es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 334 suscriptores, ocupando la posición 2 646 en la categoría Bloques y el puesto 2 341 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 334 suscriptores.

Según los últimos datos del 27 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -107, y en las últimas 24 horas de 3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 35.85%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.04% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 139 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 726 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 31.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 28 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 334
Suscriptores
+324 horas
-197 días
-10730 días
Archivo de publicaciones
አካውንቴ ስለተዘጋ ፌስቡክ ላይ ሼር አድርጉልኝ! ከአክብሮት ጋር
አካውንቴ ስለተዘጋ ፌስቡክ ላይ ሼር አድርጉልኝ! ከአክብሮት ጋር

ለአማራዎች አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ➜የመንግሥትን ቆራጥ ውሳኔ ሲጠብቁ የነበሩ የሰሜን እዝ አባላት ግብዓተ መሬታቸው ተፈጽሟል፡፡ ➜የመንግሥትን ትዕዛዝ ሲጠብቁ የነበሩ የምዕራብ እዝ አባላት በላካቸው አካል ዳተኝነት በሕዝብ ተገድለዋል፡፡ የተወሰኑትም ተማርከዋል፡፡ ➜በመንግሥት ፉከራ ተማምነው ህውሓትን ሲታገሉ የነበሩ አንዳንድ የአድግራትና የመቀሌ ተወላጆች መንግሥት ባደረገው የተናጠል ተኩስ አቁም ያለምንም ማስጠንቀቂያ ሜዳ ላይ ጥሏቸው ስለወጣ ለሞትና ለስዴት ተዳርገዋል፡፡ ➜በመንግሥት ቃላት እና በአካባቢው በሚያየው ሠራዊት እምነት አሳድሮ የተቀመጠው የኮሮም እና የራያ ሕዝብ ባላሰበው ቅጽበት በተፈጸመበት ክህዴት ከአሸባሪው እጅ እንዲወድቅ ተደርጓል፡፡ ስለሆነም… ዛሬ ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ ደብረ ብርሐን፣ ፍኖተ ሰላም፣ ደብረ ማርቆስ፣ ወረታ፣ አዲስ አበባ.... ተቀምጠህ በዚህ መንግሥት ንግግርና ዲስኩር ተስፋ የምታደርግ አማራ የነገ እጣ ፈንታህ ከላይ ከተዘረዘሩት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ የሰሞኑን እንኳን ብትመለከት በከባድ መስዋዕትነት ከእጅህ ውስጥ የገቡ ድሎችን የሚያሳጣህ መንግሥት የምትለው አካል እንጂ ህውሓት እንዳይመስልህ፡፡ እናም ስለ አገር ቀጣይነት ማሰቡን እና የመንግሥትን መግለጫ መጠባበቁን ትተህ የእራስህን ሕልውና በእራስህ እጅ ለማስከበር ማቄን ጨርቄን ሳትል መነሳት አለብህ፡፡ ➜አባቶቻችንን ለኢትዮጵያ ህልውና ማይጨውና ካራማራ ላይ ተሰውተዋል፡፡ ➜ወንድሞቻችን ለትግራይ መሬት ባድሜና ሽራሮ ላይ አልፈዋል፡፡ ➜እኛ ደግሞ ለእራሳችን ማንነት፣ ለእራሳችን ቀጣይነት ብሎም ለእራሳችን መሬት ወልቃይትና ራያ ላይ ታግለን ድል እናደርጋለን፡፡ (የፌስቡክ አካውንቴን ተረባርበው ስላዘጉት ይሄንን ፖስት ፌስቡክ ላይ እንዲትለጥፉልኝ አደራ እላለሁ፡፡)

