ለሙስሊሟ እህቴ
Ir al canal en Telegram
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ بسم الله الرحمن الرحيم በቻናላችን ዲናዊ እውቀቶች ስለሒጃብ ማብሪራያዎች ስለ ትዳር ምክሮች እናንተን ያዝናናል ያስተምራል የምንላቸው በአላህ ፍቃድ ለናንተ እናደርሳለን። ከናንተ ሚጠበቀው join ማረግ ነው። @lemuslimuaehte for any comment 👇 @fitayebot
Mostrar más2 645
Suscriptores
-224 horas
-87 días
-5030 días
Archivo de publicaciones
2 644
ደረሰኙን ሲያይ አለቀሰ!
~
አንድ የ78 ዓመት አዛውንት በድካም ምክንያት ወድቀው ሪያድ ወደሚገኝ አንድ የግል ሆስፒታል ተወሰዱ። ለ24 ሰዓታት ያህል የሚቆይ የኦክስጅን ድጋፍም ተሰጣቸው። ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ጤንነታቸው እየተሻሻለ ሲመጣ፣ ሐኪሙ የ600 ሪያል የክፍያ ደረሰኝ ሰጣቸው። አዛውንቱ ደረሰኙን ሲመለከቱ ማልቀስ ጀመሩ።
ሐኪሙም ስለ ገንዘቡ ብለው እንዳያለቅሱ ጠየቃቸው። አዛውንቱም እንዲህ ሲሉ መለሱ፡- "የማለቅሰው በደረሰኙ ላይ ስላለው የገንዘብ መጠን አይደለም፤ ይህንን ገንዘብ በሙሉ የመክፈል አቅም አለኝ። የማለቅሰው ግን ለ24 ሰዓት ብቻ ኦክስጅን ስለተጠቀምኩ 600 ሪያል መክፈል ስላለብኝ ነው። ነገር ግን ለ78 ዓመታት ከአላህ የተሰጠኝን ንጹህ አየር ስተነፍስ ኖሬ አንድም ቀን ምንም ከፍዬ አላውቅም... ለአላህ ምን ያህል ዕዳ እንዳለብኝ ታውቃለህን?"
ሐኪሙም ይህን ሲሰማ ራሱን ዝቅ አደረገ፣ እጅግም ተረብሾ አለቀሰ።
"አልሀምዱሊላህ" ክፍያ ሳንከፍል ስንት ዓመታትን ኦክስጅን ስንተነፍስ ኖርን? አላህን ሁልጊዜ የማመስገን አስፈላጊነትን ለመገንዘብ ጥቂት ጊዜ ወስደህ አስብ።
🤲 🤲اللهم لك الحمد والشكر ربي
👍 ለሌሎችም አጋራ፣ አጅር ታገኝበታለህ።
t.me/ibrahim_furii
2 644
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
በመጨረሻም‼
===========
✍ በሳዑዲ ዓረቢያ የሸዋል 1 ጨረቃ ዛሬ ረቡዕ ማየት ስላልተቻለ ነገ ሐሙስ መጋቢት 10, 2018 E.C. የረመዿን 30ኛ ቀን ማሟያ ይሆንና፣ ከነገ በኋላ ጁሙዓህ መጋቢት 11, 2018 E.C. ዒድ ይሆናል።
በሰላም ጹመን ለማጠናቀቅ ያበቃን አላህ ምስጋና የተገባው ነው። አል-ሐምዱ ሊላህ! ጾማቸውንና ዒባዳቸውን ከተቀበላቸው፣ ጎዶሏቸውን ከሞላላቸው፣ ወንጀላቸውን ምሮ ከእሳት ነፃ ካወጣቸው ባሮቹ ያድርገን።
ከወዲሁ ዒድ ሙባረክ‼
ተቀበለ-ል'ሏሁ ሚና ወሚንኩም ሷሊሓል አዕማል!
عيدكم مبارك
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
||
t.me/MuradTadesse
2 644
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
27ኛዋ ሌሊት!
