es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 365 suscriptores, ocupando la posición 1 754 en la categoría Transporte y el puesto 2 531 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 365 suscriptores.

Según los últimos datos del 19 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 119, y en las últimas 24 horas de 19, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 40.59%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 423 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 060 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 20 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 369
Suscriptores
+1924 horas
+677 días
+11930 días
Archivo de publicaciones
የቆሼ-ሚቶ-ወራቤ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ
+8
የቆሼ-ሚቶ-ወራቤ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ

73ኪ.ሜ የሚረዝመው የጉራጌ እና የስልጤ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የቆሼ-ሚቶ-ወራቤ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በመልካም የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ የቆሼ-ሚቶ-ወራቤ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ከአዲስ አበባ 158 ኪ.ሜ ርቀት ቆሼ ከተማ ላይ የሚጀምር ሲሆን፣ ኘሮጀክቱ የዲዛይንና ግንባታ መንገድ ነው፡፡ በግንባታ ላይ ከሚገኘው የወራቤ-ቦዥባር ፕሮጀክት ጋር የሚያገናኝ ሁነኛ መንገድም ነው፡፡ ነበሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ ያለ እና ከ6-7 ሜትር ያልበለጠ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በአስፋልት ኮንክሪት እየተገነባ ይገኛል፡፡ በዲዛይኑ መሰረት የመንገዱ ስፋት በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር፣ በወረዳ ከተማ 21 ሜትር እና በዞን ከተማ 22.5 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኝው የንኮማድ ኮንስትራክሰሽን ሲሆን ሽላዲያ አሾሼትስ እና ሂትኮን ኢንጂነርስ የቁጥጥር እና የማማከር ሥራውን በጥምረት እያከናወኑት ይገኛል፡፡ ለመንገዱ የሚውለው የገንዘብ መጠን 1‚850‚695‚155 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ አምስት) ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ በእስካሁኑ የሥራ እንቅስቃሴ፤ የዲዛይን እና የቅየሳ ሥራ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌትሥራ፣ የውሀ መፋሰሻ ቱቦ ሥራ፣ እንዲሁም ለፕሮጀክቱ ክንውን የሚያስፈልጉ ሌሎች ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ የተለዋጭ መንገዱ ተጠናቆ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን በቅርቡም የስትራክቸር ሥራ ይጀመራል፡፡ በፕሮጀክቱ ውስጥ የሶስት ድልድዮች ግንባታ ስራ የተካተተ ሲሆን ከዲዛይን ሥራ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን በማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ግንባታ ይሸጋገራል፡፡ ፕሮጀክቱ ከ400 በላይ ለሚሆኑ ለአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ እድል መፍጠር ችሏል፡፡ አካባቢው ከፍተኛ የሰብል (እንደ በቆሎ፣ ስንዴ፣ በርበሬ፣ ጤፍ፣ እና ቡና) የመሳሰሉትን የእህል ምርቶች አምራች እና እና ፍራፍሬ አብቃይ በመሆኑ የመንገዱ ተገንብቶ መጠናቀቅ አርሶ አደሮች ምርታቸውን በቀላሉ ከቦታ ወደ ቦታ ለማጓጓዝ ያስችላቸዋል የአርሶ-አደሩን የምርት ተጠቃሚነት ያሳድጋል፡፡ በተጨማሪም መንገዱ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአንድ ሰዓት በማሳጠር የህብረተሰቡን እንግልት በእጅጉ ይቀንሳል፡፡ በሥፍራው የሚገኝውን እምቅ የቱሪዝም ሀብት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመንገዱ መገንባት ፋይዳውን የጎላ ያደርገዋል፡፡