አማራዬ:- ➜የእድሜ ልክ ጠላቱ ያደረገህ ➜በሐሰት ትርክት ከወንድሞችህ ጋር የሚያጣላህ ➜ማንነትህንና መሬትህን ነጥቆም 27 ዓመት ሙሉ የበደለህ ➜አሀዳዊ፣ ነፍጠኛ፣ ትምክህተኛ የሚልህ ➜የአማራ ኤሊት
+1
አማራዬ:- ➜የእድሜ ልክ ጠላቱ ያደረገህ ➜በሐሰት ትርክት ከወንድሞችህ ጋር የሚያጣላህ ➜ማንነትህንና መሬትህን ነጥቆም 27 ዓመት ሙሉ የበደለህ ➜አሀዳዊ፣ ነፍጠኛ፣ ትምክህተኛ የሚልህ ➜የአማራ ኤሊት ላይ የማወራርደው ሒሳብ አለኝ እያለ የሚዝትብህ ➜ባላንጋራህን እያደራጄ በየስፍራው እንደ ውሻ የሚያስገድልህ ➜መተኛም ሆነ መቀመጫ ያሳጣህ.... ያ የተረገመ እባብ በሐሺሽ ተገፋፍቶ ቀየህ ድረስ መጥቶልኻልና በተለመደው የአባቶችህ ፉከራ... ከራያ አንስቶ እስከ ሑመራ እርሳስ ጠርጣሪ እንደ ሽንብራ" .... እያልክ አናት አናቱን ቀጥቅጠው። እንደሚያጨሰው ሐሺሽ አመድ አድርገው። ትናንትና በማይጠብሪ "ጌታቸው ረዳ ጌታ ይይልህ" እያለ እስኪያሸልብ ድረስ ለወሬ ነጋሪ ሳታስተርፍ ዱቄት እንዳደረግከው ሁሉ በሌሎች ግንባሮችም መቃብሩን ቆፍረህ ጠብቀው። ድል ለአንተ!!

