es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 348 suscriptores, ocupando la posición 1 755 en la categoría Transporte y el puesto 2 537 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 348 suscriptores.

Según los últimos datos del 18 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 91, y en las últimas 24 horas de 11, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 41.16%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.44% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 491 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 060 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 19 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 351
Suscriptores
+1124 horas
+477 días
+9130 días
Archivo de publicaciones
የወልደሃኔ-ዱርጌ 41 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል መስከረም 29፣ 2016 (ኢ መ አ):- የደቡብ ምዕራብ ሕዝቦችን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጋር የሚያስተሳስረው የወልደሃኔ-ዱርጌ 41 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል ። የመንገድ ግንባታው ከስድስት ወራት በፊት የተጀመረ ሲሆን፥ አሁን ላይ የቅየሳ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የለውጥ መንገድ እና የመኖሪያ ካምፕ ግንባታ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ። በተጨማሪም የወሰን ማስከበር የግምት እና ልኬት ሥራዎች በሰፊው እየተከናወኑ መሆኑን ቦታው ድረስ በተደረገ የመስክ ቅኝት መመልከት ተችሏል፡፡ በዚህ ረገድ በአካባቢው ማኅበረሰብ እና የመስተዳድር አካላት ንብረት ካሳ ሳይከፈል በማንሳት በኩል የታየው ትብብር እንዳለ ሆኖ በንብረቶቹ ቆጠራና ስነዳ ላይ ያለው የጥራት ችግር ቁጥጥርና ክትትል የሚያስፈልገው መሆኑም በቅኝቱ ተመላክቷል፡፡ በዚህ ዓመት መጨረሻ የግንባታውን አጠቃላይ የአፈጻጸም ደረጃ ከ31 በመቶ በላይ ለማድረስ እየተሰራ ሲሆን የሥራ ተቋራጩ በዳውሮ ዞን ጌና ወረዳ በኩል ያለው የመንገድ ክፍልም ለመጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ሀገር በቀሎቹ ኤም ሲ ጂ ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግል ማኅበር እና ሜልኮን ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግል ማኅበር በጥምረት የግንባታውን ሥራ ያከናውናሉ። የጥራት ቁጥጥሩን እና የማማከሩን ሥራ ደግሞ ቤዛ አማካሪ መሃንዲሶች ኃ.የተ.የግል ማኅበር በጋራ ከቤዛ ምህንድስና ኬንያ ሊሚትድ ጋር ይሠራሉ። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዳውሮ ዞንን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠንባሮ ልዬ ወረዳ ጋር በማቆራኘት ቀድሞ በሶዶ በኩል ይወስድ የነበረው 250 ኪ.