8 778
Suscriptores
+824 horas
+237 días
-830 días
Archivo de publicaciones
8 778
ቴዲ ርዕዮት.. .የ1990ዎቹ ከየአይዶል ተወዳዳሪ
ቴዲ በስነጥበቡ ዘርፍ ቀጥለህበት ቢሆን ኖሮ ዛሬ ፖለቲካና "ስድብ" አንድና ተመሳሳይ ዘርፎች እንደሆኑ ለመረዳት እድል አታገኝም ነበር ¡¡ 😂😂
ኧረ እንደውም በወቅቱ ካንተ ጋር ተወዳዳሪ ከነበሩት ታዳጊዎች ሃና ግርማና ዳዊት አለማየሁ ከደረሱበት ደረጃ ላይ ትደርስ ነበር !!
አስታውሳለሁኝ አንተን ከውድድሩ ውጪ እንድትሆን ያደረገህ ዳኛ ቴዲ ማክ ነበር።ዛሬ አንተ ብዙ ተከታይ ያለህ ባለሚዲያ ነህ - ቴዲ ማክን አንድ ነገር በለው ¡
በሚዲያህ ስደበው -- እ... እ... እ ማለቴ ፖለቲካ ስራበት 😂😂
8 778
ውቧ የገዳሪፍ ከተማ ....
ድሮ የኢትዮጵያ (የጎንደር) ግዛት ነበረች አሉ።
እናት አገር ገዳሪፍ ሆይ ናፍቆቱን አልቻልነውም - ምንም እንኳን በቅርቡ የምንገናኝ ቢሆንም ¡
እስኪ ...Goodnight !
8 778
ወያኔ በአፈሳ የሰበሰባቸውን ታዳጊዎች ወደ ተለያዩ የትግራይ ማሰልጠኛዎች አግዟቸው ነበር።ማሰልጠኛዎቹ በፌዴራል መንግስቱ አይን ውስጥ መሆናቸውን እንደምክንያት በመግለፅ ከትናንትና ወዲያ ጀምሮ ታዳጊዎቹን በአህሰአ ወረዳ በኩል ወደ ኤርትራ እያሻገሯቸው ነው።
(አምና july 11 ላይ የአህሰአ ወረዳን ከኤርትራ ጋር ለማገናኘት የሰሩትን መንገድ እነ ደብረፅዮን ሲመርቁ የፃፍኩትን ጭንቁርቁር ፅሑፍ አያይዤዋለሁ።ተመልሳችሁ ብታነቡት ምን ይላችኋል ?😂😂)
8 778
በውስጣችን ያለው የወያኔ ባ*ያ
------
አሁን ይሄ ምን የሚሉት ቧልታ ነው ?
ፖለቲካ (ፕሮፓጋንዳ) ተሰርቶ ተሙቶልኛል ......
1 - ሲጀመር የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በብዙ ቋንቋዎች ለመግባባት የታደለ ህዝብ ነው።እዚህ ላይ ግን ሰውዬው አማርኛ ቋንቋ ቸገረኝ አላለም።ደጋግማችሁ አዳምጡት።ሃሳቡን እየተናገረ እያለ ጠያቂው ግን ጣልቃ ገብቶ ሰውየው በቋንቋው የተቸገረ አስመስሎ
" ግዴለም በትግርኛ ተናገር " ሲል ይሰማል።ምን ለማለት እንደሆነ ግልፅ ነው - ቀሽም ሙከራ ቢሆንም ቅሉ !
2- ሲቀጥል በረሃ ላይ ለተፈጠረ የዘረፋና የሽፍትነት ወንጀል አሸተ ደምለውንና ኮ/ል ደመቀን በቀጥታ ለመወንጀል የተኼደበትን ርቀት ስታይ ፅሑፉ "ወያኔ ወያኔ " መሽተቱን ትረዳለህ - የጠነባ(የከረፋ) ሽታ‼️
ግዴላችሁም ወያኔማ ወልቃይት ጠገዴ ውስጥ በአካል አለች ያልከው ልጅ እውነት ብለሃል( ይህ ቪዲዮ በተለጠፈበት የፌስቡክ ልጥፍ ስር Leul mekonen የሰጠው ኮመንት ነው)
8 778
የምስራች ‼️
"የተከዜ ፖለቲካ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኀንነት" የተሰኘው የደራሲና ተመራማሪ ዶክተር ቹቹ አለባቸው መጽሐፍ
በአማዞን (Kindle) ላይ ተለቋል።
መጽሐፉ ኢትዮጵያዊነትን እና ስትራቴጂያዊ ሉዓላዊነትን በተከዜ ዕይታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው!
የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለመረዳት፣ ያለፉትን የታሪክና የጂኦፖለቲካዊ መስቀለኛ መንገዶችን መመርመር የግድ ነው።
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የዶክተር ቹቹ መጽሐፍ ለዲያስፖራው ወገን ተደራሽ እንዲሆን አሁን በአማዞን (Kindle) ላይ ተለቋል!
ይህ መጽሐፍ በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ-ጠለምት ቀጠና ላይ የሚያተኩር፣ በአራት ዋና ዋና ምሰሶዎች (ጂኦ-ፖለቲካ፣ ኃይል፣ ማንነት እና ብሔራዊ ደኅንነት) የተዋቀረ ጥልቅ የምርምር ሥራ ነው።
✅ መጽሐፉ ምን ይዟል?
የወልቃይት ሁመራ ኮሪደር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት ያለውን ስልታዊ ፋይዳ።
ወልቃይት እንደ ሆርሙዝ ሲል የቀጠናውን አስፈላጊት ምክንያታዊና ሳይንሳዊ በሆነ ሙግት ያስረዳል።
የአማራ ሕዝብን ታሪካዊ መሠረት፣ ማንነት እና የወቅቱን ተግዳሮቶችን በዝርዝር ይዳስሳል።
በሳይንሳዊ እና ስልታዊ መረጃዎች የታጀበ የፖሊሲ ምክረ-ሐሳብ ያቀርባል።
📚 መጽሐፉን እንዴት ማግኘት ይችላሉ?
አሁን በKindle አማካኝነት ዲጂታል ቅጂውን ከዚህ በታች ባለው ሊንክ መግዛት ይችላሉ፦
👉 [https://a.co/d/0cZr8rpp]
📢 ተጨማሪ መልካም ዜና አለ
በሚቀጥለው ሳምንት መጽሐፉ በህትመት (Paperback) መልክ የሚወጣ ሲሆን፣ በአካል መያዝ የሚፈልጉ አንባቢዎች በቅርቡ ማዘዝ ይችላሉ።
መጽሐፉ በአገር ቤት ተከታታይ መድረኮች በተለያዩ ከተሞች ይመረቃል። በተመሳሳይ ሁኔታ በውጭው ዓለም ያሉ ወገኖች መጽሐፉን አንብበው በማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮች የውይይት መድረክ እንደሚያዘጋጁ ታውቋል።
በውጭ አገር የምንኖር ወገኖች መጽሐፉን ከወዲሁ በማዘዝ በቀጣይ ለሚዘጋጀው ውይይትና ለሀሳብ ትግሉ ራሳችን እናዘጋጅ።
ያነበበ ትውልድ ሁሌም አሸናፊ ነው!
እውቀትን ለትውልድ፣ መረጃን ለስልጣኔ!
#የተከዜፖለቲካ #በጌምድር_ጎንደር #የአማራማንነት #ብሔራዊደኅንነት
#ኢትዮጵያ
8 778
ጌታቸው ረዳ ሆይ ይቺ የመለስ ዜናዊ ልጅ (ሰምሃል መለስ) ትናንት ሰድባሃለች።
"የጌታቸውን ከሃዲነት (ባንዳነት) የሚያስረዳኝ ሰው አልፈልግም።እሱ ባንዳነቱን አምኖ የተቀበለ ሰው ብቻም አይደለም ፤ በባንዳነቱ ደስተኛ የሆነ ሰው ነው" ስትል ነው ሰምሃል የዘለፈችህ።የመለስ ዜናዊን ስም ሰርክ በበጎ ስታነሳ ለምናውቅህ ለኛ ያንተ ውለታ በዚህ መጠን ወርዶ በዘለፋ መከፈሉ ስናይ በውነቱ አዝነናል።
ይቺ ባ*ጌ ልጅ ልትገሰፅ ይገባል- የሆነ ነገር በላት ጌች...¡
8 778
+4
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዞኑ ትምህርት መምሪያ የመምህራን ምደባና ዝውውር የፋ ማድረጉን ገለፀ።
ሁመራ:-ሰኔ 26/2018ዓ.ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዞኑ ትምህርት መምሪያ የመምህራን የትምህርት አመራር ልማት ቡድን የ2018/2019 ዓ.ም ምደባና ዝውውር የሚመለከታቸው ባለሙያዎችና የመምህራን ማህበር ተወካዮች በተገኝበት ፍትሃዊና ገለልተኛ በሆነ መንገድ በአገልግሎታችውን የተሰራላቸው በመሆኑን በመግለጽ ቅረታ ያላቸው መምህራን ካሉ ዝውውሩ ይፋ ከሆነበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ቅሬታቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የዞኑ ትምህርት መምሪያ የመምህራንና ትምህርት አመራር ቡድን መሪ የሆኑት አቶ የሽዋስ ሞላ ገልጸዋል።
8 778
ሽምጠጣ ...