ከፍተኛ የትራንስፖርት ፍሰትን የሚያስተናግደው የአዲስ - ጊቤ ወንዝ ዋና መንገድ የከባድ ጥገና ስራ ሊካሄድለት ነው። መንገዱ ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንፃርም የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ከፍተኛ ጥገናውን ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በወጪ ገቢ ንግድ ምልልስ ፤ በክፍተኛ የትራፊክ ፍስት እና በአገልግሎት ሳቢያ መንገዱ ጉዳት አጋጥሞታል ። ይህን ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር መስመሩን በከፍተኛ ጥገና /አስፓልት ኦቨርሌይ/ እንዲሰራ ከሁለት የስራ ተቋራጮች ጋር ውል አስሮ እየተከታተለ ነው። በተካሄደው የመስክ የስራ ቅኝትም 64 ኪሜ የሚረዝመው የአዲስ -ጊቤ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አካል የሆነው ከአዲስ - ቆራ የሚዘልቀው መንገድ ከፍተኛ ጥገናን ለማስጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ለመመልከት ተችሏል፡፡ ከነዚህም መካከል ፣ የወሰን ማስከበር ስራዎች፣ የዲዛይን ክለሳ ስራዎች፣የአማካሪ መሃንዲስ መኖሪያ፣የቢሮ እና የላብራቶሪ ህንጻዎች እንዲሁም የተለዋጭ መንገድ ግንባታዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ ግንባታውን የሚሰራው የስራ ተቋራጭ ቤአይካ ጠቅላላ ንግድ ስራ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እንዲሁም የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ቤዛ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ነው፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚውለው 1ነጥብ 47 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ እንዲሁም ከቆራ -ጊቤ ወንዝ 93 ኪሜ ከፍተኛ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክት ለመገንባት በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም ለግንባታው 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የተጠየቀበት ከቆራ-ጊቤ ወንዝ ድልድይ ለሚዘልቀው የመንገድ ግንባታ የሚውለው ገንዘብም ከመንግስት በጀት ወጪ የሚደረግበት ነው፡፡ ፕሮጀክቱን ቲክስ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከኤም.ሲ.ጂ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህ በጋራ ያከናውኑታል፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራው ደግሞ ቤዛ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሚሰራው ይሆናል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሰበታ መወጫ ላይ ጀምሮ ቆራ ከተማ ላይ የሚበቃ ሲሆን ቀጣዩ ክፍል ደግሞ ቆራ ከተማ መወጫ ላይ ጀምሮ ጊቤ ወንዝ ድልድይ ላይ የሚያበቃ ነው፡፡ ጥገናውን በተያዘለት ዕቅድ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራውን በማጠናቀቅ በቅርቡ የመንገድ ጥገናውን ለማስጀመር እየተሰራ እንደሆነም ተመላክቷል፡፡ የመንገዱ ጥገና አሽከርካሪና ተሳፋሪዎች እንግልት በማስቀረት የትራንስፖርት ምልልሱን ምቹና የተቀላጠፈ እንዲሆንና በጉዞ ወቅት የሚያጋጥም የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ያስችላል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ደረጃውን ጠብቆ እንዲሰራም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል።

የወራቤ-ቦዥባር 41.39 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ
+5
የወራቤ-ቦዥባር 41.39 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ

የወራቤ-ቦዥባር 41.39 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በመስክ የሥራ ቅኝት ተጎበኘ 41.39 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወራቤ-ቦዥባር የመንገድ ኘሮጀክት የመስክ ጉብኝት የተካሄደ ሲሆን በጉብኝቱም የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ መሠረት እየተከናወነ አለመሆኑ ተገምግሟል፡፡ ለዚህም የሥራ ተቋራጩ የአፈፃፀም ውስንነቶች፣ ያልተጠናቀቁ የወሰን ማስከበር ሥራዎች በተለይም ከረጅም ጊዜ በፊት ክፍያ ተፈፅሞባቸው አሁንም ድረስ ያልተነሱ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች፣ ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮች እና የአካባቢው ዝናባማ የአየር ፀባይ በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡ በመሆኑም በሥራ ተቋራጩ እና ከሚመለከታቸው የኢ.መ.አ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት እና ምክክር በማድረግ ችግሩን በከፊል ለመቅረፍ ጥረት ተደርጓል፡፡ በግንባታው የተስተዋሉ የአፈፃፀም ውሱንነቶችን በአስቸኳይ በማረም፣ ተጨማሪ የሠው ኃይል እና የግንባታ ማሽነሪዎችን በማሰማራት፣ የግንባታ ሥራው በፍጥነት እንዲከወን በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአፈጻጸም መሻሻል ታይቷል፡፡የኘሮጀክቱ አፈጻጸም ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡ በሕብረተሰቡ በኩል የታየው ቀና ትብብር የካሣ ክፍያ ጭምር ሳይከናወንላቸው የእርሻ መሬታቸውን ለመንገዱ ሥራ ነጻ ያደረጉ በርካታ አርሶ አደሮች መኖራቸውና ይህም የትብብር መንፈስ በቀጣይም ለሚኖረው ሥራ ወሳኝ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ከዚህ በተጨማሪም በእስካሁን ያልተነሱ ንብረቶችን በማንሳት ረገድ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ይጠበቃል፡፡ የወራቤ-በዥባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ፣ መነሻውን ከወራቤ ከተማ አስተዳደር በማድረግ በዋናነት አልቾውሪሮ እና ቀበት ወረዳዎችን በቅርበት በማገናኝት ጠረጋ ላይ ያበቃል፡፡ መንገዱ በከተማ 21.5 ሜ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር10 ሜትር የጎን ስፋት አለው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ወደ ወልቂጤ እና ጅማ ለመሄድ በቡታጅራ በኩል የሚደረገውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት ቀጥታ በወራቤ-ቦዥባር በኩል ለመጓዝ ያስችላል፡፡ የሕብረተሰቡ ከእንግልት በመታደግ የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የእንሰት ውጤቶች፣ ጎመን እና ሌሎች የእርሻ ውጤቶችን በፍጥነት እና በጥራት ወደ ማዕከላዊ የገበያ ሥፍራ ለማድረስ ያስችላል፡፡በተጨማሪም በሥፍራው የሚገኙትን አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማነት የሚያድጉበት ምቹ እድል ይፈጥራል፡፡ ለፕሮጀክቱ ሥራ የሚውለው 795 ሚሊዮን ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ የመንገዱን ግንባታ እያከናወነ የሚገኝው ማርካን ትሬዲንግ ኃ/የ/የግ/ማ ሲሆን ግንባታውን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ደግሞ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ እያከናወነው ይገኛል፡፡

የሀገረመቆር - ቁንዲ ክፍል ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+5
የሀገረመቆር - ቁንዲ ክፍል ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የሀገረመቆር- ቁንዲ ክፍል ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በያዝነው በጅት አመት ዋና ዋና ስራዎቹን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው። አሁን ላይ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም 90 በመቶ ላይ ደርሷል። 102 ኪ.ሜ የሚረዝመው ይህ ፕሮጀክት 81 ኪ.ሜ የሚሆን የአስፓልት ንጣፍ ስራው ተጠናቋል ፡፡ ቀሪ ዋና ዋና ስራዎችን ጨምሮ የማጠቃለያ ስራዎችን ለመፈጸም በትኩረት እየተሰራ ። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም-አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሚኒኬሽን ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ መንገዱን ለመገንባት የሚስፈልገውን አንድ ቢሊየን አምስት መቶ ሃምሳ ስምት ሚሊየን አንድ መቶ ሃምሳ ሺብር በኢትዮጵያ መንግስት እየተሸፈነ ነው ፡፡ የማማከሩን እና የቁጥጥሩን ስራ ስታዲያ ኢንጅነሪንግ ከጂ እና ዋይ ኢንጅነሪንግ ጋር በጥምረት እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በገጠር 8 ሜትር፣ በወረዳ 19 ሜትር እና በቀበሌ 14 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው፡፡ ከዚህ ቀደም መንገዱ ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ምቹ ያልሆነ በመሆኑ የተነሳ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ እንግልት የዳረገ ነበር፡፡ መንግስት ይህንን ችግርም ለመቅረፍ አሁን ላይ በአስፓልት ደረጃ እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን ሲጠናቀቅ ይህንን ችግር ከመፍታት ባለፈ በዋናነት ጨረቲ ወረዳን ከጎሮበቀቅሳ እና ከጎሮዳሞሌ ወረዳ ጋር ያገናኛል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢዉ የሚገኙትን ከፍተኛ የቁም እንስሳት እና የእንስሳት ተዋፅዖ ምርቶችን በፍጥነት ወደገበያ ለማድረስ ያግዛል፡፡ የዚህ መንገድ አካል የሆነው የጨረቲ- ሀገረመቆር ሎት1 መንገድ ግንባታው ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ይታወሳል ፡፡ ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት መነሻውን ጨረቲ ከተማ ላይ አድርጎ ቁንዲ ከተማ ላይ የሚያበቃ ሲሆን ፡የጨረቲ -ጎሮበቀቅሳ- ጎሮዳሞሌ - ሀገረመቆር- ቁንዲ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አካል ነው።

የሀሙሲት - እስቴ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+6
የሀሙሲት - እስቴ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የሀሙሲት-እስቴ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ይገኛል ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ከተጀመረ አንድ ዓመት ከአምስት ወራትን አስቀጥሯል። አጠቃላይ የመንገዱ ርዝመት 76.64 ኪ.ሜ ሲሆን ፣ አጠቃላይ ግንባታውን ለማካሄድ የሚያስፈልገው የግንባታ ወጪ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ነው። መንገዱን ለመገንባት የሚወጣው ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት፣ Arab Bank for Economic Development in Africa (BADEA) እና OPEC Fund for International Devlopment (OFID) ይሸፈናል። ግንባታውን የሚያከናውነው ኒንዥያ ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ግሩፕ ኮርፖሬሽን በአሁኑ ወቅት ከአጠቃላይ ስራው 21 በመቶ አከናውኗል። የስራ ተቋራጩ በቅድሚያ ተለዋጭ መንገድ በማዘጋጀት የተለያዩ የስትራክቸር ስራዎችን ፣ የአፈር ሙሊት ፣ ማፋሰሻዎችን እና የድልድይ ስራ እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ስራዎችን ከማከናወን አልፎ የአስፋልት ንጣፍ ስራ ጀምሯል። በተያዘው ዓመት ከአጠቃላይ ስራው 26 ኪሎ ሜትር አስፋልት ለማከናወን አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። የአካባቢው ነዋሪዎች እና የመስተዳድር አካላት በፕሮጀክቱ አፈፃፀም ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ከኻቲብ እና አለሚ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነሪንግ ከሀገር በቀሉ ኮር ኮንሰልቲንግ (Khatib & Alami Consulting Engineers with Core Consulting Group) ጋር በጋራ በመሆን ያካሂዱታል። የሀሙሲት-እስቴ በጠጠር መንገድ ደረጃ ላለፉት ረጅም አመታት የትራንስፖርት ግልጋሎት ሲሠጥ የቆየ ሲሆን ነባሩ መንገድ ከ6 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋት ያለውና ጠባብ የነበረ ነው። በአስፋልት ደረጃ ሲገነባ ስፋቱ በወረዳ 19 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 1ዐ ሜትር ይሆናል። አሁን ባለዉ ሁኔታ ከሀሙሲት -እስቴ 76.64 የሚረዝመዉን መንገድ በተሸከርካሪ ለመጓዝ ከ ሶስት ሰዓት በላይ ይጠቃል። ግንባታው በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ጊዜን በአማካኝ ከግማሽ በላይ በማሳጠር ህብረተሰቡ ደረጃዉን የጠበቀ መንገድ ተጠቅሞ በፍጥነት እና በተመጣጣኝ የትራንስፖርት ዋጋ ወደፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ ስምንት ድልድዮችን የሚያካትት ሲሆን የተለያዩ ፉካዎችን ይኖሩታል፡፡ የመንገዱ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት በዋነኝነት የሀሙሲትን እና የእስቴን ከተማ በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ያስተሳስራል። በተጨማሪም በመስመሩ ተራርቀው የነበሩ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች በቅርበት በማስተሳሰር ይበልጥ በኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥርላቸዋል ፡፡ እንዲሁም ለአካባቢው ህብረተሰብ የስራ እድል በስፋት እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን የግብርና ምርቶች በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ ፕሮጀክቱ በኮንትራት ውሉ መሰረት ግንባታው በሶስት ዓመት ጊዜ ወስጥ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

መልካም በዓል!