ሜ የጉዞ ርቀት ወደ 49 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል። በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ዝንጅብል፣ ቀርከሃ እና መስል የግብርና እና የከብት እርባታ ምርት ውጤቶች ወደ መሐል ገበያ በቀላሉ ለማድረስ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመንገድ ዓይነቶች እና የአገልግሎት ደረጃ መንገዶች በሶስት ይመደባሉ፡- የፌደራል፣ የክልል እና የከተማ መንገዶች። የፌዴራል መንገዶችን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሲሆን፣ የክልል እና የአካባቢ መንገዶችን በባለቤትነት የሚያስተዳድሩት ለዚሁ ዓላማ ተብለው በየክልሉ መንግስታት የተቋቋሙ የክልል መንገድ ኤጄንሲዎች ናቸው፡፡ በተመሳሳይ የከተማ መንገዶችን በባለቤትነት የሚያስተዳድሩት በየከተማ አስተዳደሩ ለዚሁ ዓላማ የተቋቋሙ ተቋማት ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የፍጥነት መንገዶች፤ዋና መንገዶች እና አገናኝ መንገዶች የፌዴራል መንገዶች፣ ሰብሳቢ እና መጋቢ መንገዶች የክልል መንገዶች ሲሆኑ፣ በከተማ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን የፌዴራል መንገዶች አካል ያልሆኑ መንገዶች የከተማ መንገዶች ናቸው፡፡ ኢ መ አ የፌደራል መንገዶች ማለትም የፍጥነት፣ አውራ፣ ዋና መዳረሻ መንገዶችን የማልማትና የማስተዳደር ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ የፍጥነት መንገዶች እና አውራ መንገዶች አዲስ አበባን ከጐረቤት ሀገራት እና ወደቦች ጋር የሚያገናኙ እና አዲስ አበባን ከክልል ዋና ከተሞች እና ከሌሎች ከፍተኛና መካከለኛ ከተሞች ጋር የሚያገናኙ መንገዶች ናቸው፡፡ ዋና መዳረሻ መንገዶች ለልማት ሊውል የሚችል ሰፊ እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ከሚገኝባቸውና ከአቅራቢያቸው በሚገኙ ወንዞች በመስኖ ሊለሙ ከሚችሉ አከባቢዎች ፣ ከፍተኛ ትርፍ የምግብ ሰብል (Cash Crops) ከሚመረትባቸው አከባቢዎች፣ እምቅ የማዕድን ሃብት ከሚገኙባው ቦታዎች እንዲሁም ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት ከሚገኝባቸው የገጠር አካባቢዎች ጋር የሚያገናኙ መንገዶች ናቸው፡፡ የክልል እና የአካባቢ መንገዶችን የማልማትና የማስተዳደር ኃላፊነት የተሰጣቸው የክልል መንገድ ኤጄንሲዎች በዋናነት የወረዳ ከተሞችን ከዞን ዋና ከተሞች ጋር የሚያገናኙ፣ የወረዳ ዋና ከተሞች ከወረዳ መለስተኛ ከተሞች ጋር የሚያገናኙ እንዲሁም የወረዳ ዋና ከተሞች ከወረዳ የልማት ከተሞች ጋር የሚያገናኙ መንገዶችን የማልማትና የማስተዳደር ሥራዎችን ያከናውናሉ፡፡ በቀጣይም የክልል መንገድ ኤጀንሲዎች ያላቸውን ኃላፊነት የሚያሻሽል/የሚያሳድግ ጥናት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ለመንግስት ቀርቦ ሲጸድቅ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ የከተሞች መንገድ ኤጄንሲዎች በከተማ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን የፌዴራል መንገዶች አካል ያልሆኑ መንገዶችን የመገንባት፣ የመጠገንና የማስተዳደር ሥራዎችን በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ዋና መዳረሻ መንገዶች እንደየሚገነቡበት ዓላማ እየታየ የፌዴራል፤ የክልል ወይም የከተማ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የማናቸውንም የፌዴራል መንገዶች የመንገድ ክልል ስፋት ይወስናል፡፡ በተመሳሳይ የክልል የመንገድ ተቋም የማናቸውንም የክልል መንገዶች የመንገድ ክልል ስፋት የሚወስን ሲሆን፣ የከተማ የመንገድ ተቋም የማናቸውንም የከተማ መንገዶች የመንገድ ክልል ስፋት ይወስናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

መልካም በዓል!
መልካም በዓል!

መልካም በዓል!