ሁለቱ ቪዲዮ ላይ የሚታየው ሽምጠጣ ነው።
- ሞንጆሪኖም ትግራይ ውስጥ አፈሳ የለም ብላ ሸመጠጠች (ዋሸች)
- ታዳጊውም በአፈሳ ተይዞ ከተጫነበት መኪና ላይ ወርዶ ሸመጠጠ ( አመለጠ)
8 778
በጦርነቱ የተገደሉት የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ ዓሊ ኼሚኒ የቀብር ስነስርዓት የሚፈፀመው ዛሬ ነው።የ100+ አገራት ልኡካን ስነስርዓቱን ለመካፈል ቴህራን ገብተዋል።የUK እና የኖርዌይ አምባሳደሮችም ተገኝተዋል
8 778
US embassy Addis ababa
----👇
Get ready! Ambassador Massinga welcomed the renowned U.S. Air Force Band Touch n’ Go to Ethiopia as part of the upcoming Freedom 250 July 4th celebration. This special visit features unique musical and cultural exchanges with local musicians, creating new sounds and unforgettable experiences. Follow along as American and Ethiopian talents come together in harmony. #Freedom250 #USinEthiopia #USAFBands
8 778
ዶ/ር ገሰሰው ወንድም በፌስቡክ ገፁ
👇
ተስፋፊዉ የህወሓት ምሁር ጠገዴን በተመለከተ <<ወልቃይት ፀገዴ ሸሞንተ ማይ ቤት አክሱማይ ፩>> የተሰኘ የትውልድ ድንቁርና ለማስፋፋት መፅሐፍ ማዘጋጀታቸውን ዛሬ ተመለከትኩ።
በመሰረቱ ተስፋፊዉ የህወሓት ምሁር የራሱን ማንነት በተመለከተ ማለትም ትግሬ ስለሚለዉ በአግባቡ በመረዳት ብሔረ ትግሬ ማን ነው? አስተምህሮ በተገቢ ሁኔታ ሳይረዳ እና ለራሱ ማሕበረሰብ ሳያስረዳ ስለማያውቀዉ ህዝብ በድፍረት የሀገረ ትግራይ የፖለቲካ ምኞት ለማሳካት ላይ ታች እየረገጠ ይገኛል።
የለም 🛑✋ አሁን ረፍዷል😂
ይህ የራሷ አሮባት የሰዉ ታማስላለች እንደተባለዉ ነው። ምክንያቱም ገሚሱ የትግሬ ልኂቅ ኤርትራን ጨምሮ ያለዉ ህዝብ የራሴ አካል ትግሬ ነው ብሎ እየቃዠ ሲገኝ፤ ገሚሱ ትግሬ ደግሞ የአንድ ወረዳ እንባሰነይቲ ወረዳ ስያሜ የያዘችውን ትግራይ ክልል ሀገር አደርጋለሁ ብሎ በመነሳት ሌት ተቀን ከራሱ ጋር ሲዋጋ የሚያድር የቀነጨረ እና ራሱን የማያውቅ ንቅል ምሁር ነው።
ሌላኛዉ ምሁር ደግሞ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ማንነቱ ሳይለቅ የትግራይ ዕጣ ፋንታ ከኢትዮጵያ ጋር ይወሰናል ብሎ በማመን ቤት ዘግቶ የሚውል ወላጅ አልባ የሆነ (Orphan) ምሁር ነው። ይህ የምሁር ስብስብ በቅርቡ ወደ ሚዲያ ብቅ ቢልም በፅንፈኛ ብሔርተኛው ምሁር ገበሬ የሚል ስድብ ስላከናነበዉ ይህን በፀጋ በመቀበል ሰፊውን የትግራይ ህዝብ ነፃ ያወጣል ተብሎ ተስፋ የሚጣልበት ስብስብ ነው።
