es
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ir al canal en Telegram
1 740
Suscriptores
Sin datos24 horas
+17 días
-630 días
Archivo de publicaciones
Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈፃፀምና የቀጣይ ስድስት ወር እቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ:: በዛሬው እለት በተካሄደው መድረክ የEASE ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ እስከ እሁን የነበረውን የአፈፃፅም ትግበራ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድን መነሻ በማድረግ ከፕሮጀክቱ ኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት ጋር የውይይት መድረክ በሀረር ተካሂዷል:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው እንደገልፁት ምንም እንኳን የEASE ፕሮጀክትን ወደ ትግበራ ከገባ አጭር ጊዜ ቢሆንም እስካሁን በደረስንበት አፈፃፀም መሰረት ወቅቱን ጠብቆ ከባለድርሻ አካላት ጋር መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ይህን መድረክ ተዘጋጅቷል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም በመድረኩ በሚቀርበው የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወር እቅድ ላይ ከኢንዱስትሪው አኳያ ማካተት ሚገባንና የተዘነጉ ጉዳዮች ካሉ ከመድረኩ በሚገኘው ግብዓት መሰረት እቅዱን ለማሻሻል ተቋማችን ዝግጁ እንደሆነም ገልፀዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህ ፕሮጀክት ሲነደፍ እንደ ሀገር ማስመዝገብ የተፈለገው ውጤት እንዳለ ጠቅሰው በዚህም መሰረት Result Framework በሚኒስቴር መ/ቤቱ ፀድቆ ሲመጣ በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት የኛ መመዘኛ እሱ ይሆናልም ብለዋል:: በፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ወ/ሮ ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው አፈፃፀምም የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ ከማቋቋም ጀምሮ የፕሮጀክቱ አመራሮችንና ባለሙያዎችን በልምድ ልውውጥና ስልጠናዎች የማብቃት እንዲሁም 65 ለሚሆኑ የተቋሙ አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል:: በተጨማሪም በቀረበው ሪፖርት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አመራሮችና ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት መቀየር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መካሄዱም በሪፖርቱ ከቀረቡት ነጥቦች ይገኙበታል:: በመቀጠልም የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በዚህም በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለመፈፀም በእቅዱ ላይ የተመላከት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በተቋሙ የሪኢኖቬሽን ስራዎች ፣ የአሰልጥኞች ስልጠና፣ የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች እንዲሁ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠዎችን ተግባራዊ ለማድረግ መያዙ ከብዙ ጥቂቱ መሆኑን በቀረበው እቅድ ተመላክቷል:: የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የፕሮጀክቱ አፈፃፀምና የቀጣይ እቅድን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት የሚረዱ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት የተካሄበት ሲሆን ኮሌጁን ጨምሮ የኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላትም ለቀጣይ የየድርሻቸውን አሳይመንቶችን በመውሰድ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 25/2017 ዓ.ም ሀረር

በዲጂታል ላይብረሪ አገልግሎት ዙሪያ ለኮሌጁ የቤተ-መፃህፍት ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ተጀመረ። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዲጂታል ላይብረሪ አገልግሎት ዙሪያ በኮሌጁ ለሚገኙ የቤተ-መፃህፍት ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል። ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊና የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ እንደተናገሩት የዲጂታል ላይብረሪ አገልግሎት ሰልጣኝ ተማሪዎች እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰብ ንባብን እንዲያዘወትሩ በማድረጉ ረገድ ለሚደረገውን ጥረት ያግዛል ያሉ ሲሆን አክለውም ስልጠናው የመፅሀፍት ውሰትንና ንባብን በማዘመን የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳ ጠቁመው ሙያዊ ስልጠናው የቤተ መፃህፍት ባለሙያዎችን እውቀትና ክህሎት በማጎልበት ረገድ የጎላ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል። በአውቶማይዜሽንና ዲጂታላይዜሽን ዘርፍ እየተሰጠ ያለው ይህ ስልጠና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን አላማውም የቤተ-መፃህፍት አገልግሎትን በማዘመን ተደራሽነቱን ለማስፋትና አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ መሆኑም ተገልፇል:: ስልጠናው ለቀጣይ ቀናት እየተሰጠ የሚቆይ ሲሆን በንድፈ ሃሳብና በኮምፒውተር የታገዘ የተግባር ስልጠናንም ያካተተ መሆኑ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 20/2017 ዓ.ም

እንኳን አደረሳችሁ!! ለኮሌጃችን ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የ
+1
እንኳን አደረሳችሁ!! ለኮሌጃችን ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የአብሮነት እንዲሆንልን እመኛለሁ:: #መልካም_የጥምቀት_በዓል!! አቶ ታደለ አሰፋ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን

ከጋንቤላ አፔኖ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ከደቡብ ምዕራብ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተወጣጣ ልኡካን ቡድን ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልምድ ልውውጥ አደረ፡፡ ኮሌጆቹ በነበራቸው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የላቀ አፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችም በኮሌጁ ዲኖች አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረጉት ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃን መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያደረገው ያለው እንቅስቃሴ አስደናቂ መሆኑን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ምሳሌ መሆን የሚችልበት የአፈፃፀም ደረጃ ላይ እንደሚገኝም በውይይታቸው ወቅት አንስተዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኙትን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡባቸው ኮሌጆች ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 9/2017 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢንቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ኢንቲትዩቱ ጋር
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢንቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ኢንቲትዩቱ ጋር በመተባበር እየሰራቸው ከሚገኙ ተግባራቶች በተጨማሪ ዘላቂነት ባለው መልኩ ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን እንዲረዳ ሁለቱ ተቋማት የመግባቢያ ስምምነቱን ተፈራርመዋል:: የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የኮሌጁ ዲን እቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የስራ አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ለገሰ ሲሆኑ ስምምነቱም በአቅም ግንባታ ስልጠናዎች፣በጥናቶች እንዲሁም በማማከር ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያለመ ሲሆን በቀጣይ በመግባቢያ ስምምነቱ መሰረት ወደ ትግበራ እንደሚገባም ትግልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 9/2017 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ በሚገኘው የብስራተ ገብርኤል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::  የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር ተቀራርቦ በጋራ ለመስራት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው አለትም በብስራተ ገብርኤል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ግንዛቤን የመፍጠር ስራ ሰርቷል:: የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለት/ቤቱ ተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት ሀላፊና የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በመድረኩም ተማሪዎቹ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላቸውን የተዛባ አመለካከት የሚቀርፍና የቴክኒክና ሙያ ነባራዊ ሁኔታን በግልፅ በሚያሳይ መልኩ በመተንተን ዘርፉ ለተማሪዎቹ የሚያስገኘውን ምቹ አጋጣሚ ሰፋ ባለ ማብራሪያ ገለፃ ያደረጉላቸው ሲሆን ተማሪዎች የነገ መዳረሻችውን ከዚሁ ትኩረት ሰተው በጥንቃቄ መምረጥ እንደሚገባቸውም ምክር ለግሰዋል:: እንዲሁም በአዲሱ ፖሊሲ መሰረት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎችንም አያይዘው የሚሰለጥኑ በመሆኑ በዘርፉ የሚሰጡትን የስልጠና አይነቶች ቀድመው በግልፅ እንዲረዷቸው በማድረግ ካላቸው ዝንባሌ ጋር የሚጣጣም የስልጠና አይነትን ምርጫቸው እንዲያደርጉ የሚረዳቸውን ግንዛቤ ማግኘትም ችለዋል:: በተጨማሪም ከት/ቤቱ ጋር የጋራ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም እንዲሁም በት/ቤቱ የቴክኒክና ሙያ ክበብ በማቋቋም ተማሪዎቹ ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ እንደሚሰራ የተገለፀ ሲሆን በተጨማሪም የቴክኖሎጂ ፈጢራ ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች በመለየት ከኮሌጁ የሚያስፈልገውን ድጋፍ እንዲያገኙ የሚደረግ መሆኑም ተገልፇል:: የግንዛቤ ማስጨበጫው በት/ቤቱ ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም ለ92 ሴት እና ለ80 ወንድ በድምሩ 172 ለሚሆኑ የት/ቤቱ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ግንዛቤ የተፈጠረበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም

በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ:: በዛሬው ዕለት በአስተዳደሩ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ ለሰልጣኞች የሰርተፍኬት መስጠትና የተመደቡበትን ኢንደስትሪ ዕጣ የማውጣት ፕሮግራም ተካሄደ። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት ቢሮው በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑና በዚህም የመጀመሪያ ዙር ለአርባ አምስት ቀናት በተሰጠ ስልጠና ሰላሳ አንድ ሰልጣኞችን ማሰልጠን መቻሉን ተናግረዋል:: የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴ/ሙ/ት/ስ ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ይህ የተሰጠው ስልጠና ኮሌጆች ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰው ሃይል በማፍራቱ ረገድ በቅንጅት እየተሰሩ ከሚገኙ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑን አንስተው ሰልጣኞች በስልጠናው የቀሰሙትን በስራው አለም በተግባር ውጤት እንዲያመጡ አሳስበዋል። የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም በበኩላቸው በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ ተመርቀው ስራ ለሚፈልጉ ወጣቶች የስራ ዕድል ከመፈጠሩ ጎን ለጎን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ጋር በተያያዘ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን ክፍተት የመሙላቱ ተግባር በተመሳሳይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በቅንጅት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት አዲሱን እሳቤ እና የጥራት ስራ አመራር ስርዓት መሠረት አድርጎ በተከለሰው እቅድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ:: በመድረኩ አዲስ በተከለሰው እቅድ ዙሪያ ተሻሽለው የመጡና አዲስ በተጨመሩ የአዲሱ እሳቤዎች እና የጥራት ስራ አመራር ስርዓት መነሻ በሆነው እቅድ ላይ ለትምህርትና ስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል:: የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በዘርፉ አዲሱ እሳቤዎች ዓላማ ከሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ልማት አኳያ ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት የታለመውን ጥራቱን የጠበቅና የተሟላ ስልጠና መስጠት እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑም ተገልፇል:: በመድረኩ በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሳታፊዎች በቀረበው የተከለሰ እቅድ ዙሪያ ያላቸውን አስተያየትና ምክረ-ሃሳብ በማቅረብ ሰፊ ውይይትም ተደርጎበታል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥር 5/2017 ዓ.ም

እንኳን ለ2017 ዓ.ም የገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ:: በቅድሚያ ለኮሌጃችን ሰራተኞች እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል(ገና) በሰላም አ
እንኳን ለ2017 ዓ.ም የገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ:: በቅድሚያ ለኮሌጃችን ሰራተኞች እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል(ገና) በሰላም አደረሳችሁ እያልኩኝ በዓሉ የሰላም፣የፍቅር፣የጤና፣የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ በዓሉን ስናከብርም የተቸገሩ ሰዎችን በመርዳትና ያለንን በማካፈል በዓሉን በበጎ ተግባር ማሳለፍ ይኖርብናል እያልኩ በድጋሚ በኮሌጁ ስም እንኳን አደረሳችሁ ማለት እወዳለሁ:: #መልካም_የገና _በዓል!! ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