photo content
+1

በአጤ ዮሐንስም ሆነ በአቶ መለስ ላይ ካንተ በላይ ክህዴት የፈጸመ የታሪክ ሌባ አለ እንዴ? አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ የአማራ ሕዝብ እንደ አገር የተሠራን ገድል ‹‹የእኛ›› ብሎ ከመቀበል ባለፈ የእኔ እና የአንተ እያለ የሚደለድል ሕዝብ አይደለም፡፡ ለብቻው ከተሰጠው ታሪክ በተጨማሪ እንደ አገር የሚጋራው ገድል ያለው ሕዝብ ደግሞ የታሪክ እጥረት ስለማያጋጥመው የታሪክ ስርቆት ውስጥ አይገባም፡፡ በመሆኑም ‹‹አክሱም የኔ ነው›› ስትለው ‹‹የእኛ ነው›› ብሎህ ታቦቱን ሊሳለም ይመጣል፡፡ ሐውልቱን ይኮራበታል ፡፡ ደብረ ሊባኖስን ይመንንበታል፡፡ ቁልቢን ይሳልበታል፡፡ አልነጃሽን ይሰግድበታል፡፡ አንተ አጼ ምኒልክ ያልቆረጠውን ጡት ፍለጋ የታሪክ ድርሳናትን ስታገላብጥ፣ እሱ ከአጼ ዮሐንስ ታሪክ ላይ ስለ ሽንፈቱ እና ስለ አንገቱ የሚያወራውን አንቀጽ መሰረዝ ያምረዋል፡፡ ሽንፈትህን እንደ ሽንፈቱ፣ ድልህን እንደ ድሉ ቆጥሮ ተሸነፍን ወይም ደግሞ አሸነፍን ይልኻል፡፡ . ሌላውን ተወውና ስለ አጼ ዮሐንስ እና ስለ መለስ ብናወራ እንኳን... ‹‹የብቻዬ ናቸው›› እያልክ ከምታናፋው ከአንተ ይልቅ በእኛ ልብ ውስጥ በጎ ታሪካቸውም ሆነ አስተምህሯቸው ነፍስ ዘርቶ ታገኘዋለህ፡፡ በመሆኑም... እኛ ‹‹ኢትዮጵያ እናትህ፣ ሚስትህ፣ ልጂህ ናት...›› የሚለውን የአጼ ዮሐንስ አስተምህሮ ወርሰን ኢትዮጵያን ‹‹እናቴ›› ስንላት አንተ ግን ‹‹ጠላቴ›› ብለህ ፍርሰቷን ትመኛለህ፡፡ ንጉሡ የተዋጋላትን እና ሕይወቱን የሰጣትን አገር ክዴህ የንጉሡን አንገት ከቆረጠችው አገር ጋር አንገት ለአንገት ተቃቅፈህ ትወጋታለህ፡፡ አጼ ዮሐንስ በስናይዳር እየቆላ ድባቅ ሲመታት በኖረችው አገር አገርህን ድባቅ ለማስመታት ከምሥር ጋር ታሤራለህ፡፡ አገር ሲቀልስ በኖረው በራስ አሉላ ሥም የአገር ማፍረስ ዘመቻህን ትሰይማለህ፡፡ . ስለ መለስ ዜናዊም በግሌ ሳስብ ኢትዮጵያን በዘር መከፋፈሉን እና አማራ ጠል መሆኑን ጠንቅቄ ባውቅም ያደረጋቸውን መልካም ነገሮች ግን ልክዳቸው አልችልም፡፡ ስለሆነም በውጩ ማሕበረሰብ ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት ያላት አገር በመፍጠሩና የዓባይን ግድብ በማስጀመሩ አደንቀዋለሁ፡፡ በአጼ ምኒልክ ዘመን የተፈረመውን የቅኝ ግዛት ውልም ድባቅ የመታበትን ሎጂክ ልረሳው አልችልም፡፡ የአማራ ሕዝብም ቢሆን በመለስ ዘመን ከተደረገበት ይልቅ የተደረገለትን በማሰብ ሲሞት ከማልቀሱም በላይ ያስጀመረውን ግድብም ‹‹እንደጀመርን እንጨርሰዋለን›› በሚል አስተሳሰብ ለአሥር ዓመታት ያህል ግብጽን በንቃት እየተጠባበቀ ቦንድ ሲገዛ ኑሯል፡፡ -ያንተው ሜቴክ ግን መለስ ሲሞት ፕሮጀክቱን ትቶ በጀቱን ጨርሶት አረፈ፡፡ -ያንተው ህውሓት ግን የመለስን ሕልም በማሳካት ፈንታ ግድቡን በማጓተት የሥልጣን ቆይታዋን ታረዝምበት ያዘች፡፡ እኛ አማራዎች ስንገደልበት በከረምነው ክልል ውስጥ የተሠራው ግድብ ውሃ መያዙን ሰምተን ደስታችንን ስንገልጽ፣ ሲገድለን የከረመው ያንተው ኦነግ ግን ከግብጽ ጋር ተባብሮ ግድቡን ለማስተጓጎልና የኦሮሞ ተወላጅ የሆነውን ጠ/ሚር ለመፈንቀል እየተፍገመገመ ነው፡፡ እኛ አማራዎች የትግራይ ተወላጅ በሆነው ጠ/ሚኒስትር ተጀምሮ በዶክተር ዐቢይ ዘመን በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን ግድብ በኢትዮጵያ እሳቤ ተጋርተን ግድቡንም ሆነ መሪዎቹን የእኛ በማለት ደስታችንን ስንገልጽ ያንተው ትሕነግ ግን የመለስን ግድብ የሚደበድብ የአልሲሲን ቦምብ አንጋጦ እየተመለከተ ነው፡፡ የእኛ ዲያስፖራዎች የጸጥታው ምክር ቤት ለግብጽ ወግኖ አገራቸው ላይ ማዕቀብ እንዳይጥል ሲሟገቱ ያንተዎቹ ግን ስለ መለስ ግድብም ሆነ የእርዳታ ስንዴ ስለሚጠብቀው ሕዝብ ማሰብ ተስኗቸው በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል እየወተወቱ ነው፡፡ እናስ አቶ መለስንም ሆነ አጼ ዮሐንስን፣ አገራቸውንም ሆነ ታሪካቸውን የካድክ አንተ ወይስ እኛ? በሥማቸው እና በብሔራቸው ከመኩራት ባለፈ የትኛውን በጎ ሕልማቸውን ወይም ደግሞ ታሪካቸውን ወርሰህ ነው ታሪክህን የምንሰርቅህ?