~
ስለ ለይለተል ቀድር የትኛውም ቁጥር ቢገመት የ27ኛዋ ግን ይለያል። ከየትኛውም ሌሊት በተለየ ከፍ ያለ ግምት ይሰጣታል። ስለሆነም ለዚችኛዋ ሌሊት የበለጠ ትኩረት መስጠት ይገባል። ሶላት፣ ቁርኣን መቅራት፣ አዝካር፣ ድምፅን ዝቅ፣ ቀልብን ስብር አድርጎ ደግሞ ደጋግሞ በዱዓእ የሙጥኝ ማለት ያስፈልጋል። ኢኽላስ እና ኹሹዕ መዘንጋት የሌለባቸው ትጥቆች ናቸው። ባይሆን የሱብሕን ነገር አደራ! ብልጥ ነጋዴ ትርፍ ፍለጋ ወረቱን አይጥልም።
=
ቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
2 644
🔖ከመልካሞች ጋር መዋል ማለት ፣ንጹህ ሺቶ እንደሚቀባ ሰው ነው።ባታገኝ እንኳን ጠረናቸው አይለይህም።
~ያረብ ወዳንተ የሚያቃርብ ጓደኛ ፣ጎረቤት፣ በሁሉም ቦታ ላይ ወፍቀን።አንድ ንግግር ትዝ ይለኛል። من تجالس توارث ምንም ጠንካራ ብንሆን አቀማማጫችንን እንምረጥ።
~
t.me/https_Asselfya
2 644
عن أبي أُمَامَةَ الْبَاهِلِي رضي الله عنه قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ: اقْرَءُوا الْقُرْآنَ فَإِنَّهُ يَأْتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ شَفِيعًا لأَصْحَابِهِ... رواه مسلم (804).
ከአቡ ኡማማ አል-ባሂሊ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፈው፡- የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፡- "ቁርኣንን አንብቡ በትንሣኤ ቀን ለባልደረቦቹ አማላጅ ሆኖ ይመጣልና..." (ሙስሊም (804) ዘግበውታል::
هذا الحديث دليل على فضل تلاوة القرآن، وعظيم ثوابه وأنه شفيع لأصحابه يوم القيامة في دخول الجنة.
ይህ ሐዲስ ቁርኣንን መቅራት ያለውን ትሩፋት፣ የምንዳዉን ታላቅነት እና በትንሳኤ ቀን ለባልደረቦቹ እንደሚያማለድ ማስረጃ ነው።
2 644
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
FYI, ከነገ ከጥር 23 ጀምሮ ፌስታል ይዞ የተገኘ ሰው ከ2000 ብር እስከ 5 ሺህ ብር ይቀጣል ተብሏልና ገቢ ማስገኛ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ።
2 644
#ሴቶች_በጅሀነም_ውስጥ_ቅጣታቸው_ብርቱ_የሆነው_ለምድነው⁉️
👉አሊይ ኢብኑ አቡጣልብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳወሩት ነብዩ
صلي الله عليه وسلم
ወደ ሰማይ በለሊት ጉዞዋቸው የሴቶች ጀሀነም መብዛት እና በጅሀነም ውስጥ አሰቃቂ ቅጣታቸውን እንዲህ በማለት ገልፀውታል።
1⃣ በጀሀነም ውስጥ በምላሷ ተንጠልጥላ የምትቀጣ