በመሆኑ ህወሓት ከ1983-2013 ዓ/ም አከባቢውን በጉልበት በመውረር ሲያስተዳድር የፈፀመዉ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት አንዱ የማንነት ወረራ እና የትውልድ ንቅለ ተከላ ነበር። በዚህ መሰረት ሃይ ባይ በሌለበት ዘመን የወልቃይት ታሪክ አዛብቶ በማቅረብ ሰብአ ወልቃይት <<70 ወልቃይት መስተዋት ማንነት>> የተሰኘ የውሸት ትርክት መፃፉ ይታወቃል። ይህ በዚህ ሳያበቃ 8ቱ ማይ ቤት ጠገዴን <<ፀገዴ እና ጠገዴ>> በማለት ገሚሱ በአማራ ክልል ሲቀጥል ገሚሱ ደግሞ በትግራይ ክልል እንዲጠቃለል በማድረግ ታሪክ ማዛባቱ የሚታወስ ነው።
አሁን ማሕበረሰቡ ነፃነቱን አረጋግጦ ማንነቱን በማፅናት ላይ እያለ ይህ መፀሐፍ ተፅፎ ማየት ትልቅ ድፍረት እና ወንብድና መሆኑ ግልፅ ነው። ነገደ በለዉ መደባይ ጠገዴ ራሱን፣ ታሪኩን፣ ማንነቱን፣ ስነ ልቦናዉ ጠንቅቆ የሚያውቅ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ንቃት እና ዕድገት ከፍታ የራሱ ሚና የሚጫወት አማራ ማሕበረሰብ ነው። የፍላስማን ታሪክ ሆነ የመደባይ ታሪክ አዛብቶ እና አላልቶ በማጥበቅ የሚታለል ትውልድ በአሁኑ ጊዜ የለም።
ከንቱ ድካም አትድከሙ‼️
በአጭሩ ይህ ለወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ህዝብ ማንቂያ ደወል ነው።
8 778
በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥ ወያኔ ወደ ሙሉ ግንባር ውጊያ ይገባል። ዝግጅቶች በፍጥነት እያለቁ ነው።
ቢያንስ በአምስት ግንባር ሙሉ የማጥቃት ውጊያ የሚከፍት ሲሆን፤ ውጊያው "ሠ" ሰዓት ላይ የመጀመር ዕድል አለው። (በተመሳሳይ ሰዓት)
በአጭር ቀናት ውስጥ ለሚጀመረው ውጊያ፣ ወያኔ በሁሉም የትግራይ ወረዳዎች ደረቅ ሬሽን እንዲዘጋጅ ያዘዘው ትእዛዝ ተፈጽሞ፣ ሬሽኖቹ በከባድ መኪናዎች እየተሰበሰቡ በአቅራቢያ ያለ ካምፕ እንዲገቡ እየተደረገ ነው። ምናልባትም ከ 80 በመቶ በላይ ሬሽን ወደ ዋና ዋና ማዕከላት ገብቷል።
የኛ አቋም ግልፅ ነው።
ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት የአማራ ሕዝብ ሲዋደቅላቸው የኖረው ታሪካዊ ርስቶቹ በሁኔታዎች የማይቀያየሩ፣ ቋሚና ዘላቂ የማንነት እና የክብር ጉዳይ ናቸው፡፡
እነዚህ ታሪካዊ የአማራ ርስቶች የግዛት ሁኔታና የሕዝባችን ሥነ-ልቦናዊ ስሪት የሚወሰኑ የዕጣ ፈንታው ወሳኝ ጉዳዮች በመሆናቸው በሕልውና ትግሉ ሂደት ቀይ መስመር ሆነው የሚታዩ ናቸው፡፡
የመሳይ መኮንን እንግዳ "የትናንቱ ሕወሓትና የዛሬው ሕወሓት ይለያያሉ" ማለታቸውን ተንበሌኑ ላይ ተመልክቻለሁ።
እኛ የምናውቀው ወያኔ ደግሞ በደደቢት ትርክት የተለከፈውን ነው።
መሳይ መኮንን ተፈጥሮ በቸረው ግሩም ድምፅ የዛሬ ሁለት ዓመት ይህን የፋኖ መግለጫ ማንበቡን አስታውሳለሁ👇
https://youtu.be/s443IIpDe48?si=Y50vcW1rUol0_rD0
ይህ መግለጫ በወቅቱ በአርበኛ ሀብቴ ወልዴ (ትልቁ) የሚመራው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ያወጣው ሲሆን፤ ዕዙ በሥራ አስፈፃሚ ደረጃ መክሮ ፖለቲካዊ ግምገማ አድርጎ ያዘጋጀው ነው።
አጭር ቃል ከመግለጫው፦