የዓባይ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት ➖➖➖➖➖ ➜ነሃሴ መጨረሻ ላይ በሁለቱ ተርባይኖች 700 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ➜በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ በየዓመቱ የሚያስገኝ ➜ግብጽና ሱዳን ከትሕነግ ባንዳዎች ጋር የጀመሩትን ግንኙነት የሚበጣጥስ፤ ➜18 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃ ይዞ ለመስኖና ለዓሣ እርባታ መዋል የሚችል ሐይቅ የሚፈጥር ➜የምዕራባውያንን ፍርዴ ገምድል ተጽዕኖ ድባቅ የሚመታ ➜በአገራዊ ፕሮጀክት የመበልጸግ አቅም እንዳለን የገለጸ ➜የሦስት ሺህ ዘመን የግብጽን ሥጋት እውን አድርጎ ተስፋ ያስቆረጠ ➜የዓባይን ጎርፍ የማደሪያ ስፍራ ከሜዲትራሊያ ወደ ኢትዮጵያ ያዛወረ ➜በዓባይ ፖለቲካ ላይ የግብጽን ሚና ቀምቶ ለእናት አገሩ የሚሰጥ 💪 በዚህ ዜና ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊደሰት ይገባል። ባንዳም ጭምር!

photo content

አማራ፦ ➖➖ ➜በተመረዘ ውሃ ጤናው ሲቃወስና አትምጣብን እየተባለ ሲመለስ የከረመን ሠራዊት በፍቅር ተቀብሎ "ከፍትፍቱ ፊቱ" እያለ የሚያጎርስ ሕዝብ ያለው፤ ➜መንግሥት ሲዳከም በሽግግር መንግሥት ሥም
+2
አማራ፦ ➖➖ ➜በተመረዘ ውሃ ጤናው ሲቃወስና አትምጣብን እየተባለ ሲመለስ የከረመን ሠራዊት በፍቅር ተቀብሎ "ከፍትፍቱ ፊቱ" እያለ የሚያጎርስ ሕዝብ ያለው፤ ➜መንግሥት ሲዳከም በሽግግር መንግሥት ሥም ጠልፈው ለመጣል በማሰብ ፈንታ መንግሥትን ደግፈው አገርን ማሻገር በሚሹ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሚታወቅ፥ ➜ለመከላከያ ሠራዊቱ ደጀን ሆኖ የትኛውንም አገራዊ ጠላት የሚያንኮታኮት ልዩ ሃይልና ታጣቂ ያለው፤ ➜ኢትዮጵያን ያንጠለጠለ ፖርቲ ሁላ ባያሸንፍ እንኳን እንዳሻው የሚንቀሳቀስበትና የሚፈነጭበት ክልል የመሠረተ፥ ➜በግብር ከፋይነታቸው እና በበጎ አድራጎት ተግባራቸው የሚታወቁ ባለሃብቶች ያሉት፥ ➜መሪዎችን በብሔራቸው ሳይሆን በአገራዊ ፍቅራቸው የሚመዝኑ ሕዝቦች የያዘ ➜በክልሉ ውስጥ እውነተኛ ፌደራሊዝም በማስፈን ብሔረሰቦችን በልዩ ዞን አደራጅቶ ማንነታቸውንና ቋንቋቸውን ያስከበረ፥ ➜ከየትኛው ብሔር የወጣ የአገር መሪ ኢትዮጵያን የማፍረስ እቅድ ከሌለው በስተቀር ይሄን ሕዝብ የሚጠላበት ምክንያት ሊያገኝ የማይቻለው፥ ጨምሩበት