ሴት ተመለከቱ ። ይች በምላሧ ተንጠልጥላ የምትቀጣዋ ሴት ባሏን አዛ የምታደርግ ሴት ናት አሉ።
2⃣ በጅሀነም ውስጥ በጡቷ ተጠልጥላ የምትቀጣ
ሴት ተመለከቱ ። በጡቷ ተጠልጥል የምትቀጣዋ ሴት
ለባሏ በፍራሺ ግንኙነት እንቢ ተኛ የምትል
ሴት ናት አሉ።
3⃣በጅሀነም ውስጥ በእግሯ ተንጠልጥላ የምትቀጣ
ሴት ተመለከቱ በእግሯ ተንጠልጥላ የምትቀጣዋ ሴት
ከባሏ ፍቃድ ውጭ ከቤት የምትወጣ ሴት ነች አሉ።
4⃣ በጂሀነም ውስጥ እጅ እና እግሯ የፊጥኝ ታስራ
እባብ እና ጊንጥ የሚበላት ሴት ተመለከቱ ይችም
ሴት ወዱዑ የማታስተካክል ንፅህናዋን የማትጠብቅ
ጀናባዋን የማትታጠብ በሶላት ላይ ዝንጉ የሆነች
ሴት ናት አሉ።
5⃣በጅሀነም ውስጥ አይነ ስውር ደንቆሮ ዱዳ ሁና
በእሳት ሳጥን ተይዛ አንጎሏ በአፍንጫዋ የሚፍስ ሴት
ተመለከቱ ። ይች ሴት በሀራም /በዚና የወለደችውን
ልጅ ለባሏ ያንተ ልጅ ነው ብላ የምትሰጥ ናት አሉ።
6⃣ በጀሀነም ውስጥ ከአናቷ እስከ እግሯ በእሳት
መጋዝ የምትሰነጠቅ ሴት ተመለከቱ ። ይችም ሴት
ዝሙተኛ/ በሀራም ወንዶችን ስታሳድድ የነበርች
ሴት ነች አሉ።
7⃣በጅሀነም ውስጥ አካሏ የአህያ እራሷ የአሳማ
እና የጂሀነም እሳት በተለያዩ ቀለማት የሚነዱባት ሴት
ተመለከቱ። አካሏ አህያ እራሷ አሳማ የመሰለችዋ ሴት
ውሸታም እና ወሬ አመላላሽ ነሚማ የሆነች
ሴት ናት አሉ።
8⃣በጆሀነም ውስጥ በውሻ አምሳል ተመስላ
በፊንጥጣዋ እሳት እየገባ በአፏ የሚወጣ ሴት
ተመለከቱ ። ይችም ሴት ደግሞ ዘፋኝ አስለቃሽ
የሆነች ሴት ናት አሉ።
🔴👉እህቶች ከሞት ማምለጥ የለም ስለዚህ ከነዚህ እራሷችሁን ጠብቁ።
2 644
ያኔ ድሮ... ረመዳን ገና በሩቅ ሲታሰብ፣ ናፍቆቱ ከወራት በፊት ልብን ያንኳኳ ነበር። አየሩ፣ ሰፈሩ፣ የሥራ ቦታውና ትምህርት ቤቱ ሁሉ 'ረመዳን! ረመዳን!' ይሸት ነበር።
እናቶቻችን ወገባቸውን ታጥቀው፣ ቤታቸውን አሰናድተው የረመዳንን መዓዛ ቀድመው ያሸቱን ነበር። መስጂዶችም ቢሆኑ ግድግዳቸው ሳይቀር ናፍቆት ይታይባቸው ነበር።
ዛሬ ግን... ዛሬ ልባችን በዱንያ ትቢያ የደረቀ ይመስላል። እንግዳው በር ላይ ደርሷል፤ ተቀባዩ ግን የለም። ቀደምት ደጋግ ሰለፎች ገና ስድስት ወር ሲቀረው 'ረመዳን ሆይ ናልን!' እያሉ ይዘጋጁ ነበር። እኛ ግን ይሄው ሊገባ ከአንድ ወር ከ20 ቀናት በታች ቀርቶት እንኳን፣ ስለ ረመዳን የሚያወራ አንደበት፣ የሚዘጋጅ ልቦና አጣን።
ያ አላህ! የረመዳንን ግዝፈት የምታውቅ፣ ዝግጅቷ ያማረ ህያው ልብ ስጠን።
✅ t.me/AbuSufiyan_Albenan
2 644
قال رسول الله ﷺ احفظ الله يحفظك
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:-"አላህን ጠብቀው(ትእዛዙን ፈፅም፣ክልከላውን ራቅ፣ድንበሮቹን አክብር፣በግልፅም በድብቅም ፍራው) ይጠብቅሃል።"