የሃላባ፣ ከምባታ እና ሃዲያ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የሃላባ-አንጋጫ-ዋቶ እና ዳምቦያ-ዱራሜ 65 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን መካከል በተገባው ውል መሠረት 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞለት በታኅሳስ ወር 2013 ወደ ግንባታ መገባቱ ይታወቃል። ነገር ግን በዋናነት በሥራ ተቋራጩ አቅም ማነስ፣ ከኅብረተሰቡ በቀረበ የዲዛይን ይሻሻልን ጥያቄ፣ የግንባታ ዕቃዎች የአቅርቦት እጥረት እና የዋጋ መናር እንዲሁም ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግር፣ አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ ከሚጠበቀው ደረጃ ላይ አልደረሰም። የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቱ አፈፃፀም በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ ተደጋጋሚ የመስክ ጉብኝቶች እና ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን፣ አስፈላጊው ድጋፍ እና ትብብር እየተደረገ ነው፡፡ በአሁን ወቅትም የመንገድ ግንባታው ተነካክቶ የትራፊክ ፍሰቱን እንዳያስተጓጉል አስፈላጊው የመንገድ ጥገና ተደርጓል። ከዚህም ባለፈ የአካባቢው የተራዘመ የክረምት ወራት የትራፊክ ፍሰቱ ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድር በተመሳሳይ አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል፡፡ ስለሆነም መንገዱ አሁን ላይ የትራፊክ እንቅስቃሴውን በማያስተጓጉልበት ደረጃ ላይ ይገኛል። በቀጣይም አስፈላጊው የጥገና ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። መንገዱ የሚገነባበት አዝጋሚ ፍጥነት በኅብረተሰቡ ላይ ቅሬታ የፈጠረ መሆኑን በመገንዘብ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሥራ ተቋራጩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተከታታይ ምክክር እያደረገ እና ሌሎች አማራጮችንም እያጤነ/እየመረመረ ይገኛል፡፡ ችግሮቹን በአጭር ጊዜ ለመቅረፍ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ በመሆኑ፣ ኅብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ ኢ መ አ ይጠይቃል። በተጨማሪ መረጀዎች › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በተንጠልጣይ ድልድዮች ( Trial Bridges ) ማኑዋል ዙሪያ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ መስከረም 9 ቀን 2016 ዓም (ኢመአ)፡ ሄልቬታስ ኢትዮጵያ ( HELVETAS ETHIOPIA ) እና ድልድይ ለብልዕግና ( Bridges Prosperity ) በተሰኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፉ ድርጅቶች የተዘጋጀና በተንጠልጣይ ድልድዮች ( Trial Bridges ) ማኑዋል ዙሪያ ውይይት ትኩረት ያደረገ ውይይት ተካሄደ፡፡ የውይይት መድረኩ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት ከዚህ ቀደም አገልግሎት ላይ ይውል የነበረውን የተንጠልጣይ ድልድዮች ማኑዋል ማሻሻል በማስፈለጉ ነው ፡፡ ለሁለት ቀናት በሚውለው በዚሁ መድረክ ላይ ከከተማና ልማት ሚኒስተር ፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ፣ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ፣ ከተለያዩ ክልሎች ወዘተተረፈ የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን በተንጠልጣይ ድልድዮች ዙሪያ የተደረጉ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል ፡፡ መቀመጫውን በአገረ ስዊዘርላንድ ያደረገው ሄልቬታስ በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 20 ዓመታት በስድስት ክልሎች ማለትም በኦሮሚያ ፣ በአማራ ፣ በማዕከላዊ ደቡብ ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ፣ በሲዳማ እና በሶማሊያ ክልሎች 126 ተንጠልጣይ ድልድዮችን ለመገንባት ችሏል ፡፡ ለቀጣይ ሶስት ዓመታት በሚቆየው በዚሁ ፕሮግራም ትግበራ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች አንድ መቶ ሃምሳ ( 150 ) ተንጠልጣይ ድልድዮች ተገንብተው ለአንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃምሳ ሺ ( 1 350 000 ) ዜጎች አገልግሎት ይሰጣሉ ተብሎ ይገመታል ፡፡ ይህ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጀት ተንጠልጣይ ድልድዮችን ለመገንባት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ በዚሁ ዓመት ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር መፈራረሙ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጅግጅጋ-ገላልሼ-ደገሕመደው-ሰገግ አስፋልት መንገድ ግንባታ ምዕራፍ ሁለት የማጠቃለያ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2016 (ኢ መ አ) በሶማሌ ክልል 109 ነጥብ 82 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የጅግጅጋ-ገላልሼ-ደገሕመደው-ሰገግ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ምዕራፍ ሁለት የማጠቃለያ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ 55 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው በፕሮጀክቱ ምዕራፍ ሁለት የማጠቃለያ ሥራዎች እየተከናወኑ የሚገኘ ሲሆን፣ የግንባታውን ሥራ በሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ ከአጠቃላይ የፕሮጀክቱ ክፍል አሁን ላይ 33 ኪሎ ሜትሩን አስፋልት ማልበስ ተችሏል፡፡ እንዲሁም የስድስት ድልድዮች ግንባታ ሥራ በከፊል ተጠናቅቋል፡፡ በተጨማሪም የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የማፍሰሻ ቱቦ እና የፉካ፣ የሰብ ቤዝ፣ የቤዝ ኮርስ፣ የአስፓልት ፤ የቤዝ ኮርስ እና የኮንክሪት ጠጠር መፍጨት እና የመንገድ መስመሮችና ምልክቶችን የመትከል ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ሀገር በቀሉ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ሲ-ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ እየሰራ ነው፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1,828,264,182.76 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊዮን) ብር፣ ወጪው ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል፡፡ በክልሉ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ የተፈጠረው የውኃ እጥረት በግንባታው ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ ለመቅረፍ በሥራ ተቋራጩ በኩል ዘጠኝ የውኃ ማጠራቀሚያ ኩሬዎች ተዘጋጅተው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡ ኩሬው ከግንባታው አልፎም የአካባቢውን ማኅበረሰብ እየጠቀመ ይገኛል፡፡ በግንባታው ሂደት የገጠመውን የግንባታ ጥሬ ዕቃ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል የተለያየ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ፥ ቀድሞ ወደ ደገሕመደው ከተማ ለመሄድ፣ በደገሐቡር በኩል ይወስድ የነበረውን የ240 ኪ.ሜ ርቀት ወደ 195 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡ በመሆኑም ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን 4 ሰዓት ተኩል የጉዞ ጊዜ በአንድ ሰዓት ዝቅ ያደርገዋል፡፡ የፋፈን እና ደገሐቡር ዞኖችን በቅርበት በማገናኝት፥ በአካባቢው የሚገኙ አርብቶ-አደሮች እና በእንስሳት ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችንም ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በፕሮጀክቱ ክልል የሚገኙትንም አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማነት የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡ የዚሁ ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ ቀደም ሲል ተጠናቅቆ በአሁኑ ወቅት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ አሁን በግንባታ ላይ ያለው የምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክት ቀጣይ ክፍል ከኪሎ ሜትር 55 እስከ 109 ነጥብ 82 ኪሎ ሜትር ያለው በተያዘው በጀት ዓመት የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአቅም ግንባታ ሥልጠናም እየተሰጠ ነው፤ የግንባታውን ዘርፍ ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ በሚያደርግ ተክኖሎጂ ዙሪያ ወርክሾፕም ተካሄደ ------------------------------------------------------- አዲስ አበባ ፣ መስከረም 8 ቀን 2016 ዓም (ኢመአ): ከአፍሪካ ቀንድ ሀገሮች ለመጡ ሲቪል መሃንዲሶች ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ ፡የግንባታውን ዘርፍ ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ በሚያደርግ ተክኖሎጂ ዙሪያ ወርክሾፕም ተካሄደ፡፡ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአለም ገና ኢንጂነሪንግና ማኔጅመንት ማሰልጠኛ ማእከል የተጀመረውና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከአለምአቀፍ ሰራተኞች ማህበር /International labor Organization ( ILO ) / ጋር በመተባበር እየተሰጠ ባለው ስልጠና መንገድም ሆነ ድልድዮች ከመገንባታቸው አስቀድሞ በሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሁም በሰራተኞች አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ የመንገድ ኢንቨስትመንት ፕሮግራም ዙሪያ ነው፡፡ በአለምአቀፍ ሰራተኞች ማህበር / International labor Organization ( ILO ) / ስፖንሰር አድራጊነት በተዘጋጀው በዚህ ስልጠና 26 ሰልጣኞች የተሳተፉ ሲሆን አስራ ሰባቱ (17) ከሶማሊያ የመጡ ሲሆን ቀሪዎቹ ዘጠኝ ተሳታፊዎችም ከደቡብ ሱዳን እና ከኢትዮጵያ ተሳታፊ ሆነዋል ፡፡ ለ15 ቀናት በሚቆየው የስልጠና መርሃግብር የሚካተቱት ኮርሶች በተግባር የተደገፉ ሲሆን ለሀገራቱ ጠቃሚ መሆናቸው ታምኖበት እየተሰጠ እንደሚገኝ አሰልጣኞቹ ገልጸዋል ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት ለመጡ በምህንድስና ተያያያዥ የሙያ ዘርፎች ለተሰማሩ ሙያተኞች ተሞክሮዎችና ልምዶቹን ሲያካፍል መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይም በግንባታም ሆነ በድህረ ግንባታ ወቅት የአፈር መረጋጋት (soils stability) በመፍጠር ደረጃውን የጠበቀ የግንባታ ሂደት ለማረጋገጥ የሚያስችል ኢንቫሮ ታክ የተሰኘ ቴክኖሎጂን አስመልክቶ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቃሊቲ የመንገድ ምርምር ማዕከል ዎርክሾፕ ተካሂዷል። Black Stone Road Development በተባለው የአሜሪካ ድርጅት የበለፀገውን የኢንቫሮ ታክ ቴክኖሎጂን በጥርጊያም ሆነ በአስፋልት መንገድ ግንባታ ሂደት ላይ መጠቀም እንደሚቻል ነው የተነገረው። በወርክሾፑ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዘርፉ ባለሙያዎች ፣ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ፣ አማካሪ መሃንዲሶች እና ከክልል ገጠር መንገድ ቢሮዎች የተውጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሀገር በቀል እና አለምአቀፍ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የግንባታው ዘርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲሻሻል ለማስቻል የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ለዚህም በዛሬው ዕለት የተካሄውን ዎርክሾኘ ጨምሮ በየጊዜው እየተከናወኑ ያሉ ተመሳሳይ ጥናቶች ሁነኛ ማሳያዎች ናቸው።

መልካም አዲስ ዓመት! ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልጽግና!
መልካም አዲስ ዓመት! ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልጽግና!

መልካም አዲስ ዓመት! ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልጽግና!

በፊቅ-ሰገግ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ስራ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጀት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው አዲስ አበባ፣ ጳግሜ 02፣ 2015 (ኢ መ አ) ፡- በሶማሌ ክልል የፊቅ-ሰገግ-ገርቦ-ደናን ፕሮጀክት አካል የሆነው ምዕራፍ አንድ ፊቅ-ሰገግ አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 90 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍን ሲሆን ፣ በሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ የአስፋልት ንጣፍ ሂደቱን ለመጀመር የቅድመ ዝግጀት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ አሁን ላይ በዋናነት የሰብቤዝ ሥራ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን፥ ጎን ለጎን የጠረጋ ፣ የማፋሰሻ ቱቦ የማምረት፣ የሮድ ቤድ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ አጠቃላይ የግንባታ ሥራው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉል ተለዋጭ መንገድ ተገንብቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው። የሁለት ድልድዮች ግንባታ ሥራ የተጀመረ ሲሆን፣ ቀሪ ስድስት ድልድዮች በሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ ግንባታውን ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ - ተቋራጭ ድርጅት በማከናወን ላይ ነው፡፡ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ. ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ እየሠራ ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው አንድ ቢሊየን አራት መቶ ሃያ ሁለት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ብር /1,422,968,463.00 / ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የሚሸፈነው። በክልሉ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን ድርቅ ተከትሎ የተፈጠረው የውኃ እጥረት፣ ከወሰን ማስከበር ጋር የሚነሱ ጉዳዮች በወቅቱ እልባት አለማግኘታቸው እንዲሁም በኅብረተሰቡ በኩል የሚነሱ አግባብነት የጎደላቸው ጥያቄዎች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል፡፡ ችግሮቹን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር፣ ከሥራ ተቋራጩ እንዲሁም ከዞንና ወረዳ መስተዳድር አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን እያደረገ በመሆኑ አዎንታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አፈጻጸምም 35 በመቶ ደርሷል፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 675 ኪ.ሜ ርቀት ፊቅ ወረዳ ላይ ጀምሮ ሰገግ ወረዳ ላይ ያበቃል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ኤረር ዞን እንዲሁም ሰገግ እና ዮሆብ ወረዳዎችን በቅርበት ያገናኛል፡፡ ከጎዴ-ጅጅጋ-ሐረር ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜና የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሰዋል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦችም የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የዚሁ መንገድ ፕሮጀክት ትስስር ቀጣይ ክፍል የሆኑት ምዕራፍ 2 ሰገግ-ገርቦ-ዮአለ አስፋልት መንገድ በግንባታ ላይ ይገኛል።

በመንገድና የድልድይ ሀብት አስተዳደር ስርዓት አደረጃጀት እና የመሬት መንሸራተት ቁጥጥር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሄደ። በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና በአለም አቀፉ የጃፓን ድርጅት (JICA) ትብብር በመንገድና የድልድይ ሀብት አስተዳደር ስርዓት አደረጃጀት እና በመሬት መንሸራተት መከላከልና ቁጥጥር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ነዉ በተቋሙ የመንገድ ምርምር ማዕከል የተካሄደው። በጥናቱ የኢመአ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሂሩት ዮሐንስ፣ በኢትዮጵያ የ ጂ አይ ካ የፕሮጀክት ቀረፃና አማካሪ ሚስተር ማሳዮሺ ካዋይ ፣የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የስራ ሃላፊዎች እና በመንገድ ዘርፉ የተሰማሩ አካላት ተገኝተዋል። በዕለቱም (JICA) በሀገረ ጃፓን በመንገድና ድልድዮች ጥገናና በመሬት መንሸራት ቁጥጥር ላይ ያላቸውን ተሞክሮ እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በተለይም የመሬት መንሸራትን አስመልክቶ ያጠናው ጥናት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። በቀረበው ጥናት በመንገድ ግንባታ በኢንዱስትሪው ላይ የኢትዮጵያን የመንገድ ሀብት አስተዳደርና አያያዝን የተሳለጠ ለማድረግ ፣ በርካታ ወጪ ወጥቶባቸው የሚገነቡ መንገዶችና ድልድዮች በወጣባቸው ወጪ ልክ እንዲያገለግሉና ከመንገድ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ያሉ ሁኔታዎችን በማጥናት ለውጥ ለማምጣት ብሎም የተሻለ የፓሊሲ አቅጣጫዎችንና የተሻሉ የህግ ማዕቀፎችን ለማውጣት የሚያስችሉ ምክረ ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡ የቀረበዉን ጥናት በተመለከተ ተሳታፊ ከሆኑ አካላት ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች በጥናቱ አቅራቢዎች ምላሽ ተሰጥቶበታል። በአሁኑ ወቅት ኢመአ በተለይ የመሬት መንሸራትን በዘላቂነት ለመከላከል የመንገድ ምርምርን በቴክኖሎጂ በመደገፍ እና ችግሮቹ የሚከሰትባቸውን አካባቢዎች ለይቶ በማውጣት በዘርፉ መፍትሄ ለማምጣት የማያግዙ በርካታ ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ የመንገድ ዘርፉን ለማዘመን ጂ አይ ካ የሚያደርገውን የቴክኖሎጂና የግብአት ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et