es
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ir al canal en Telegram
1 741
Suscriptores
+224 horas
+37 días
-730 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  በአስተዳደሩ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር አዘጋጅነት የሚካሄደውን የ2015 ዓ.ም የክህሎት ውድድር በክላስተር ደረጃ ማካሄድ ጀመረ።      በዛሬው ዕለት በኮሌጃችን በዉድ ወርክ እና በአይ.ሲ.ቲ ዘርፎች ላይ አሰልጣኝ መምህራንና ሰልጣኝ ተማሪዎች  ለውድድሩ በተመረጡ ዳኞች ፊት ውድድራቸውን እያካሄዱ ይገኛሉ።      የክህሎት ውድድሩ በቀጣይ ቀናትም በሌሎች ሙያዎች ላይ መካሄዱን የሚቀጥል ሲሆን ውድድሩን በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች ኮሌጆቹን እንዲሁም አስተዳደሩን በመወከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር ላይ የሚሳተፉ ይሆናል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 22/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት እና የድሬዳዋ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት በጋራ በመሆን የ2015 ዓ.ም የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ውድድርን አስመልክቶ ለኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎች እና አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የኦረንቴሽን መድረክ ተዘጋጀ፤ እንደሚታወቀው የበለጸጉ አገራት የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ውድድርን ቁልፍ የመነሻ መሳሪያ አድርገው ቴክኖሎጂዎችን በአግባቡ በመቅዳትና በማሻሻል  በሂደት አስደናቂ ቴክኖሎጂዎችን ያፈለቁት ለፈጠራ ስራዎች ትኩረት በመስጠት ስራውን ለሰሩት አስፈላጊውን ማበረታቻና እውቅና በመስጠታቸው ነው፡፡ በመሆኑም የተቀዱ ቴክኖሎጂዎችን ለምርትና አገልግሎት የሚውሉበት ስርዓት አለመዘርጋት ክፍተቶች በዋነኛነት የተለዩ ሲሆን አሰራሩን ለማሻሻል ቅንጅቶችን በማጠናከር ልዩ ክህሎት ያላቸውና የፈጠራ ባለሙያዎችን በማበረታታት ቴክኖሎጂ የመቅዳት አቅማችንን በክህሎት ውድድር ማሳደግና ማበረታታት ወሳኝ ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም በአገር አቀፍ ደረጃ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር ለሚካሄደው በሰልጣኞችና በአሰልጣኞች እንዲሁም በኢንተርፕራይዞች ዘንድ ተመሳሳይ የተነሳሽነት መንፈስ በመፍጠር በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚከናወነው የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ውድድር የከተማ አስተዳደሩን የሚወክሉ የኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎች እና አሰልጣኝ መምህራንን እንዲሁም ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን ለመለየትና ለማበረታታት ከፊታችን መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄድ መሆኑን በቢሮው የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ቡድን መሪ ወ/ሮ አለምጸሃይ ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 19/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የ2015 ዓ.ም የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ውድድርን አስመልክቶ
+7
የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የ2015 ዓ.ም የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ውድድርን አስመልክቶ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የተለያዩ እንደስትሪዎችና ተቋማት ለተወጣጡ ውድድሩን በዳኝነት ለሚመሩ ዳኞች የኦረንቴሽን መድረክ አዘጋጀ፡፡ በዚህም ግልጽ የዳኝነት አሰራር ማስረጽና ቅሬታዎችን መቀነስ ብሎም እንዳይኖሩ መስራት የውድድሩ ዋንኛ ተግባርና ኃላፊነት በመሆኑ የዳኞች መመልመያ ተግባርና ኃላፊነት መመሪያ ለክህሎት ውድድሩ በማዘጋጀት በውድድሩ ሂደት ቅሬታዎች እንዳይፈጠሩ በመስራት ለተወዳዳሪዎች የዳኝነት አሰጣጥ ላይ የሚከናወኑ ሂደቶችን በማሳወቅና ግንዛቤ በመፍጠር በጥብቅ ዲሲፒሊን የሚመራ የዳኝነት ክትትልና ግምገማ ስርዓት በመዘርጋት መረጃዎችን በተደራጀ ሁኔታ ለውሳኔ አሰጣጥ በሚያመች ሁኔታ ከማወዳደሪያ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በየደረጃው ለሚገኙ አካላት ውጤቱን በማደራጀት ማስረከብ እንዲሁም በዳኝነት ስራቸው ላይ ለሚነሱ ቅሬታዎች ከአስፈላጊው መረጃ ጋር እንደአስፈላጊነቱ ለቅሬታ ኮሚቴ ምላሽ መስጠት በሚያስችላቸው አግባብነት ላይ ተገቢ የሆነ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ተደርጓል፡፡ በመሆኑም ውድድሩ ከፊታችን መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ጀምሮ የኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎች እና አሰልጣኝ መምህራንን እንዲሁም ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን በማሳተፍ የሚካሄድ ሲሆን በተለይም መሰል ውድድሮችን ማካሄድ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት በመሆኑ በውድድር ከማሸነፍ በላይ የክህሎት እና እውቀት ሽግግሩ ወሳኝ መሆኑን በኤጀንሲው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል። የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 19/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2015 ዓ.ም ስልጠና ዘመን ለአዲስ የምሽት ሰልጣኝ ተማሪዎች ስለ ቴ/ሙ/ት/ስ ፖሊሲና ስትራቴጂ እንዲሁም ስለ ኮሌጁ ውስጣዊ አሰራር ህግና ደንብ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2015 ዓ.ም አዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች በየመረጧቸው ዲፖርትመንቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በዚህም ከዲፓርትመንት ተጠሪዎችና አሰልጣኝ መምህራኖች ጋር የትውውቅ ፕሮግራም አድርገዋል።    ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በየዲፓርትመንታቸው የሚገኙትን ወርክ ሾፖችና መማሪያ ክፍሎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በአሰልጣኝ መምህራኖቻቸው ስለሚማሩበት ዲፓርትመንት ሰፋ ያለ ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል።    በተጨማሪም የዘንድሮ አዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ መደበኛው ትምህርትና ስልጠና ከመግባታቸው አስቀድሞ በኮሌጁ የተሰጣቸውን የ life Skill ስልጠና አጠናቀው መጋቢት 11 2015 ዓ.ም መደበኛ ትምህርትና ስልጠናቸውን በይፋ ጀምረዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 13/2015 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ #የኢንዱስትሪ_ቴክኒካል_አማካሪ_ቦርድ ለአዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች በሙያ ስልጠና እና የስራ አለም እንዲሁም በኢንዱስትሪው ተቀባይነት ዙሪያ ኦረንቴሽን ሰጥቷል። በተጨማሪም አሁን በስራ ላይ የሚገኙ የኮሌጁ ሴት ሰልጣኝ ተማሪዎች ለአዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች ያላቸውን ተሞክሮ አካፍለዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 8/2015 ዓ.ም