የማንኩሳ-ብር ሸለቆ ማሰልጠኛ ካምፕ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+8
የማንኩሳ-ብር ሸለቆ ማሰልጠኛ ካምፕ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የማንኩሳ-ብር ሸለቆ ማሰልጠኛ ካምፕ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ሰሞኑን በመስክ የሥራ ቅኝት ተጎብኘቷል፡፡ ፕሮጀክቱ በቅርቡ የተጀመረ ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ አፈጻጻሙ በእቅዱ መሰረት እየተከናወነ ነው። በእስካሁኑ የግንባታ ሥራ እንቅስቃሴ የቅየሳ ስራ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የውሃ መተላለፊያ/መፋሰሻ ቱቦዎች ሥራ /የሰብ ቤዝ ሥራዎችን ጨምሮ ሌሎች የስተራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ 36 ኪ.ሜ የሚረዝመው ፕሮጀክቱ መነሻውን ከአዲስ አበባ 400 ከ.ሜ ርቀት ላይ ከምትገኘው ማንኩሳ ከተማ በማድረግ የተለያዩ ከተሞችን በቅርበት በማስተሳሰር የደብረማርቆስ-ደብረኤሊያስ-ቁጭ መንገድን ይቀላቀላል፡፡ ግንባታውን ቲክስ ኮንስትራክሽን እና ፋል ጄነራል ኮንትራክተር በጥምረት እያከናወኑት ነው፡፡ የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ትራንስ ናሽናል ኢንጂነሪንግ ሃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ ግንባታው የሚጠይቀው 972,716,279 (ዘጠኝ መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን ሰባት መቶ አሥራ ስድስት ሺህ ሁለት መቶ ሰባ ዘጠኝ ብር) ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ የፕሮጀክቱ ሥፍራ በተለይም የብርሸለቆ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ካምፕ መዳረሻ እንደመሆኑ መጠን የመንገዱ መገንባት ሀገራዊ ፋይዳውን የጎላ ያደርገዋል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የተለያዩ የሰብል እና የቅመማ-ቅመም ምርት ውጤቶችን በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያሳድጋል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ ሰፋፊ የመንግስት እና የግል የግብርና ምርቶች መቀላጠፍም ሚናው የላቀ ነው። የጤና ፣ የትራንስፖርትና የሌሎች ማሕበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተደራሽነትን ያስፋፋል፡፡ የማንኩሳ-ብርሸለቆ ነባር መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ በመሆኑ እጅግ አሰቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል። መንግስት አካባቢው ካለው ሰፊ እስትራቴጂካዊ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ ወሰኖ በመፋጠን ላይ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በወረዳ ከተማ 21.5 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል፡፡

የሀዋሳ አየር ማረፍያ ቢሻን ጉራቻ ጥቁር ውሀ የመንገድ ፕሮጀክት
+2
የሀዋሳ አየር ማረፍያ ቢሻን ጉራቻ ጥቁር ውሀ የመንገድ ፕሮጀክት