አላህ ለባሪያው የሚያደርገው ጥበቃ ለሁለት ይከፈላል:-
አንደኛው ለዱንያ የሚጠቅመውን ነገር ይጠብቅለታል። ጤናውን፣ቤተሰቡን ፣ ገንዘቡን እና ሌሎች ነገሮች ይጠብቅለታል።
ሁለተኛውና ዋነኛው ዲኑን ይጠብቅለታል።በዲኑ ላይ ብዥታና ጥርጣሬ እንዳያድርበት ያደርገዋል። ልቡንም በአላህ ብቻ እንዲንጠለጠል ያደርገዋል።
ሸይኽ ሷሊሕ ኣሉ_ሸይኽ
2 644
የአላህ ዉሳኔ ላንተ ጥሩ መስሎ ላይታይህ ይችላል በዛም ላይ መራራና ከባድ ልትቋቋመው የማትችል አይነት ዉሳኔ
አልሀምዱሊላህ ሁሌም አንተየፈለከው ይሆናል በፈቃዳችን አንድም አስፈፅመን አናውቅም ለማስፈፀምም አቅሙ የለንም
ችግር በገጠመህ ግዜ ምን አደርጋለው ግዴታዬ ነው ብለህ መውጫ ስላጣህ ካመረርክ ቡሃላ አትቀበል
ከመጀመሪያዉኑ ወደህና አምነህ ተቀበለው በዛም ታገስ ኢሄ አንተ የፈለክልኝ ነው በል በመታገስህም የታጋሾችን ምንዳ ለማግኘት ጣር
2 644
እናንተ ዘንጊዎች ሆይ ... እናንተ በደለኞች !
እናንተ አመፀኞች ... እናንተ ተሳሳች ፣ አጥፊዎች ... ብሎ አልጠራንም አሏህ !
እንደዛ ተብሎ ለመጠራት የተገባን ብንሆንም ... 😞
یَـٰعِبَادِیَ ٱلَّذِینَ أَسۡرَفُوا۟ عَلَىٰۤ أَنفُسِهِمۡ ...
«እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! »
ባሮቼ ... ብሎ ከነ ወንጀላችን ወደርሱ ያስጠጋን ጌታ ነው አሏህ !
ከስያሜ ፣ ከጥሪ እንኳን ልባችን ስብር ብሎ እንድንደነገጥ አላደረገም ። ይልቁንስ ወንጀሎችን ሁሉ እንደሚምር ቃል ገብቶ ከራህመቱ ተስፋ እንዳንቆርጥ አባሸረን ።
﴿إِنَّهُ هُوَ الْغَفُورُ الرَّحِيمُ﴾
« እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና ፡፡ »
...
2 644
ሪዝቅሽ ካልሆነ ሽማግሌ ተልኳ አይደለም ቀን ተቆርጦም ሊቀር ይችላል።! ስለዚህ አቀራረብሽን አደብና ገደብ አድርጊለት፣ አላህንም ምትፈልጊውን ሳይሆን ሚጠቅምሽን እንዲሰጥሽ ለምኝው።
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/enkuwoch
2 644
#በሳውዲ_አረቢያ የተከሰተው እውነተኛ ታሪክ
===========
ወንድማማቾች ወይም እህትማማቾች ፍርድ ቤት ሲሄዱ፣ የግድ ስለውርስ ወይም ስለ መሬት ክርክር ሊሆን ይችላል ብለን እናስባለን
ነገርግን አይደለም። ይህኛው በተቃራኒው ነበር።
ሂዛም አልጋምዲ የተባሉ አዛውንት የራሳቸውን ታናሽ ወንድም ፍርድ ቤት አቁመውት ነበር። ፍርድ ቤት የገተራቸው የገንዘብ ወይም ሌላ የውርስ ጉዳይ አልነበረም።እኚህ ሁለት ወንድማማቾች ደካማ እና አረጋዊ የሆኑ እናታቸውን የመንከባከብ ኃላፊነት ለመውሰድ ሁለቱ ወንድማማቾች እያንዳንዳቸው አጥብቀው ስለፈለጉ ነበር።
ሂዛም ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዳ
ሁልጊዜም እንደሚያደርገው እናቱን መንከባከብ እንደሚፈልግ፣ እሷም ህይወቱ እንደሆነች በመግለጽ በብርቱ ተማፀነ። ሆኖም ታናሽ ወንድሙ የመከራከሪያ ነጥብ አነሳ ወንድሜ ሂዛም በዕድሜ ገፍቷል ዕረፍት ያስፈልገዋል"አለ
ሁለቱም ወንድሞች እናታቸውን የመንከባከብ ክብር እንዲያገኙ ለዳኛው ሲማጸኑ…የፍርድ ቤቱ አዳራሽ በስሜት ድባብ ተናወጠ።
ዳኛው ምን መወሰን እንዳለባቸው ግራ ስለተጋቡ… እናታቸውን አስመጥተው ከሁለቱ እንድትመርጥ ጠየቋት። እናትም ስትመልስ "ሁለቱም ልጆቼ እንደ ቀኝ እና ግራ ዐይኖቼ ናቸው እና መምረጥ አልችልም" ትላለች።
እናትየው መወሰን ስላልቻለች፣ዳኛው በምክንያት ላይ ተመሥርተው መወሰን ነበረበት፣በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ወጣትነቱንና ጥንካሬውን ከግምት በማስገባት እናቱን የመንከባከብ ኃላፊነት ለታናሽ ወንድም ይሰጣል።
ውሳኔው ሲነገር፣ ሂዛም በሀዘን ድባቡ ተውጦ ማየት አሳዛኝ ነበር
እሱ ያለቀሰው ከፍርሃት ወይም ከቁጣ የተነሳ አልነበረም፤ ነገር ግን በዘመኗ የቀሩትን ቀናት እናቱን ማገልገል የሚችልበት ዕድል "ያጣ" መስሎ ስለተሰማው ነው።
ከእናቶቻችሁ በህይዎት ያልተለያችሁ ወንድም እህቶች ሆይ እድሉን ፈጥናችሁ ተጠቀሙበት… የማይገኝ ታላቅ ቢዝነስንም ሸቅሉበት።
2 644
.
⭕️ጠቃሚ ምክሮች‼️
قـالـ الإمام الحافظ ابن القيم - رحمه الله -
۞ أربعة تهدم البدن
❶ - الهم ..
❷ - والحزن !!
❸ - والجوع
❹ - والسهر
ኢብኑል ቀይም እንዲህ ይላል:-
☆ አራት ነገራቶች ሰውነትን ያደክማሉ
__ ሀሳብ ማብዛት
__ ትካዜ
__ ረሀብ
__ እንቅልፍ ማጣት
۞ وأربعة تزيد في ماء الوجه وبهجته
❶ - المروءة !!
❷ - والوفاء
❸ - والكرم
❹ - والتقوى
☆ አራት ነገራቶች የፊት ውበት ይጨምራሉ
__ አደብ(መልካም ስነ ምግባር)
__ ቃል መጠበቅ
__ የአላህ ፍራቻ
__ መልካምነት (ደግ)
۞ وأربعة تجلب البغضاء والمقت
❶ - الكبر ..
❷ - والحسد !!
❸ - والكذب .
❹ - والنميمة !!
☆ አራት ነገር ጥላቻን ያስወርሳሉ
__ ኩራት
__ ምቀኝነት
__ ውሸታምነት
__ ነገር ማዋሰድ
۞ وأربعة تجلب الرزق
❶ - قيام الليل ..
❷ - وكثرة الإستغفار بالأسحار .. !!
❸ - وتعاهد الصدقة !!
❹ - والذكر أول النهار وآخره
☆ አራት ነገር ሪዝቅን ያሰፋሉ
__ ለይል መስገድ
__ ለሊት የሚደረግ እስቲግፋር
__ ሰደቃ ማብዛት
__ ከቀኑ መጀመሪያና መጨረሻ የሚደረግ ዚክር
۞ وأربعة تمنع الرزق
❶ - نوم الصبحة ..
❷ - وقلة الصلاة !!
❸ - والكسل ..
❹ - والخيانة !!
