es
Feedback
Disciples of Jesus

Disciples of Jesus

Ir al canal en Telegram

"ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀመዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከብራል" ዮሐ 15:8 #የዚህ ግሩፕ ዓላማ አማኞች አማኝ ብቻ ሆነው እንዳይቀጥሉ ነገር ግን ደቀመዝሙር እንዲሆኑ መርዳት ነው።

Mostrar más
363
Suscriptores
-224 horas
-47 días
-130 días
Archivo de publicaciones
ላለመጸለይ ከምናበዛቸው ምክንያቶች ይልቅ የእግዚአብሔር አስፈላጊነት ከበለጠብን በእግሮቹ ስር መገኘት ቀላል ይሆንልናል።

"የአደባባይ ሰው ሆነህ በየማዕዘኑ ላይ ቆመህ ሰውን አይተህ በሰው ታይተህ ሰውን አይተህ በሰው ታይተህ በስውር አይቶ በግልጥ የሚከፍልህን በከፍታ ላይ የሚያስኬድህን ረስተህ የለም ወይ አሳዳጊ ጌታህን። #በስውር_የሚቀመጡ #ጌታቸውንም_የሚያደምጡ #የሕይወትን_ቃል_የሚያመጡ #የሕይወትን_ቃል_የሚያመጡ #ሰውን_ለማነጽ_ነቅተው_የሚታጠቁ #ለበጎ_ስራ_ሁሉ_የሚበቁ #ምስጉኖች_ናቸው_መማለድን_የሚያውቁ። ከእግዚአብሔር የተላከ እርሱ ነው የተባረከ ቃሉን ብቻ የሰበከ ቃሉን ብቻ የሰበከ አንተንስ ማን ነው አስነስቶ የላከህ? በፍጻሜው ላይ ትጠየቃለህ እንደ ስራህም ያኔ ትከፈላለህ። ስራህ ድካምህ ብዙ ነው አንተነትህን ያጎላው ጌታ እንዳይታይ የጋረደው ጌታ እንዳይታይ የጋረደው እስቲ በእውነት መርምረው ሕይወትህን መጸለይ ትተህ መራቆትህን ኢየሱስን ጋርደህ አንተ መታየትህን። ስማው ኢየሱስ ይመክርሃል ተው እረፍ ጸልይ ይልሃል ከእግሮቹ ስር ሥጋህን ጣል ከእግሮቹ ስር ሥጋህን ጣል። ያን ጊዜ ጌታ ከሰገነት ላይ ወጥቶ ለዓለም ይታያል ብርሃኑ በርቶ ሕይወት ይበዛል የስንዴው ቅንጣት ሞቶ።" በጓዳ በእግዚአብሔር ፊት በመጽናት፣ በጸሎት ብዙ በአደባባይ ላይ የሚታዩ ስራዎቻችን ተሰርተው ያልቃሉ። በአደባባይ ከምንገለጥበት ጊዜ ይልቅ በጓዳችን በእግዚአብሔር ፊት የምናሳልፈው ጊዜ የድል ሁሉ ምንጭ፣ የመፍትሄ መገኛ ነው። ወደ አደባባይ ከምንዘረጋበት ጊዜ ይልቅ ለመንበርከክ እና ለምልጃ እንፍጠን፤ በዛ ድል አለ። በስውር የሚያይ አባታችን በግልጥ ይከፍለናል። የአደባባይ ሰው ሆነን በጓዳ ከመስነፍ ጌታ ይጠብቀን፤ የምንተጋበትን ጸጋ ያብዛልን! “አንተ ግን ስትጸልይ ወደ ክፍልህ ግባ፤ በሩንም ዘግተህ በስውር ወዳለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የተደረገውን የሚያይ አባትህም ዋጋህን ይከፍልሃል።” ማቴዎስ 6፥6 (አ. መ.ት)