የሀዋሳ አየር ማረፍያ ቢሻን ጉራቻ ጥቁር ውሀ የመንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ ፡፡ 35 ኪ.ሜ የሚረዝመው የመንገድ ስራ ግንባታ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎም በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ የሀዋሳ ኤርፖርትን መዳረሻው ሰለሚያደረግ በዋናነትም ለሲዳማ እና ደቡብ ክልሎች የዓየር ትራንስፖርት ተጠቃሚዎች የመንገዱ መገንባት ምቹ መሰረተ ልማትን ዕውን በማድርግ እስትራቲጂካዊ ጠቀሜታውን የጎላ አድርጎታል ። ብሎም ለሀዋሳ ሀይቅ እና ለአካባቢው ተደራሽ በመሆኑ የቱሪዝም ፍሰትን እንዲጨምር በማድረግ እረገድም ሚናው ላቅ ያለ ነው። በሀይቁ ውስጥ የሚገኘውን ከፍተኛ የዓሳ ምርት በአጭር ጊዜ ወደገበያ ለማውጣትም ያስችላል፡፡ በተጨማሪም በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚመረቱ ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የተለያዩ አልባሳትን መንገዱን በመጠቀም ወደ ሀዋሳ አየር ማረፍያ ለማድረስ ይረዳል፡፡ የመንገዱ መገንባት ከዚህ ቀደም መንገድ ተጠቃሚውን ህዝብ ይፈጠርበት የነበረውን ማህበራዊ እንግልት በማስቀረትይ የተቀላጠፈ የትራንስፖርት ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሎታል ። ቀድም ብሎ በግንባታው ላይም ከፍተኛ የሆነ የወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ቢያጋጥምም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከከተማው አስተዳደር እና ባለደርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ርብርብ እና የቅርብ ክትትል በማድረግ በተሻለ ጥራት ፕሮጀከቱ ለፍጻሜው በቅቷል ፡፡ የሀዋሳ አየር ማረፍያ ቢሻን ጉራቻ ጥቁር ውሀ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሁለት ክፍሎች ያሉት ሲሆን የመጀመሪያው 14 ኪሎሜትር ከቢሻን ጉራቻ ጥቁር ውሀ በመነሳት ወደ ሀዋሳ አየር ማረፍያ የሚሄድ ሲሆን ሁለተኛው 21 ኪሎሜትር የሚሆነው ከሀዋሳ ከተማ በመነሳት ወደ ሀዋሳ አየር ማረፍያ የሚያቀና መንገድ ነው፡፡ መንገዱን ገንብቶ ለማጠናቀቅ የወሰደውን 592,084,000.00 ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ በአስፋልት ኮንክሪት የተሰራው ይህ ፕሮጀክት የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር፣በከተማ 21.5 ሜትር፣በወረዳ 14 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው፡፡ የመንገዱን ግንባታ አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ አከናውኖታል፡፡ በማማከርና በቁጥጥር ስራው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ሱፐርቪዥን ኮርፖሬሽን ተሳትፏል፡፡

የአለውሃ ድልድይ
+2
የአለውሃ ድልድይ

በወራሪ ቡድኑ የጥፋት ተግባር ተሰብሮ የነበረው የአለውሃ ድልድይ በአዲስ የብረት ድልድይ የግንባታ ስራው ተጠናቆ ለትራንስፖርት አግልግሎት ከዛሬ ጀምሮ ከፍት መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር አ
በወራሪ ቡድኑ የጥፋት ተግባር ተሰብሮ የነበረው የአለውሃ ድልድይ በአዲስ የብረት ድልድይ የግንባታ ስራው ተጠናቆ ለትራንስፖርት አግልግሎት ከዛሬ ጀምሮ ከፍት መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር አሰታወቀ። በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ ዲስትሪክት ባለፉት ቀናት አዲሱን የብረት ድልድይ ግንባታ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ ሲያድርግ ቆይቷል ። ይህን ተከትሎም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት የነበረውን ይህን ድልድይ በአዲስ የብርት ድልድይ በመገንባት መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት ዳግም እንዲጀመር ተደርጓል። የብረት ድልድዩ እስከ 600 ኩንታል ወይም 60 ቶን ድረስ መሸከም የሚችል አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ነው። የብረት ድልድዩ አጠቃላይ ርዝመቱ 54 ነጥብ 86 ሜትር ነው። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአካባቢው ያለውን የትራፊክ ፍሰት እና የምርት ምልልስ ታሳቢ ያደረገ ደረጃውን የጠበቀ ድልድይ ለመገንባት እየተነቀሳቀሰ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የዲዛይን ስራው የተጠናቀቀ ሲሆን በቀጣይ ወደ ግንባታ ስራ ይሸጋገራል የአለውሃ ድልድይ በሰሜን ወሎ ዞን ከወልድያ ወደ ቆቦ በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ነው።

የአርብ ገበያ-ሰከላ-ቲሊሊ ክፍል ሁለት የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+7
የአርብ ገበያ-ሰከላ-ቲሊሊ ክፍል ሁለት የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት