺህ እንኳን አለመሙላቱ ያስገርማል ። - ቢያንስ ቢዝነስ የሚሰሩ ሰወች እንኳን ስለ ድረገፅ ያላቸው ግንዛቤ የሚያስገምት ነው ። 1964 ላይ ናይክ ሲመሰረት ባሉት ሱቆቹና አከፋፋዮቹ አማካኝነት ገበያው አሪፍ ነው የተባለ በቀን አራት ጫማዎች ይሸጥ ነበር። ባብዛኛው ግን ናይክ ይሸጥ የነበረው ሶስት ጫማ ነው ። ከአመታት በኋላ ዛሬ ላይ ደሞ በባለፈው አመት ብቻ የናይክ ሽያጭ በቀን ሁለት ሚሊየን ጫማ ደርሷል ። ከዚህ ውስጥ ደግሞ ግማሽ ፐርሰንት የሚሆነው ሽያጭ የተከናወነው በኦንላይን በተደረገ ግብይት ነው ። ናይክ ወደዚህ የኦንላይን ግብይት ባይገባ አንድ ሚሊየን ሰወች ቤታቸው ቁጭ ብለው ላይገዙት ይችሉ ነበር እንደማለት ነው ። ዌብሳይት እቃ ለሚሸጡ ብቻ አይደለም ለአገልግሎት ሰጭዎች እንዲሁም ላብዛኛው ድርጅቶችና ተቋማት የሚጠቅም ነገር ነው። ይህን ይህን ስናይ የዌብሳይት ጥቅም ገና ብዙ አልገባንም ማለት ይቻላል! - ዛሬ ላይ ቢዝነስ ካርድ መስጠት ባህላዊ ዘዴ እየሆነ መጥቷል። ቢዝነስ ካርድ አለህ ? አይባልም። ዌብሳይትህን ንገረኝ ነው የሚባለው። አገልግሎት ሰጭም ሆነ የተለያዩ ምርቶችን ሻጭና አምራች ሆኖ ዌብሳይት ከሌለው አግባብ አይደለም። Via~ዋሲሁን ተስፋዬ @consite🏗
በ2016 በጀት ዓመት ከ 1.6 ቢሊዮን ብር በላይ የበጀት ድልድል ጥሰት ተፈፅሟል ተባለ
በ2016 በጀት ዓመት በተደረገው ኦዲት፣ በርካታ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ለተለያዩ የሂሳብ ኮዶች ከተደለደለላቸው በጀት በላይ ወጪ ማድረጋቸው ተጋልጧል፡፡ በአጠቃላይ ብር ከ 1 ቢሊዮን 628 ሚሊዮን ብር በላይ የበጀት ድልድል ጥሰት መገኘቱ ታውቋል፡፡
ይህን ተከትሎ በ19 የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ከመደበኛ በጀት በላይ ወጪ መደረጉና በዚህም ከ 1 ቢሊዮን 103 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በ 4 መስሪያቤቶች ከ 1 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በተጨማሪም በ9 መንግስታዊ ተቋማት ደግሞ ከ 416 ሚሊዮን ብር በላይ ከካፒታል በጀት በላይ ጥቅም ላይ መዋሉን ካፒታል ሰምቷል።
የፌደራል ዋና ኦዲተር ሪፖርቱን ተከትሎ እንደገለፀዉ የበጀት ዝውውር ሳይፈፀም ለሂሳብ ኮዶች ከተደለደለው በጀት በላይ ክፍያ መፈጸም ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑና በተጨማሪም የእቅድ ዝግጅቱ በተጨባጭ ማስረጃ ያልተደገፈ ነዉ ሲል አጋልጧል።
+3
በሕንፃ ላይ የሚከሰት እሳት አደጋን የማጥፋት ሥራን ቀለል ያደረጉት ድሮኖች
******
አስቸጋሪ የነበረውን በሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች ላይ የሚነሳን የእሳት አደጋ የማጥፋት ሥራን ቀለል ያደረጉ ድሮኖች በሀገረ ቻይና ተሠርተዋል።
በምሥሉ ላይ እንደምትመለከቱት፣ በሼንዘን ግዛት ከእሳት አደጋ ማጥፊያ መኪኖች ጋር የተቆራኙ ቻይና-ሠራሽ የእሳት ማጥፊያ ድሮኖች ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች ላይ ሊነሣ የሚችልን እሳት የማጥፋት ልምምድ ላይ ተሰማርተው ይታያሉ።
