5 586
Suscriptores
+424 horas
+187 días
+1230 días
Archivo de publicaciones
5 586
ቀን 26/09/2018
ለሁሉም የትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ።
ከነገ ሐሙስ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ መማር ማስተማር የሚቀጥል መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን።
ቀሪ የትምህርት ቀናት አጭር በመሆኑ ተከታታይ ምዘና በተገቢው መልኩ ይደራጃል ፣ ስም ቁጥጥር ይካሄዳል ፣ የባከኑ ክፍለ ጊዜያት እና የትምህርት ይዘት ሽፋን ይደረጋል።
በመሆኑም ማንኛውም ተማሪ ከትምህርት ገበታው ቀርቶ ለሚወሰደው እርምጃ ኋላፊነቱን ወላጅና ተማሪ እንደሚወስድ ከወዲሁ እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
5 586
ከላይ በተገለጸው መሠረት በተለይ ከዳግማዊ ብርሃን ት/ቤት ተመድባችሁ የመጣችሁ ተማሪዎች ኦንላይን ስኩል ሊስት ላይ ስማችሁ ስለሌለ የ1ኛ ሴሚስተር ውጤት አልገባላችሁም። ስለዚህ በጠዋት ተገኝታችሁ ዳግም ምዝገባ ካላከናወናችሁ ውጤት ላይ ለሚፈጠረው ችግር ት/ቤቱ ሃላፊነት አይወስድም።
ማሳሰቢያ :- ስትመጡ የት/ቤት መታወቂያ እና ዩኒፎርም መልበስ እንዳይረሳ።
5 586
ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች የምትዘጋጁ ውድ ተማሪዎች፤ እንኳን ለዚህ ወሳኝ ምዕራፍ አደረሳችሁ። ይህ ወቅት እስካሁን በትምህርት ገበታችሁ ያሳለፋችሁትን የልፋት፣ የጥረት እና የዕቅድ ውጤት የምታሳዩበት ታላቅ አጋጣሚ ነው።
የፈተና ወቅት የውጤታማነታችሁ ማረጋገጫ እንጂ የጭንቀት ምንጭ አይደለም!
ፈተና መድረሱ መረበሽንና ፍርሃትን ሊፈጥር ይችላል፤ ነገር ግን እውነተኛው ስኬት የሚመጣው ፈተናን ከመፍራት ሳይሆን በራስ መተማመንና ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ነው። ወደ ፈተና ክፍል ስትገቡም ሆነ ከመፈተናችሁ በፊት ልታደርጓቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፡
1. ከፈተናው በፊት፡ የስነ-ልቦና እና የዝግጅት ወቅት
እስካሁን ድረስ ያጠናችሁትን እቅድ አውጥታችሁ ከልሱ (Smart Revision):
አዳዲስ መፃህፍትን ለማጥናትና ለመዳሰስ በመሞከር ከመጨናነቅ ይልቅ እስካሁን የተማራችኋቸውን ዋና ዋና ነጥቦች፣ ማጠቃለያዎችና ያለፉ የፈተና ጥያቄዎችን (Past exam Papers) ደጋግማችሁ ከልሱ።
#አእምሯችሁን_በነፃነት_አዘጋጁ:
"አልችልም" ወይም "ብወድቅስ" የሚሉ አሉታዊ ሀሳቦችን አስወግዱ። ባለፉት አመታት ያሳለፋችኋቸውን ስኬቶች በማሰብ "እችላለሁ፣ አልፋለሁ!" የሚል ጠንካራ ስነ-ልቦና ይኑራችሁ።
#የእንቅልፍና_የጤና_ጉዳይ: በቂ እንቅልፍ አለማግኘት ትኩረትን ይበትናል። በመሆኑም ከፈተና በፊት ባሉት ቀናት ቢያንስ ከ7-8 ሰዓት መተኛት እና ቀላልና ገንቢ ምግቦችን መመገብ ለፈጣንና ንቁ አእምሮ እጅግ አስፈላጊ ነው።
#የቁሳቁስ_ዝግጅት: የተፈታችነት ማረጋገጫ መታወቂያ (Admission ID card)፣ ብዕር፣ እርሳስ፣ ላጲስ እና ሌሎች የሚያስፈልጓችሁን ነገሮች ከፈተናው ዋዜማ ምሽት ጀምሮ አዘጋጅታችሁ አስቀምጡ።
2. በፈተናው ቀን፡ በእርጋታ መጀመር
#በማለዳ_መነሳትና_መድረስ: በፈተናው ቀን በጠዋት በመነሳት፣ አእምሯችሁን አረጋግታችሁ ወደ ፈተና ጣቢያው ቀድማችሁ ተገኙ። መጣደፍ አላስፈላጊ ጭንቀትን ይፈጥራል።
#ትኩረትን_መሰብሰብ (Focus): ወደ ፈተና ክፍል ከመግባታችሁ በፊትም ሆነ ከገባችሁ በኋላ ከጓደኞቻችሁ ጋር የሚያስጨንቁ ወይም ግራ የሚያጋቡ የትምህርት አርዕስቶችን አታንሱ። በምትኩ በጥልቀት ትንፋሽ በመውሰድ ራሳችሁን አረጋጉ።
#ፀሎት_አድርጉ: እንደየእምነታችሁ አእምሯችሁን እንዲያበራላችሁ፣ ትውስታችሁን እንዲያድስላችሁና ሰላም እንዲሰጣችሁ ፈጣሪያችሁን በጸሎት ጠይቁ።
3. በፈተናው ወቅት፡ ብልሃተኛ መሆን
"ፈተናን መስራት እውቀትን ብቻ ሳይሆን ጊዜን የመጠቀም ጥበብንም ይጠይቃል።"
#መመሪያዎችን_በጥንቃቄ_ማንበብ:
የፈተናውን ወረቀት እንደተቀበላችሁ መመሪያዎቹን (Instructions) ሳታነቡ መጀመር ትልቅ ስህተት ነው። ምን ያህል ጥያቄዎች እንዳሉ እና የተሰጠውን ጊዜ በሚገባ አስተውሉ።