☆ አራት ነገር ሪዝቅን ያጣብባሉ:-
__ የጧት እንቅልፍ
__ ሶላት ማሳነስ
__ ስልቹነት
__ አታላይነት
📚ዛድ አል መዓድ
❒ انظر [ زاد المعاد (٣٧٨/٤) ]
2 644
ሱብሓነላህ
በተከበረው ሓዲሰልቁድሲ ኣላህ እንዲህ ይላል
~~~{ኣንተ የሰው ልጅ ሆይ በእናትህ ሆድ ዉስጥ ኣቀመጥኩህ በእንግዴ ልጅ ኣድርጌም ሸፈንኩህ ከማህፀን እንዳትወጣ ፊትህ ወደ እናት ጀርባ ኣደርጉት እናት የምትበላው ምግብ ሽታ እንዳያስቸግርህ በስተቀኝ እና በስተግራ ትራስ ኣደረኩልህ በቀኝ በኩል የእናትህ ጉበት በግራ በኩል የእናትህ ጣፍያ በእናትህ ሆድ ዉስጥ እንዴት እንደምትቀመጥና እንደምትቆም ኣሳውቅኩህ እንዲህ የሚያደርግ ከኔ ሌላ ኣለን?
የእርግዝና ወቅቱ ኣልቆ ወደ ዱንያ ስትወጣ መላኢካ ልኬ በክንፉ ተቀብሎህ ጥርስ የምታኝክበት የለህ እጅ የለህ የምትጨብጥበት እግር የለህ የምትራመድበት በእናትህ ደርት ላይ ሁለት ጅማቶች ኣደረኩልህ የተጣራ ወተት የሚያወጡ በሙቀት ሰኣት የሚቀዘቅዝ በብርድ ሰኣት የሚሞቅ የሆነ በወላጆችህ ልብ ላይ ያንተን ሙሓባ ኣደረኩልህ ኣንተ ሳትበላ ኣይበሉ ኣንተ ሳትጠጣ ኣይጠጡ ኣንተ ሳትተኛ ኣይተኙ
ኣሁን የጠነከርክ ጊዜ የደለደልክ ጊዜ ለብቻህ ተደብቀህ በወንጀል ትጣላኝ ጀመር ከኔ ኣታፍርም? ወንጀል ከመስራት ጋራ ዱዓ ያደረግክ ጊዜ ዱዓህን እቀበልሃለሁ የጠየከኝ እሰጥሃለሁ ተውበት ያደርግክ እንደሆነም ተውበትህ እቀብልሃለሁ
ኣላህ ቁድራውን የምናውቅ ያድርገን
2 644
ያኔ እኮ እኛም እንደዚህ ነበርን!
ማን ይሆን ቀስ በቀስ ወደ ወንጀል
ያንፏቀቀን...ማን ይሆን ዉሸት...ስርቆት
ሀሜት... ክህደት... ያስተማረን
በህፃናት አለም የዉሸት እሚባል የለም
ሁሌም የእውነት ይኖራሉ።
ህፃን እያለሁ ከጓደኞቼ ጋር ስንጫወት
ቤተሰብ ሲል ስለምንሰማ አሁን እኮ
ብንሞት አሏህ ጀነት ነዉ እሚያስገባን
ማነዉ በህፃንነቱ መሞት የሚፈልገው
ስንባባል ሁላችንም እኔ እኔ እንል ነበር..
አሁን ግን ሁላችንም መሞት አንፈልግም
ምክናየቱም በወንጀል ነትበናል።
ምን አልባት የአንድ ቀን ዉሎ እና አዳራችን
የአሏህን ማህርታ ቢያሥገኝልን ብለን
ሥለምንመኝ ነው። እዉነት ጊዜዉ ሲሽከረከር
ወደ አሏህ እየተጠጋን ይሆን ወይስ...
በወንጀል ማነቆ ተጠፍረን ይሆን...