አሁን በሥራ ላይ ያሉት የእሳት አደጋ ማጥፊያ መኪኖች ማጥፋት የሚችሉት እስከ 100 ሜትር ከፍታ ላይ ያለን እሳት ሲሆን፣ እነዚህ ድሮኖች ግን እስከ 151 ሜትር ርዝመት ባላቸው ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች (ባለ 34 ወለሎች ሕንፃ) ጫፍ ላይ የተነሣን እሳት ጭምር ለማጥፋት እንደሚችሉ የፒፕልስ ዴይሊ በፎቶ የተደገፈ መረጃ ያሳያል።
በነስሩ ጀማል
📍📍Sample Terms of Reference (TOR)
🚨 ለዲዛይንም ሆነ የግንባታ ቁጥጥር ማማከር አገልግሎት Terms of Reference/TOR (የስራው ዝርዝር መግለጫ) ሳያዘጋጁ መነጋገር ሆነ አማካሪ ለመቅጠር ግዥ መፈፀም አዳጋች ነው።
🚨የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ቁጥጥር ማማከር አገልግሎት (consultancy service for construction supervision) መነሻ የሚሆን TOR አያይዘንላችኋል።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
3ተኛው ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን የንግድ ትርዒት ከሰኔ 19 እስከ 21 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል
በከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እውቅና ተሰጥቶት በዓለም አቀፉ ዲኤምጂ ኢቨንት (dmg events) የሚዘጋጀው ሦስተኛው ዓለም አቀፍ የቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ኤግዚቢሽን፤ ሲምፖዚየም እና የንግድ ትርዒትን ከምስራቅ አፍሪካ መሰረተ ልማት እና የውሀ ኤክስፖ ጋር በመተባበር ከሰኔ 19 እስከ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ሊካሄድ ነው።
ዘንድሮ በሚካሄደው በሦስተኛው የንግድ ትርኢት ላይ የኮንስትራክሽን ዘርፉን ከማነቃቃት ባሻገር፤ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ተነግርዋል።
ከቻይና፣ ጀርመን፣ ህንድ፣ ጣሊያን፣ ኬንያ፣ ኦማን፣ ሰዑዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስን ጨምሮ የሌሎች ሀገራት የተውጣጡ ኤግዚቢሽን አቅራቢዎች፣ አዳዲስ የግንባታ እና የመሠረተ ልማት ግብዓቶችን በንግድ ትርዒቱ ላይ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የ ኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ሀይል ፍላጎት
የ ኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት በ 2030 እኤአ ለሁሉም ዜጋ የኤሌትሪክን ሀይል ለማቅረብ 6.8 ቢልዮን ዳላር እንደሚያስፈልገው ገለጸ።
37 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ኤሌትሪክ ሀይል አቅርቦት የሚኖር ሲሆን የተቀረው ደግሞ የኤሌትሪክ መስመር እና የጸሀይ ሀይል ቅይጥን ይጠቀማል።
ተጨማሪ ለማንበብ - https://ow.ly/8Y9l50WeH2R