ከእልፍኝ ይልቅ ደጅ ደጁን ማብዛታችን የመጠውለግ፣ የመድረቅ፣ ፍሬ የማጣታችን ዋና ምክንያቱ ነው። በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ካልጠነከረ የውስጥ ሰውነት የሚፈስ የአደባባይ ሕይወት፣ አገልግሎት ፍሬአልባ ነውና በእልፍኝ በመቆየት፣ ከእግዚአብሔር ጋር በመሰንበት፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በውስጥ ሰውነታችን በመጠንከር የአደባባይ ሕይወታችንን፣ አገልግሎታችንን የፍሬ እናድርግ። ለእግዚአብሔር አብዝቶ መገኘት መቼም ቢሆን አያከስርም። እረፍት፣ ብርታት፣ ትርፍ፣ ፍሬ ያለው፦ ሳይታክቱ፣ ገና እንዳልያዙት በመቁጠር ወደ እግዚአብሔር በመገስገስ፣ ወደ እርሱ በመዘርጋት ውስጥ ነው።

. ⭐ዘማሪ አውታሩ ከበደ ⭐ 02. በመንፈስህ ክብር NEW ALBUM sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ ማርከን ዜማ @Markenzema_bot በዚህ ቻናል የማይደመጥ መዝሙር የለም ብቻ ምን አለፋችሁ join ይበሉ 👇 https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp https://t.me/+S2wsmZMSQp3vcGxp

በክርስትና ሕይወታችን ውስጥ ትልቁ ድልና፣ ዕለት ዕለት ሕያው ሆኖ የመሰንበት ምስጢር ያለው ይሄ ሕይወት በማን እና በምን እንደሚኖር በማወቅ እንዲሁም በእርሱ በመኖር ውስጥ ነው። የክርስትና ምልልስ ሕያውነት ያለው በኢየሱስ በመኖር፣ ዘወትር በመንፈሱ ውስጥ በመገኘት ነው። ይሄ እውነት ሲገባን በሕይወት ወደሚያኖረው፣ ሁለንተናን አለምልሞ ወደሚያቆየው ወደ እርሱ ለመገስገስ ስፍስፍ እንላለን። እርሱ የሕይወት፣ በሕይወት የመሰንበት ክልላችን ነውና በእርሱ መገኘት ውስጥ ለመስጠም አለ የተባለ አቅማችንን ሁሉ አሟጠን እንጠቀማለን፤ ያለንን ጊዜና ዕድል ሁሉ ከእርሱ ጋር ለመቆየት እንበጅታለን። አሣ የሕያውነት ክልሉ ከሆነው ከውሃ ለመውጣት በቀረበ ልክ ወደሞት እየገሰገሰ ነው፤ በሕይወት ለመቆየት የሕያውነት ክልሉ በሆነው በውሃ ውስጥ መሰንበቱ የግድ አስፈላጊ ነው። ለእኛም ኢየሱስ የሕያውነት ክልላችን፣ የሕይወት ወሰናችን መሆኑ ሲገባን በሕይወት ለመኖር፣ ሕያው ሆኖ ለመቆየት በእርሱ መሸሸግን፣ መሸፈንን፣ መሰንበትን እንዴት እናበዛ ይሆን?!

. ሰላም ደስታ አልደራደርም ሙሉ አልበም ውድ ያድረግከኝን አንተን ውዴ እንዳደርግህ ከክብርህ በላይ የወደድከኝን እንድወድህ ፀጋ በረዳኝ መጠን እንድቀርብህ እኔም እሻለሁ የ እውነቴን ልወድድህ @DofJ3 @DofJ7

. ሰላም ደስታ አልደራደርም ሙሉ አልበም ▷ @markenzema_bot ◁ ▷ @markenzema_bot ◁ △Join Us△

ልባችን የእግዚአብሔር ወዳጅ ከሆነልን፣ አብሮት ከሰነበተ እግዚአብሔር የእርሱ የሆነውን የሚያፈስበት፣ የሚዘራበት፣ የሚገልጥበት ምቹ ስፍራ ይሆናል።