"ትሕነግ ከቀደመ ስህተቱ የሚማር ሳይሆን፤ ለመሳሳት የሚኖር፤ በአማራ ጥላቻ የተለከፈ፣ የወጣበትን ሕዝብ ከወንድሞቹ ጋር ደም ማቃባትን ፖለቲካ አድርጎ ያመነበት፣ ፋሺዝምን ዕድሜ ልኩን መመሪያው ያደረገ የጥፋት ኃይል በመሆኑ ከእርሱ ሊቃጣ የሚችልን ጥቃት መመከት ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው፡፡"
ይህ መግለጫ ከወጣ ገና ሁለተኛው ክረምት ላይ ነን። ባለፉት ሁለት ክረምቶች የሕወሓት የተገንጣይነት እሳቤ ሲጨምር እንጅ ሲቀንስ አላየንም።
ወደ ውስጡ ተመልክቶ የአማራ ሕዝብን ይቅርታ ለመጠየቅ አልሞከረም። የኢትዮጵያ ሐገረ-መንግሥትን የሚያይበት ዕይታ አልተቀየረም። የትርክትም፣ የፖሊሲም፣ የጉዞ አቅጣጫ ለውጦች የሉም።
ይህ በሆነበት ሁኔታ "የትናንቱ ሕወሓትና የዛሬው ሕወሓት ይለያያሉ" ማለት ዐይናችሁን ተጨፈኑ ላሞኛችሁ ነው።
ለማንኛውም ይህ የኀልውና ትግል ግንባረ ብዙ መሆኑን ባለፉት ሦስት ዓመታት በተከታታይ ጽሁፎች፣ ሰነዶች ለማመላከት ሞክሬለሁ።
የአማራ ህዝብ ዘረፍ ብዙ የጦር ግንባር ተከፍቶበታል። ሁሉም ግንባር የአገር ባለቤትነትን ላለማጣት የሚደረግ የኀልውና ትግል ነው።
እናም ለመገንጠል የሚዋጋ ኃይል የአማራ የትግል አጋር ሊሆን አይችልም!!
ለወያኔ የትርፍ ስሌቱ አራት ኪሎ ሳይሆን ተከዜ ነው። አልፋና ኦሜጋው ኮሪደሩ ነው!!
እናም ይህን መልዕክት ድጋሜ ላስተላልፍ
የኀልውና ትግሉን የምትመሩ ወንድሞች ከታሪካዊ ስህተት ራሳችሁን ጠብቁ። የማኀበራዊ ሚዲያ ግርግር አይታችሁ አትወስኑ። ማንም የሕዝብን ስትራቴጂካዊ ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ የለም… ብሄርተኛ መሆን ማለት objective reality መረዳት ነው። በእጅ የገባ ነገር መልሶ አይጣልም!!
ታዋቂው የእስራኤል ወታደራዊ ልሂቅ ሞሼ ዳያን በተናገረው አባባል ፅሁፌን ልደምድም፦
“አሜሪካውያን ገንዘብ፣ ጦር መሣሪያና ምክር ሰጡን፤ ገንዘቡን ወሰድን፣ የጦር መሣሪያውን ወሰድን፤ ምክሩን ግን አልተቀበልንም”
ከወያኔ የሚወሰድ ምክር የለም!!
@highlight
----------
ከMulualem G. Medhin የፌስቡክ ገፅ
8 778
"የትናንቱ ህወሓትና የዛሬው ህወሓት ይለያያሉ" ❓
መሳይ ጥልቅ ጥናት አድርጎ ሲያበቃ ተምብሌን አደረገው 😂
( ጎበዝ ...ኔጌቲቭ IQ አለ ለካ ! ይኼውናላችሁ መሳይ መሲ 😂)
8 778
ይሄ ነገር የት ደረሰ ?
ወንጀለኞቹ ተያዙ ወይስ "በዘመድዬ ዘመድዬ" ላሽ ተባለ ?
ወንጀለኞቹ ተይዘው ለህግ ካልቀረቡ እንዲሁ በዋዛ የምንፋታ አይመስለኝም ።
8 778
ሞንጆሪኖ እውነቷን ነው ።ድሮን ድምፅ የላትም ፤ በአንፃሩ የሚግ ድምፅ ይረብሻል 😂😂
//....በውዝፍ የቆየውን መንግስታችንን ለመመለስ ስብሰባ ላይ እንዳለን አቢይ ስብሰባችንን ለመረበሽ ሞክሮ ነበር።ድሮን ቢልክ እኮ አንድ ነገር ነበር።ሰዉ ተደናግጦ ከአዳራሹ እንዲበተን አስቦ ሚግ ነው የላከብን ....//
- የትናንቱ የፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) ንግግር ጭብጥ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