ምንጭ። Addis Fortune
@ethiopianarchitectureandurbanism
በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ገበያው በህዝብ ዘንድ ያለው እምነት እያሽቆለቆለ ነው ተባለ
በኢትዮጵያ ለሦስት አስርት ዓመታት ያለ ተቆጣጣሪ አካል ሲንቀሳቀስ የቆየውና በተደጋጋሚ ገንቢዎች ቃል በገቡት ጊዜ ቤቶችን ባለማስረከባቸው የሕዝብን እምነት ያጣው የሪል እስቴት ዘርፍ፣ በገበያው እንዲቆይ ከተፈለገ ለውጥ እንደሚያስፈልገው ተጠቁሟል።
በዚህም መሰረት፣ በቅርቡ የኢትዮጵያ የሪል እስቴት ገንቢዎች ማህበር ተቋቁሞ አባላቱን በራሱ ለመቆጣጠር ማቀዱን ይፋ አድርጓል።
ማህበሩ በኢትዮጵያ ግንባታ ዘርፍ ውስጥ ታዋቂ በሆኑ ግለሰቦች የተመሰረተ ሲሆን፣ የሪል እስቴት ገበያው አደገኛ እየሆነ መምጣቱንና የሕዝብ እምነት ማሽቆልቆሉን አጽንኦት ሰጥቷል።
ይህን ችግር ለመፍታትም ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በቅርበት በመሥራት የዘርፉን ልማት ለማፋጠንና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ አቅዷል።
የማህበሩ መስራቾች፣ “የዘርፉን ስም ለመጠበቅ ራሳችንን በራሳችን እንቆጣጠራለን፤ እንዲሁም በገንቢዎችና በገዢዎች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችል አሠራር እንዘረጋለን” ብለዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ፕሮፌሰር ቶማስ ግርማይ በማህበሩ ይፋዊ ማስጀመሪያ ወቅት ባቀረቡት ጥናት፣ ከግማሽ የሚጠጉ የቤት ገዢዎች ከገንቢዎች ባገኙት ንብረት እንዳልረኩ አመልክተዋል።
ፕሮፌሰር ግርማይ “የሕዝቡ የሪል እስቴት ገንቢዎች ግንዛቤ በአሁኑ ጊዜ አሉታዊ ነው፤ የዘርፉም ገጽታ መስተካከል አለበት” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የቤት እጥረት አሁንም ዋነኛ ችግር ሆኖ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የማህበሩ ምስረታ በዘርፉ ታማኝነትንና ተጠያቂነትን ለመመለስ ትልቅ ጥረት መሆኑን ባለሙያዎች ገልጸዋል።
Source: capitalethiopia
#ADVERTISEMENT
🔧📐📐ፀግሽ ፕሌት እና ጄቦልት 📐📐
መማምረቻ ድርጅት⚙🔧🛠
🛠🛠🛠የምንሰጣቸው አገልግሎቶች🛠🛠🛠
1 መገለጫችን የሆነው የሞደፊክ ስራዎች
2 እዲሁም ፕሌት ከ 1ሚሊም እስከ 30 ሚሊም እንቆርጣለን እበሳለን
3 በመቀጠል ጄቦልት 12ሚ እስከ 32ድረስ ጥርስ አውጥተን አጥፈን እናቀርባለን
4 የተለያዩ ቦልቶች በፈለጉት መጥን
📍 አድራሻ መገኛችንቁ1. በእጆት ባለ ስልክ ለናተ ቅርብ ቁ2. በታታሪዎች መገኛ ኮርቻ ተራ ቁ3. አየር ጤና ኪዳን ምህረት ጊቢ ማንኛውም ልሜራ እዛው በዘመናዊ ማሽን እቆርጣለን ቁ4. ሴሚት ፍየል ቤት በቅርባ ባራቱም አቅጣጫ ማሳሰብያ ከጊዜው አንፃር የዋጋ ንረት ካሳሰቦት እኛጋ እሚገርም መፍትሄ አለ በማያስቡት መልክ ስራዎን ይሰራሉ ይደውሉ ስልክ ቁጥር☎️ 📞0912492727 📞0913061530 📞0923764834 መልካም ስራ ለራስ ነው ቸር ይግጠማቹ ፀግሽ ፕሌት እና ጄቦልት!