"ኃጢአትን ባትሰራ መልካም ነው ፤ ኃጢአት ከሠራህ ሳትቆይ ንስሐ ብትገባ መልካም ነው። ንስሐ ከገባህ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ባትመለስ መልካም ነው። ወደ ኃጢአት ካልተመለስክ ይህ በእግዚአብሔር ዕርዳታና ቸርነት መሆኑን ብታውቅ መልካም ነው። ይህንን ካወቅህ ስለአለህበት ሁኔታ እግዚአብሔርን ብታመሰግን መልካም ነው። " #ቅዱሱ ሰብ ባስልዮስ

+++ "ስንሞት ያመናል እንዴ?" +++ ሕፃናት መጠየቅ ይወዳሉ። አንዴ መጠየቅ ከጀመሩ በኋላ ደግሞ ከእነርሱ የሚወጣው "ለምን ሆነ?" የሚለው የጥያቄ ዝናብ እንዲህ በቀላሉ ቶሎ የሚያባራ አይደለም። እኛም በእነዚህ ጥያቄዎቻቸው ቶሎ ተሰላችተን ወይም ተበሳጭተን ይሆናል። ይሁን እንጂ ጉዳዩ ግን የሕፃናቱ አዲስ አእምሮ ራሱን የሚያሳድግበትና የነገ ማንነታቸውን የሚቀርጽበት ወሳኝ ሂደት ነው። የነገ ወጣቶችን ማንነት የሚቀርጹት ዛሬ "ለምን?" እያሉ ለሚጠይቁ ሕፃናት የምንመልሳቸው መልሶች ናቸው። ስለዚህ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባናል። በጠና የታመመ ሕፃን ልጅ ያላት አንዲት እናት ነበረች። ይህች እናት በምትችለው ሁሉ ልጇን አሳክማና ተንከባክባ ለማዳን ብትጥርም፣ ይህ ልፋቷ ግን ሊሳካላት አልቻለም። ልጇን የያዘው በሽታ መድኃኒት ስላልነበረው ወደ ሞት አፋፍ አቅርቦታል። ታዲያ አንድ ቀን ሕፃኑ ልጅ እናቱን እንዲህ ሲል ጠየቃት :- "እናቴ፣ መሞት ምን ይመስላል? ስንሞት ያመናል እንዴ?" በእናትየው ዓይኖች እንባዎች ሞሉ። ፊቷም በኃዘን ደፈረሰ። የረሳችው ነገር ያለ ይመስል "ቆይ መጣኹ" ብላ ሮጣ ከክፍሉ ወጣች። ብቻዋን ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ልጇ የጠየቃትን ጥያቄ መመለስ እንዳለባት ብታውቅም ለዚህ ለጋ አእምሮ እንዴት አድርጋ መልስ እንደምትሰጥ ግራ ገብቷታል። እንደ ምንም ራሷን አረጋግታና ጥበቡን እንዲሰጣት ወደ ፈጣሪዋ ተማጽና ተመልሳ ወደ ልጇ ክፍል ገባች። ሕፃኑ መልሱን በጉጉት ይጠብቃል። እናትየውም የውስጧን ኃዘን ለመሰወር ለይምሰል ፈገግ ብላ እንዲህ አለችው "ልጄ፣ ታስታውሳለህ አንድ ጊዜ ጎረቤት ያለ ጓደኛህ ቤት ሄደህ ስትጫወት አምሽተህ ስለደከመህ በዚያው እንቅልፍ ወስዶህ ነበር። ከዚያም በማግስቱ ግን ስትነቃ ራስህ ያገኘኸው በመኖሪያ ቤታችን ውስጥ ስለሆነ 'እንዴት እዚህ መጣኹ?' እያልክ ስትጠይቀኝ ነበር። እኔም አባት ወደዚያ መጥቶ በጥንካራ ክንዶቹ ተሸክሞህ የአንተ ወደ ሆነው ቤትህ እንዳመጣህ ነግሬሃለኹ። አስታወስክ?" ልጅየው :- "አዎን እናቴ" እናትየው ቀጠለች :- "የኔ ልጅ፣ ሞትም እንደዚሁ ነው። እኛ መኖሪያችን ባልሆነች በዚህ ዓለም ሆነን እናንቀላፋለን። የሰማይ አባታችን እግዚአብሔር ደግሞ ብርቱ በሆኑ እጆቹ አቅፎ ወደ ሰማይ ይወስደናል። ከዚያም ነግቶ እንደ ገና ስንነቃ ራሳችንን በገዛ አባታችን ቤት ውስጥ እናገኘዋለን" አለችው። እውነት ነው! ሞት ለክርስቲያኖች ሁሉ የሚኖረው ትርጉም ይህ ነው። ከእግዚአብሔር ተልከን ወደዚህ ዓለም እንደ መጣን ወደ እርሱ መመለሳችን ደግሞ የማይቀር ነው። ሞት ማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ድንኳን" ብሎ ከገለጸው ከጊዜያዊው መቆያችን ወደ እውነተኛው መኖሪያ አገራችን መሸጋገር ነው። በ2ኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ግሪካዊው ፈላስፋ አርስጣደስ በጊዜው አዲስ ሃይማኖት ስለሆነበት ስለ ክርስትና እና ይህ የክርስትና እምነት በሞት ላይ ስላለው እሳቤ ለአንድ ወዳጁ በጻፈለት ደብዳቤ ላይ እንዲህ የሚል ንግግር አስፍሮ ነበር። "ከክርስቲያኖቹ ውስጥ አንድ ጻድቅ የሆነ ሰው ከዚህ ዓለም በሞት ቢለይ ምእመናኑ ደስ ይሰኛሉ። ለፈጣሪያቸውም ምስጋናን ያቀርባሉ። ያም ሰው ከአንድ ስፍራ ወደ ሌላ ቅርብ ሥፍራ የተሸጋገረ ይመስል ሰውነቱን በመዝሙራትና በምስጋና አጅበው ይሸኙታል" ይላል። ክርስትና እንዲህ ነዋ! ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ክርስቲያኖች በሞት ላይ ሊኖራቸው ስለሚገባ እይታ ሲናገር "ከእኛ መካከል አንድ ሰው በሞተ ጊዜ፣ የማያምነው ሬሳ ሲያይ ክርስቲያኑ ግን ያንቀላፋ ሰውነት ይመለከታል። ያላመነው "የሞተው ሰው ሄደ" ይላል። በርግጥ በዚህ እኛም እንስማማለን። ነገር ግን ወደ የት እንደሚሄድም እናውቃለን። የሚሄደው ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ጴጥሮስ እንዲሁም ሌሎች የቅዱሳን ማኅበር ወደ አሉበት ነው። በኋላም ተስፋ መቁረጥ ባለበት እንባ ሳይሆን፣ በክብርና በማንጸባረቅ እንደሚነሣ እናስባለን!" +++ "ለባሪያዎችህ ሞት የለባቸውም ፍልሰት እንጂ" +++ ዲያቆን አቤል ካሳሁን

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆Part 3 እና 4 ተከታተሉ

🛑Quite time 4🚨 ሰምታቹ👂 በማስታወሻ ጻፋ✍ ቀጥታ ወደተግባር🎬 የጻፋቹትን ፋቶ አንስቶ 📸 መልቀቅ እዳትረሱ 😡 ግዴታቹ ነው Share 👇share 👇share @DofJ7

🛑Quiet Time ልዩ ትምህርት👨‍🏫 መስታወት እንጂ🪞 መነጽር አደለም ራሳቹን ቃኙበት ትለወጣላቹ የማይሰማ እንዳይኖር 😡😡 @DofJ7

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆Quiet Time part one እና 2 ይቀጥላል

Repost from Disciples of Jesus
Mensaje de voz39:40