ከአንድ ወታደር የተላከ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ከርቀት ስትታዘበው- ተከዜ ወንዝ የሚመስል- በከርሱ ውሃ የያዘ፤ ተሻግረኽ ስትጠጣው ግን- ከባሩድ በላይ የሚገድል- በሄምሎክ የተመረዘ፤ ሸለቆው ማዶ ቁጭ ብ
+1
ከአንድ ወታደር የተላከ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ከርቀት ስትታዘበው- ተከዜ ወንዝ የሚመስል- በከርሱ ውሃ የያዘ፤ ተሻግረኽ ስትጠጣው ግን- ከባሩድ በላይ የሚገድል- በሄምሎክ የተመረዘ፤ ሸለቆው ማዶ ቁጭ ብለህ- ባሻገር ያለውን ጋራ- አድማሱን ስታስተውለው፤ አልፈኸው እስክትሄድ ድረስ- ሐኖሱ ድባቡ ሁላ- እናት ኢትዮጵያን መሳይ ነው፤ ‹‹ይሄ አገር ማን ነው›› የምትል- ወንዙን ስትሻገረው፣ መርዙን ስትጎነጨው፤ ጉድ ነው! . አገሬ ልንገርሽማ፥ ምን ምን እንዳጋጠመኝ- ስሚማ በመይሳው ሞት ሕይወቴ ያንቺ ሆኖ ሳለ- ስሜቱን ከሥሙ ጋር- ለእኔ የሰጠ ድርጅት ከሴት ደፋሪ መድቦኝ- ሥሜን እንደ ጥጥ ሲያባዝት ያንን የሰሜን አርበኛ- ከአንበጣ ተርታ መድቦ- ጨፍጭፎ ያደረ ባንዳ፤ ከዝንጀሮ ጋር ሸምቆ- ሌባ ዘራፊ እያለ- ሲነዛ ፕሮፖጋንዳ፤ ቄስሽ መስቀሉን ጥሎ- ቦንብ ታቅፎ ሲንጋጋ በምሞትለት ስጠቃ- በምዋጋለት ስወጋ፤ ደፍረውኝ እንደ ደፋሪ- ሰልበውኝ እንደ ሰላቢ ክደውኝ እንደ ከሃዲ- ወግተውኝ እንደ ደብዳቢ ሶሪያ እንደተገኘ- ሰማይ ሰማዩን እያየሁ- ስልልሽ ‹‹ያላህ ያረቢ›› አክሱም ጽዮንን አጥፍቶ- ለደብረ ጽዮን የሚሰግድ፤ የሚረዳኝ ብቸኛ ጌታ- ጌታቸው ረዳ ነው ብሎ- እግዜር አላሁን የሚክድ፤ ሲገድል ጀጋኑ የሚባል- ሲሞት ንጹሕ የሚሆን፤ ከተኩሶ ክሱ በርትቶ- ሲለቀልቀኝ እድፉን፤ ታጣቂ ካላየ በቀር- መባረቅ የማያሰኘው- መተኮስ የማይችል ክላሽ፤ መያዜን ያወቀ ውርጋጥ- ተኩሶ ከሸሼ ወዲያ- እኔን ሲያደርገኝ ተከሳሽ፤ እናም እናታለሜ- እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም- ነፍሴን ልሰጥሽ ወጥቼ ጠላትሽን ከመታሁ ወዲያ- እያነባሁ ነው የወጣሁ- ምድሩ ላይ አንቺን አጥቼ፡፡

"ፈርዖን እስራኤላዊያንን ተከትሎ ባይመጣ ኖሮ ከመላው ሠራዊቱ ጋር በኤርትራ ባሕር ሰምጦ አይቀርም ነበር። ልክ እንደዚሁ ሁሉ ትሕነግም ኢትዮጵያውያንን ተከትሎ የሚመጣ ከሆነ ሰምጦ የሚጠፋበት ባሕር "ተከዜ" ይሆናል።" እየመዘገባችሁ!! 😁