#ጊዜን_በአግባቡ_መከፋፈል: ለአንድ ጥያቄ ብዙ ጊዜ አታጥፉ። ቀላል የሆኑትንና የምታውቋቸውን ጥያቄዎች በፍጥነት በመስራት በራስ መተማመናችሁን ጨምሩ። አስቸጋሪ የሆኑትን ጥያቄዎች ምልክት አድርጋችሁባቸው እለፉና በኋላ ተመለሱባቸው።
#መልስ_ማጥቆር (Answer Sheet): በተለይ በመለስ መስጫ ወረቀት ላይ ስታጠቁሩ የጥያቄው ቁጥርና የማጥቆሪያው ቁጥር መገጣጠሙን ደጋግማችሁ አረጋግጡ። አንዱን ጥያቄ ዘላችሁ ከሆነ መልሱ ሌላ ቦታ እንዳይጠቆር ጥንቃቄ አድርጉ።
#ደግሞ_መፈተሽ (Review): ፈተናውን ሰርታችሁ ከጨረሳችሁ በኋላ ጊዜ ካላችሁ መልሶቻችሁን አንድ በአንድ በጥንቃቄ ከልሱ። የዘለላችሁት ጥያቄ አለመኖሩን አረጋግጡ።
#የማጠቃለያ_መልዕክት
ውድ ተማሪዎች፤ ይህ ፈተና እናንተን ለመጣል ሳይሆን ወደ ቀጣዩ የታሪካችሁ ምዕራፍ እንድትሻገሩ የተዘጋጀ ድልድይ ነው። 6ኛ ክፍሎች ወደ መካከለኛ ደረጃ፣ 8ኛ ክፍሎች ወደ ሁለተኛ ደረጃ፣ እንዲሁም 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ወደ ህይወት ምዕራፍ የምታደርጉትን ጉዞ የሚያፋጥንላችሁ የቁርጠኝነታችሁ መለኪያ ነው።
ወላጆቻችሁ፣ መምህራኖቻችሁና መላው የት/ት ማህበረሰብ እናንተን ለመደገፍና በእናንተ ለመኩራት ዝግጁ ናቸው። በራሳችሁ እውቀት፣ ጥረትና ብቃት ተማመኑ። ከአላስፈላጊ ኩረጃና የፈተና ስርቆት ራሳችሁን ጠብቁ፤ ምክንያቱም በራስ ልፋት የሚገኝ አነስተኛ ውጤት በስርቆት ከሚገኝ የውሸት ውጤት በላይ ዘላቂ ክብርና እውነተኛ እውቀትን ይሰጣል።
እናንተ የኢትዮጵያ ተስፋዎች ናችሁ! መልካም የፈተና ወቅት ይሁንላችሁ፣ ስኬት ከእናንተ ጋር ይሁን!
✍
5 586
+8
በየካቲት 23 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የዓለም አቀፍ ትንባሆ የማይጨስበት ቀን ተከበረ
ዛሬ ሰኞ 10/9/2018 ዓ.ም በየካቲት 23 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በጠዋት የሰልፍ ሥነ-ሥርዓት ላይ እና በእረፍት ሰዓት ግንቦት 23 የሚከበረውን ዓለም አቀፍ ትንባሆ የማይጨስበት ቀን በተለየ ሁኔታ ለማክበር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር ተካሂዷል። መርሃ ግብሩ “ለኒኮቲንና ለትምባሆ ሱሰኝነት አጋላጭ የሆኑ ስልቶችን እናጋልጥ!!” /“Unmasking the Appeal - Countering Nicotine and Tobacco Addiction”/ በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን፣ አዲስ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሐኒት ባለስልጣን አዲስ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጣቢያ የተገኙ ባለሙያዎች እና በት/ቤቱ ጤና ክበብ ስር በሚገኘው የፀረ-አደንዛዥ እፅ ክበብ ተጠሪ መምህር መስፍን መሠለ ቀኑን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በማዘጋጀት ለመምህራን፣ ሰራተኞችና ተማሪዎች በትምባሆ ጎጂነት ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ ሰጥተዋል። በተለይም የትምባሆና የኒኮቲን ሱሰኝነት በጤና፣ በማህበራዊ ሕይወትና በትምህርት ላይ የሚያስከትለው ጉዳት ተብራርቶ የቀረበ ሲሆን፣ ተማሪዎች ከእነዚህ ጎጂ ልማዶች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ምክረ ሀሳቦች ተሰጥተዋል። ት/ቤቱም ጤናማ እና ከሱስ ነፃ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።
5 586
6 - 9 - 18
ማሰሰቢያ
ለ12 ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆቻቸው
የተፈታኝ አድሚሽን ካርድ የሚሰጠው በአግባቡ ትምህርቱን ለተከታተለ ተማሪ ብቻ መሆኑን እያሣወቅን ከት/ቤት የሚቀሩ (ቀሪ ) ያለባችሁ ተማሪዎችና ወላጆች ከነገ ጀምሮ የቀራችሁበትን ምክንያት ለር/መ/ራን ሪፖርት እድታደርጉ እናሳስባለን ::
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
