Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Ir al canal en Telegram
Mostrar más
1 739
Suscriptores
Sin datos24 horas
+27 días
-330 días
Archivo de publicaciones
የካይዘን ፍልስፍና ስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ባሻገር ምርትና ምርታማነትን በማሻሻሉ ረገድ ፋይዳው የላቀ በመሆኑ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ የካይዘን ማሻሻያ ትግበራ ንቅናቄ ማስጀመሪያ የሆነ የግንዛቤ መስጫ መድረክ ለኮሌጁ አጠቃላይ ሰራተኞች አካሄደ::
የካይዘን ፅንሰ-ሀሳብን ተረድቶ በትኩረት መተግበር ከተቻለ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን መፍቻ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የካይዘን ትግበራ ምቹና ፅዱ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር ባሻገር የሀብት ብክነትን ከማስወገዱም በተጨማሪ አሰራርን በማዘመን ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑንም ገልፀዋል::
ም/ል ዲኑ አክለውም በቀጣይ ቀናት በተቋሙ በሚተገበረው የካይዘን ማሻሻያ ትግበራ ወቅት ከትግበራው የሚጠበቀውን ውጤት ለማግኘት ሁሉም የኮሌጁ አመራርና ሰራተኞች ተገቢውን ትኩረትና ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል::
በመድረኩ የካይዘን ትግበራ ማሻሻያ ንቅናቄውን አስመልክቶ ለኮሌጁ ሰራተኞች የተዘጋጀውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና
ከአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመት ቢሮ በመጡ ባለሙያ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን በዚህም በተቋም ደረጃ የካይዘን ትግበራ የሚፈጥራቸው ለውጦችና ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን የዳሰሰ የግንዛቤ ስልጠና መስጠት ተችሏል::
በተጨማሪም በኮሌጁ በቀጣይ ቀናት የሚተገበረውን የካይዘን ማሻሻያ ትግበራ መነሻነት የተዘጋጀውን የካይዘን ማስተግበሪያ እና የአፈፃፀም መከታተያ መመሪያ ሠነድ በኮሌጁ የካይዘን ልማት ቡድን መሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት ለሰራተኛው የቀረበ ሲሆን በዚህም የትግበራውን አካሄድ እና የትግበራ ሂደቱ የሚያካትታቸውን ዝርዝር ጉዳዮች አስመልክቶ በሰፊው ገለፃ ማድረግም ተችሏል::
"ዛሬን እናሻሽል፣ ብክነትን እናስወግድ ፣ ቅልጥፍናን እንጨምር፣ ነገን እንገንባ!"
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
የካቲት 19/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለሶስተኛ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የምርቃት እና የማጠቃለያ መድረክ ተካሄደ
" ብቃት ፣ ክህሎት ፣ ስኬት " በሚል መሪ ሀሳብ ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ማጠቃለያ መርሀ ግብር በዛሬው እለት ተካሂዷል።
በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ፕሮጀክቱ በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን መቀጠል ያልቻሉ ወጣቶችን ለ 12 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት በአስተዳደሩ ባሉ ድርጅቶች ላይ ለስድስት ወራት የስራ ላይ ልምምድ አድርገው በቋሚነት ተቀጣሪ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል ።
አቶ ሮቤል አክለውም ወጣቶች በተለያዩ ፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው ስራቸውን በትጋት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀው የስራ ባህላቸውን የቀየረ ኢንዱስትሪዎችም በዳበረ ተወዳዳሪ የሰው ኃይል እንዲመሩ ማድረግ ያስቻለ ፕሮጀክት መሆኑን ነው አቶ ሮቤል በእለቱ ያስታወቁት ።
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ እንዳሉት በብቃት ፕሮጀክት ፕሮግራም እንደ ሀገር 60 ሺህ 399 ወጣቶች ተመዝግበው ከ 54ሺ በላይ እንዳጠናቀቁና ለ 52 ሺህ ወጣቶች ደግሞ ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ገልፀው በድሬዳዋ አስተዳደርም በሶስት ዓመታት 2 ሺህ 846 ወጣቶች ታቅፈው ከ 2 ሺህ 700 በላይ የሚሆኑት እንደተመረቁና ከነዚም መካከል 60 በመቶ ወጣት ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል ።
©️ DGC የካቲት 7/2018
የቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡
የቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት ከሚተገበርባቸው 24 የሚሆኑ የሀገሪቱ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አንደኛው ሲሆን በዚህም የኮሌጁን ዲኖች ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ያለውን የስራ እንቅስቃሴ ለመመልከት እንዲሁም በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ያለውን ተሞክሮ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን የስራ ልምድ ልውውጥ በኮልጁ ማካሄድ ችለዋል::
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብር ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ የEASE ፕሮጀክት ትግበራን ጨምሮ ጠቅላላ በተቋም የተመዘገቡ የአፈፃፀም ውጤቶችን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከምስረታው አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል::
ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው አቀባበልና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻ በማድረግ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ካሳየው የስራ አፈፃፀም ብዙ ልምዶችን መቅሰም መቻላቸውንም ገልፀዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው የልምምድ ልውውጥ መርሃ-ግብርም የተሳካ ቆይታን በኮሌጃችን ማድረግ ችለዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥር 21/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሀዘን መግለጫ
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሆቴልና ቱሪዝም ዲፖርትመንት ሰልጣኝ ተማሪ የነበረችው ወጣት ኤደን ሰለሞን ባደረባት ህመም ጥር 17/2018 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይታናለች።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በሰልጣኝ ተማሪ ኤደን ሰለሞን ህልፈተ ህይወት ጥልቅ ሀዘን የተሰማው መሆኑን እየገለፀ ለቤተሰቦቿ እና ለወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትን ይመኛል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
#ዜና | የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቲክኒክ ኮሌጅ በሙያ ደህንነት እና ጤንነት (occupational Safty and Health) ዙሪያ ሲያስለጥናቸው የቆየውን ከአስር ስድስት(16) በላይ የኢንዱስትሪ አንቀሳቃሽ ባለሞያዎችን አስመርቋል::
ኮሌጁ ይህን ስልጠና ሲያከናውን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ከሽንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ ጋር በመዋዋል የፋብሪካውን ከአስራ ስድስት (16 ) በላይ የሆኑ ሰራተኞችን አሰልጥኖ ማስመረቁን በወቅቱ ተጠቅሷል ።
በወቅቱ ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዳሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው በስሩ ዘርፈብዙ ስራዎችን እንደሚሰራ ጠቅሰው ከስራዎቹም መካከል የፋብሪካን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሞያ ክፍተቶችን በመሙላት ደህንነታቸው የተጠበቀ የበቁ ዜጎችን ማብቃት ነው ብለዋል ::
ቢሮው የሞያ ክፍተትን በስልጠና ማጠናከር ብቻ ሳይሆን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በኩል በአስተዳደሩ ለሚገኙ የተለያዩ ፋብሪካዎች መለዋወጫዎችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር ከውጪ ግብዓቱ የሚመጣበትንም ጊዜ እንዲቆጠብ እያደረገ ይገኛልም በማለት ሀላፊዋ አክለው ተናግረዋል ::
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ይህ የፋብሪካ ውስጥ የሞያ ደህንነትና የጤና አጠባበቅ ስልጠና እንደ ሀገር ያለ ክፍተት መኖሩን ጠቅሰው ኮሌጁ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሽንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ ጋር በመዋዋል የፋብሪካውን ከአስር ስድስት (16) በላይ ሰራተኞች ማሰልጠናቸውን ተናግረዋል ::
ስልጠናውን ተከታትለው የተመረቁት ስልጣኖች በበኩላቸው የወሰዱት የሞያ ደህንነትና የጤና ስልጠና ከፋብሪካ ውስጥ ስራችን ውጪም የግል ሕይወታችንን ለምን መራበት አካባቢም የሚጠቅመን ነው ብለዋል ::
በምረቃና ማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይም ስልጠናቸውን
ላጠናቀቁ ሰልጣኖች የእውቅና ስርተፊኬት ተሰጥቷል ::
#DireTvአማርኛ |ጥር 16 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
#እንኳን_አደረሳችሁ!!
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሠላም አደረሳችሁ እያልኩ፤ በዓሉ የሠላም፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
#መልላም_የጥምቀት_በዓል!!
አቶ ታደለ አሰፋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን
ኮሌጁ የታዳጊና ወጣቶችን ፈጠራ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተወጣጡ ተማሪዎች ግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ ለታዳጊዎች መልዕክት ያስተለፉት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ የብቁ ሞያተኞችና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መፍለቂያ ወደ ሆነው ተቋማችን እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን እዚህ እንድትገኙ የሆነበት ምክንያት አሁን ላይ በንድፍ ምትማሯቸውን ትምህርቶችን በተግባር ችግሮችን ለመፍታት የምትጠቀሙበትን አግባብ ለማስገንዘብ እንዲሁም ያላችሁን የፈጠራ ሀሳብ ከወዲሁ መሰረት የምታሲዙበትን መንገድ ለማመቻቸት እንደሆነም ገልፀዋል::
ባደጉት ሀገራት ከፍተኛ ተከፋይ መሆን የሚያስችሉት የክህሎት ሙያዎች እንደሆኑ የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ እንደ ፕሮጀክት በነዚህ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ ለማድረግ ስናስብ አስተዳደሩ ላይ ያሉ ወጣቶች የራሳቸው ሙያ ኖሯቸውና ከስራ ጋር ተገናኝተው እራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን እንዲደግፉ ለማስቻል ነውም ብለዋል::
በመድረኩ የፈጠራ ሀሳብን ወደ ተግባር አሳድጎ ችግር ፈቺ ቢዝነሶችን እውን የማድረግን ፅንሰ ሀሳብ በተመለከት የጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር አስተባባሪ በሆኑት አቶ ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት ግንዛቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ(STEM) ምንነትና በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ለታዳጊዎቹ ግንዛቤ ሰጥተዋል::
በቀጣይም የፈጠራ ሀሳብ ያላቸውን ታዳጊዎች በመለየት ሀሳባቸው ወደ ችግር ፈቺ ቢዝነሶች መለወጥ የሚያስችላቸውን ክህሎቶች በተቋሙ እንደሚሰጣቸውም ተገልፀዋል::
በእለቱ በተካሄደው የግንዛቤ መድረክም የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህርትና እና ሰልጣኝ ተማሪ ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎቹ በዘርፉ ያደረጏቸውን ስኬታማ ጉዞዎች እና የህይወት ልምዳቸውን ማካፈልም ችለዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥር 9/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የበጀት አመቱ የመጀመሪያ 6ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ::
በሪፖርት መድረኩ የEASE ፕሮጀክት በ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ 6ወር ውስጥ ለማከናወን በእቅድ በተያዙ ተግባራት መነሻነት የነበረውን አፈፃፀም ጨምሮ በፕሮጀክቱ የቀጣይ ስድስት ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከፕሮጀክቱ ኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት ጋር ውይይት ማድረግ ተችሏል::
የEASE ፕሮጀክት የ6ወር የስራ አፈፃፅም ሪፖርት በፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለኮሌጁ አድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላቱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ባለፉት 6ወራት ከተከናወኑ ተግባራት..
-የተለያዩ የሪኢኖቬሽን ስራዎች፣
-ለ8 የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንን በቻይና በElectric Vehicle ስልጠና እንዲበቁ ማድረግ)፣
-ለኮሌጁ ሰራተኞች እንዲሁም ለሰልጣኝ ተማሪዎች የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች መስጠት፣
-የኢንዱስትሪ አንቀሳቃሾችን የአቅም ግንባታ ስልጠና ስራን ጨምሮ በርካታ ቁልፍ ተግባራት መከናወናቸውን በሪፖርቱ በዝርዝር አመላክተዋል::
የኮሌጁ አመራሮችን ጨምሮ የአድቫይዘሪን ቦርድ አባላቱ በቀረበው የፕሮጀክት አፈፃፀምና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት አመላካች የሆኑ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት የተካሄበት የተገኙ የጋራ ውጤቶችን ለማስቀጠል በቀጣይ በተሻለ ትጋትና ቅንጅት ለመስራት ከመግባባት የተደረሰበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥር 7/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