አልጋው አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ባሁኑ ሰዓት "ፋሚሊ" የሚባለው የሽቦ አልጋ የሰው ማረፊያ መሆኑ ቀርቶ የአሽዋ መንፊያ ቢሆንም እኔ ግን ‹‹ቅርስ አልሸጥም›› ብዬ እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ ስነፋበት ነበር። ይሄውም አልጋ ሽቦው በጣም የረገበ በመሆኑ 80 ኪሎ ሰውነቴን ሳሳርፍበት አርባ ኪሎ ሚስቴን ከላዩ ላይ ገልብጦ እንደ አንሶላ እኔ ላይ ይደርባታል፡፡ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ወደ ትግል ስገባም አልጋ ላይ ሳይሆን አይጥ ላይ የተኛን ይመስል ‹‹ሲጥ ሲጥ›› የሚል ድምጽ ሲያወጣ ቆይቶ ጸጥ ይላል፡፡ በዚህን ጊዜም ከእኛ ስር ያለውን ኮንዶሚንየም የተከራየው ሰካራም ወንደላጤ ‹‹አስጨርሱኝ›› እያለ ይጮኻል፡፡😁 እሜቴ ‹‹ይሄን አልጋ እንቀይረው›› ባለችኝ ቁጥር የምሰጣት መልስ ‹‹መንግሥት ከተቀየረ በኋላ እንቀይረዋለን›› የሚል ነው፡፡ ‹‹መንግሥት ካልተቀየረስ?›› ብላ ስትጠይቀኝም ‹‹መንግሥት ካልተቀየረማ ለየትኛው እንቅልፍ ብለን ነው አልጋ የምንቀይረው?›› የሚል መልስ እሰጣታለሁ፡፡ ይሄን የምላት ታዲያ ወሬ ለማሳመር አይደለም፡፡ በፕሮጀክት ሥልጠናዎችና ስብሰባዎች ላይ ስሳተፍ ባለ ኮከብ ሆቴል ውስጥም አድሬ ስለሞከርኩት እንጂ… በእነዚያ ጊዜያትም፣ ምቾት እና ውበት ካለው ዘመናዊ አልጋ ላይ ተጋድሜ የፌስቡክ አካውንቴን ስከፍተው እንደኔ ሽቦ አልጋ የሚወዛወዘው መንግሥት የሆነ ሥጋትና ጥቃት ተሸክሞ ይመጣና እንቅልፌን ገፍትሮ እንደ እሜቴ እቅፍ ያደረግኛል፡፡ ያን ጊዜም ለአንድ አዳር መለስተኛ አልጋ መግዛት የሚያስችል ብር የተከፈለበት አልጋ ላይ ቁጭ ብዬ አጎዛና ዠንድ ላይ የተኛውን ሕዝብ ‹‹አትነሳም ወይ›› እያልኩ ስቀሰቅስ ሌሊቱ ይነጋል፡፡ በዛሬው እለት ታዲያ ወደ ሰሚት ሄጄ ጥፋት ስፈጽም ከዋልኩ በኋላ ሚስትን ማታለል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ጎግል እያደረግኩ ወደ ቤቴ ስመለስ…. አዲስ በገዛችው አልጋ ላይ ፒኪኒ ለብሳ የተጋደመች ባለቤቴ ‹‹ባልን ለማማለል የሚረዱ ወሳኝ ምክሮች›› የሚል አርቲክል የያዘ መጽሔት እያነበበች አገኘኋት፡፡ በሚያምር ዘመናዊ አልጋ ላይ የተዘረረች ጥንታዊ ሚስቴን ስመለከትም፣ በመማለል ፈንታ በአዲስ ዙፋን ላይ አሮጌውን ኢህአዴግ ሳገኝ የተሰማኝን ስሜት አስተናግጄ ወደ ሳሎን ልመለስ ስል ‹‹አዲሱን አልጋ መርቀው እንጂ›› በማለት ተናገረች፡፡ ይሄንንም ስትለኝ የብአዴን አመራር መጥራት ባለመቻሌ ቅር እየተሰኘሁ ጠረጴዛ ላይ ያስቀመጠችውን መቀስ አንስቼ ባለ አበባ ፒኪኒዋን በመቁረጥ አገልግሎቱን አስጀመርኩ፡፡ ወደ እርሻ በገባን ጊዜም… አሳዬ ደርቤ፥ የአገኘሁ ተሻገር፥ የደመቀ አርሶ አደር ከጊደር ጀርባ ላይ፥ ማረሻውን ጠምዶ፥ ጠልቆ የሚቆፍር›› ከሚል ፉከራ ጋር እንደ ጊደር ጠምጄ ላርሳት ስል… ‹‹እኔ'ሳ ምን ልበል፥ የሽሜ እና የዐቢይ ፥ ሞደሏ ገበሬ ከባሕላዊ እርሻ- የወጣሁ ከበሬ›› ብላኝ በጊደር ፈንታ ትራክተር ሆና እላዬ ላይ ትሾር ጀመር፡፡ አንድ ዙር እርሻ ላይ እያለሁም፣ እሷ ሁለት ዙር ጨርሳ ሞተሯን ካጠፋች በኋላ ‹‹ጨርስና ልተኛበት›› እያለች ስትጨቃጨቅ ‹‹እንደ መገጭ ግድብ ስምንት ዓመት የምቆይ ይመስል እስከ ጧት ድረስ መታገስ እንዴት ያቅትሻል?›› እያልኩ ተንሸራትቼ ከወረድኩ በኋላ በእንቅልፍ ክኒን ፈንታ ተንሸራታች ሞባይሌን አንስቼ ሥጋት እሸምት ጀመር፡፡