.አሏህየወደዚች ምድር ለጋ ስጋ እና አጥንት ከንፁህ ልብ ጋር ሰተኸን ነበር በሀራም ስጋችንንም አጥንታችንንም አጠነከርነዉ ያች ብርሀን ልባችን ወንጀል አደበዘዛት ሩሀችን ወደ አንተ መምጫዋን አንተ ነህ እምታዉቀዉ...ወደ አንተ ስትመጣ ከቅጣትህ እዝነትህን አስቀድምላት አንተ አሏህዬ አንተ..ከእናት በላይ አዛኝ እኮ ነህ!!።
2 644
አንድን አካል ስንወደውም ሆነ ስንጠላው ሚዛናችን ሊሆን የሚገባው የአኺራ ጉዳይ(የዲኑን ሁኔታ መሰረት አድርገን) እንጂ የዱንያን ጥቅም መሰረት አድርገን መሆን የለበትም።
2 644
ላ ተቅነጡ፣
ላ ተሕዘኑ፣
ላ ተይአሱ፣
ላ ተሂኑ፣
ላ ተኻፉ፣
አብሽሩ...... ይላል።
ይህን የሚለን የፈጠረን አምላካችን ነው። በተለያዩ የቀርኣን አንቀጾች ውስጥ ያገኟቸዋል።
ሱብሓነከ ረቢ።
ሰዎች "አይዟችሁ፣ አብሽሩ.. " ሲሉን ምን ያህል እንፅናናለን፣ እንበረታለን??? አላህ እንዲህ ሲለንስ...
~ ተስፋ አትቁረጡ
~ አትዘኑ
~ አትድከሙ
~ አትስነፉ
~ አትፍሩ
~ አይዟችሁ፣ በመልካም ተበሰሩ
.
.
እናም አምላካችሁ ቸር እና አዛኝ ነውና አብሽሩ ለማለት ነው።
ሶባሐል ኸይር
2 644
አብሽሩ የአላህ ባሮች ሆይ
በስራ ማጣት ምክንያት የቤተሰብ ሀሳብ የልጅ ቀለብ ሀሳብ ወ ወ ወ ያሳሰባችሁ የአዛኙ ባሮች ሆይ
በህመም ምክንያት ሌቱን ሰዎች ስክንን ያለ እንቅልፍ ሲይዛቸው ጅስማቸውን ሲያሳርፉ እናንተ በህመም ምክንያት እየተሰቃያችሁ እምታድሩ የ ሙጅቡ ባሮች ሆይ
በተለያዩ ሃሳቦች እንቅልፍ ካይናችሁ ብንን ብሎ ጠፍቶ በሀሳብ ጭልልጥ ብላችሁ ጣራው ላይ አይናችሁን ተክላችሁ እምታድሩ የ የሶመዱ ባሮች ሆይ
በሰዋች በደል የተነሳ ከአይናችሁ እምባ አስጎራፊዎች የ በሲሩ ባሮች ሆይ
ቤተሰብ ታሞባችሁ ማሳከሚያ አጥታችሁ ወይ በጉልበት አትረዱ ወይ በገንዘብ አትረዱ እምትገቡበት ቀዳዳ ያጣችሁት የ ገንዩ ባሮች ሆይ
አብሽሩ የአላህ እርዳታ ቅርብ ነው
አብሽሩ የተጨነቃችሁበት ነገር ሁሉ መገፈፊያው እየደረሰ ነው ብዙውን አልፋችሁታል ስቃዩ መከራው ህመሙ ችግሩ ተገፎ
እፎይታ ሰላም ደስታ ሊተካ ቀርቧል አብሽሩ ፈረጁ እየቀረበ ነው
ام حسبتم ان تدخلوا الجنة ولما ياتكم مثل الذين حلوا من قبلكم مستهم الباساء والضراء وزلزلوا حتى يقول الرسول والذين امنوا معه متى نصر الله ٌ الا ان نصر الله قريب
አዎ ውድ የአላህ ባሮች ሆይ የአላህ እርዳታ ቅርብ ነው አብሽሩ
በትእግስት እና አላህን በመማፀን ጠብቁት የአላህ እርዳታ ቅርብ ነው ሁሉም ይገፈፋል እመኑኝ እዚህ እስከምንደርስ ድረስ ብዙ አሳልፈን የለ?! ይሄም ያልፋል ወሏሂ ያልፋል!!
ጀነት ያስገባናል ብለን እምንተማመንበት አሏህ የዱንያን ችግር ላይገፍልን ተጠራጠርን እንደ????
https://t.me/+Dst-TmCESgFkODc8
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