+3
ማስታወቂያ:-NAYHAf Construction Metal Trading- አቅራቢ🏗 ጥራትና ታማኝነትን የተላበሰ አገልግሎት" ከደንበኞች አብዛኛሆቻችሁ ታውቁታላችሁ
መገኛ አድራሻው ቦታ:-📍- ተክለሃይማኖት በርበሬ በረንዳ
ስልክ ቁጥር:-🔺📞+251- 944454610 🔺📞+251- 952730999 #LTZ 28 #LTZ 38 #LTZ 48 #CHS ከ ባለ 12mm ጀምሮ .... #RHS #I BEAM #U CHANNEL #H BEAM #Mesh Wire #የ ኣጥር ሽቦ #Galvanized Pipe #Angle #Aluminium Sheet #D ብረት#8 ቁጥር #ፌርሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ! ስትፈልጉ በቀጥታ ይደውሉ.. .
የኢትዮጵያ ኮንትራክተሮች ማህበር ፕሬዘዳንት ኢንጂነር የሱፍ መሀመድ የአፍሪካ ኮንትራክተሮች ፌዴሬሽን የስራ አመራር አባል ሆነው ተመረጡ።
የኢትዮጵያ ኮንትራክተሮች ማህበር በግብፅ ካይሮ በሚካሄደው 20ኛው የአፍሪካ ኮንትራክተሮች አሶሴሽን እየተሳተፈ ይገኛል።
የኢትዮጲያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት ኢ/ር የሱፍ መሐመድ በግብጽ ካይሮ እየተካሄደ በሚገኘው 20 ኛው የአፍሪካ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበራት ፌዴሬሽን(AFCCA) ጉባኤ ላይ ም /ፕሬዘዳንት ሆነው ተመረጡ።በአፍሪካ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሀገራችን ተቋራጮች እና ባለሙያዎች በስራዎች በሰፊው የመሳተፍ ሙከራዎችን የበለጠ ለማሣደግ ኢ/ር ዩሱፍ መሀመድ ም/ፕሬዘዳንት ሆነው መመረጣቸው እንደ ትልቅ አጋጣሚ የሚወሰድ ይሆናል። ማኅበሩ ለሚያደርገው ሁለንተናዊ እቅድ ደግሞ የሞራል ስንቅ የሚሆን ነው። የኢትዮጵያ ኮንትራክተሮች እና የዘርፉ ተዋናዮች እንኳን ደስ ያላችሁ ።
Invitation to Bid Tender No.
ECWCT/NCB/PSW/106/2017The Ethiopian Construction Works Corporation (ECWC) here by invites registered eligible bidders For the Procurement of Supply, Install & Commission Water Pumps And related works under national competitive bidding (NCB).
1. Interested Potential Bidders are required to present renewed relevant Trade License for the fiscal year, VAT Registration Certificate, Tax Clearance Certificate and Online Supplier list Registration Certificate together with the offer.
2. Bidding document should be prepared in English language.
3. Those bidders willing to participate for supply of any type of tonner must accompanied the bid with manufacturer authorization letter or manufacturer license.
4. Interested Potential Bidders obtain a complete set of bidding document from the Procurement Office with Payment of none refundable fee of Birr 400.00(Four hundred birr).
5. This invitation of bid is open to all interested potential bidders regardless of their nationality.
6. Bid must be accompanied with a Bid Security an amount of Birr 300,000.00(Three hundred thousand birr only) in the form of certified check (CPO) or Bank guarantee. Bid Bond in the form of insurance bond or in any other form shall not be accepted.
7. Bids must be delivered or deposited in the Tender Box situated at the office of the Procurement dep’t, before the closing date and time.
8. The deadline for bid Submission shall be on June 19, 2025 at 10:00 A.M.
9. Bids will be opened on June 19, 2025 at 10:30 A.M. in Ethiopian Construction Works Corporation Procurement Department conference room, in the presence of bidders and/or their representatives who choose to attend.
10. The Ethiopian Construction Works Corporation reserves its rights to reject any or all bids.11. Bidders may get further information at the following address: _____ Ethiopian Construction Works Corporation. Gurd Shola behind Athletics federation building and Infront of Andinet international College P. O. Box 21952/1000 Telephone 011 8 96 29 91/
01118 67 80 89
Fax No. 251-11-6 67 60 90 Addis Ababa, Ethiopia
