es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 369 suscriptores, ocupando la posición 1 753 en la categoría Transporte y el puesto 2 530 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 369 suscriptores.

Según los últimos datos del 20 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 129, y en las últimas 24 horas de 8, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 38.47%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.24% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 143 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 037 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 21 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 369
Suscriptores
+824 horas
+697 días
+12930 días
Archivo de publicaciones
76 ኪ.ሜትር የሚረዝመው የሶዶ -ኦሞ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ ዋና ዋና ስራዎችን አጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ እየተሰራ ነው። አሁናዊ የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ ስራው ከአጠቃላይ ኪ.ሜትር ውስጥ 58 ኪ.ሜትር የሚሸፍን አስፓልት የማንጠፍ ስራው ተከናውኗል። ከመሬት በታች የሚሰሩ ስራዎችን አጠናቆ ቀሪ ኪሎሜትርን አስፓልት ለማልበስም እየተሰራ ነው። አካባቢው ላይ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን ከፍተኛ የመሬት መንሸራት እና ናዳ ለመከላከል በሚያስችል መልኩ ሰፋፊ የአቃፊ ግንብ እና የጋብዮን ስራዎች ተከናውነዋል። ሶዶ -ኦሞ ወንዝ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ያለ መንገድ ነው ። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሶዶ ከተማ 7 ኪ.ሜትር ላይ በመነሳት ኦሞ ወንዝ ላይ የሚያበቃ ሲሆን ግንባታው በሚጠናቀቅበት ወቅት ወደግልገል ጊቤ 3 የኤሌትሪክ ማመንጫ ግድብ በተፈለገው ፍጥነት ለመድረስ ያስችላል። የመንገድ ፕሮጀክቱ መገንባት በዋነኝነት የዞን ከተማ የሆኑትን ወላይታን እና ዳውሮ ዞኖችን በዘነናዊ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በማገናኘት ተጠቃሚ ያደርጋል። ከዚህ ቀደም ከሶዶ ተነስቶ የኦሞ ወንዝ ለመድርስ መንገዱ ምቹ ባለመሆኑና ከ2 ሰዓት በላይ ይፈጅ የነበረውን በተሽከርካሪ የሚደረገውን የትራንስፖርት ጉዞ በአማካኝ በግማሽ ይቀንሰዋል። በአሁን ሰዓት የመንገድ ፕሮጀክቱ የጎን ስፋት በወረዳ 21.5 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 1ዐ ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው። ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባንያ ግንባታውን እያከናወነው ሲሆን የማማከርና የቁጥር ሥራውን ደግሞ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ እያካሄደው ይገኛል። አንድ ቢሊየን ሶስት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊየን አራት መቶ አስራ ሁለት ሺህ ሃምሳ ብር ከ ሁለት ሳንቲም ወጪ እየተደረገለት የሚገኘውን ይኸው የመንገድ ፕሮጀክት የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። በተጨማሪም የዚሁ መንገድ ቀጣይ ክፋል የሆኑት የሶዶ- ተርጫ በግንባታ ሂደት ላይ ሲሆኑ በሚጠናቀቅበት ጊዜ የጨበራ ጩርጩራን ጥብቅ ደን እንዲሁም በገበታ ለሃገር ድጋፍ የሚሰራውን የኮይሻ ፕሮጀክት ጋር በማስተሳሰር ለሀገራችን የቱሪስት መስህብ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።

የኢተያ - ሮቤ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ማንጠፍ ስራ ተጀመረ፡፡ በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ 75 ነጥብ 6ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህው ፕሮጀክት የግንባታ ሂደቱ አሁን ላይ በጥሩ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል። ቀደም ብሎ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በተቋራጩ አቅም ማነስ ምክንያት በመጓተቱ የቅሬታ ምንጭ ሲሆን ቆይቷል። ኢመባ ተቋራጩ በገባው ውል መሰረት ግንባታውን እንዲያፋጥን በወሰደው አስተዳደራዊ እርምጃ የመንገድ ግንባታ እንቅስቃሴው እንዲነቃቃ አድርጓል። በአሁኑ ወቅትም ወደ አስፖልት የማንጠፍ ስራ የተሸጋገረ ሲሆን እስከ በጀት አመቱ መጨረሻ ድረስም 30 ኪ.ሜ የሚሸፍነውን የመንገዱን ክፍል አስፋልት ለማልበስ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው ፡፡ ከአስፋልት ንጣፍ ስራው ጎን ለጎን የአፈር ቆረጣና ሙሌት እንዲሁም የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ ስራም በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በቀጣይ የ8 አዳዲስ ድልድዮች ግንባታ ስራን ጨምሮ የስትራክቸርና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች በካተተ መልኩ ይሰራል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱን ግንባታ የሚያከናውነው የስራ ተቋራጭ ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 የተባለው አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው ፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ ሆኖ ለትራንስፖርት በእጅጉ አሰቸጋሪ የነበረ ነው ፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅም በአካባቢው የሚመረቱ ከፍተኛ የግብርና ምርት ውጤቶችንና የቁም እንስሳትን በቀጥታ ወደ ማእከላዊ ገበያ በፍጥነት በማድረስ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል። በመንገዱ ብልሽት ሳቢያ በተለይም በክረምት ወቅት የሚከሰተውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መስተጓጎል በማስቀረት ምቹ የትራንስፖርት ፍሰትን ይፈጥራል ፡፡ የኢተያ - ሮቤ የመንገድ ግንባታ ኘሮጀክት የስራውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየተሳተፈ የሚገኘው አገር በቀሉ ሃይ ዌይ ኢንጅነርስ ኤንድ ኮንሰልታንትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ድርጅት ነው ፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት በኢተያ ፣ በሁሩታ ፣ በዲክሲስ እና በሮቤ ከተሞች የመንገድ አካፋይ ታክሎበት በ21 ሜትር ስፋት የሚገነባ ይሆናል፡፡ መንገዱ በሚያልፍባቸው ቀበሌዎች ውስጥ በ12 ሜትር ስፋት እና በገጠራማው ክፍል ደግሞ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር ስፋት ይገነባል፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ስራ የሚውለውን 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በኢትዮጵያ መንግሥት የሚሸፈን ይሆናል፡፡

"ለአገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ" 👏👏👏
+2
"ለአገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ" 👏👏👏

"ለአገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ"

ጠ/ ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ የጅግጅጋ - ገለለሽ - ደገሀምዶ 109.82 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ ስራን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀመሩ። በሶማሌ ክልል ገለለሽ ከተማ ላይ በተካሄደው የመንገዶቹ ግንባታ ጅማሮ መርሀ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ጨምሮ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፉ ብናልፍ አንዱአለም የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ እንዲሁም የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ በመንገዱ ግንባታ ጅማሮ መርሀ ግብር ላይ እንደገለጹት የአካባቢው ህብረተሰብ ለረጅም አመታት የዘለቀ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ጥያቄ በመንግስት በኩል ተቀባይነት አግኝቶ 1.8 ቢሊዮን ብር በመመደብ በአስፋልት ደረጃ የሚገነባ መንገድ ነው ብለዋል። ዶ/ር አብይ አህመድ አክለውም አካባቢው ምንም አይነት መንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ በተለይም ክረምት ላይ ቀናትን ይፈጅ የነበረው መንገድ በቀጣይ በአስፋልት ደረጃ ሲገነባ ከሁለት ሰአት ባጠረ ጊዜ ውስጥ መጠቀም የሚያስችል እንደሆነ ገልጸዋል። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ በክልሉ ውስጥ ያሉና የመንገድ መሰረተ ልማት ባልተዳረሰባቸው እና ጸጋ ያላቸውን አካባቢዎች በመለየት በመንገድ የማስተሳሰሩ ስራ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለመንገድ ፕሮጀክቱ በስኬት መጠናቀቅ ክልሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ የግንባታ ስራው የተጀመረው የጅግጅጋ ገለለሽ ደገሀምዶ መንገድ ምንም አይነት የመንገድ መሰረተ ልማት የሌለው አካባቢ እና ማህበረሰቡም በአቅራቢያ ወዳሉ ጤና ተቋማትም ሆነ ምርቱን ለገበያ አውጥቶ በመሸጥ ተጠቃሚ እንዳይሆን በእጅጉ እንደሚቸገር አስታውሰው በቀጣይ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ዝርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል። ኢ/ር ሀብታሙ አያይዘውም መንገዱ በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቆ የሚጠበቅበትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ግልጋሎት መስጠት እንዲችል ከመንገድ ወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮች በፍጥነት መቅረፍ እንደሚያስፈልግ አንስተው የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት ትብብር እና ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል። ከ350 ኪ.ሜ በላይ ርዝማኔ ያላቸው የመንገድ ፕሮጀቶች በሱማሌ ክልል በግንባታ ሂደት ላይ ይግኛሉ 9 አዳዲስ መንገዶችም ወደ ግንባታ ለማስገባት በሂደት ላይ እንደሚገኝ ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በጅማሮ መርሀ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ተናግረዋል። የጅግጅጋ-ገለለሽ _ ደገሀምዶ ሎት ሁለት አስፋልት መንገድ 109.82 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። መንገዱን በብር 1,828,264,182.76 ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን የሚያከናውነው የስራ ተቋራጭ ቤአኤካ ጄኔራል ቢዝነስ የተባለው አገር በቀል ድርጅት ሲሆን ለግንባታ የሚያስፈልገው ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል ፡፡ ግንባታው ከ20 እስከ 32 ሜትር እርዝመት ያላቸው የ5 ድልድይ ስራንም ያካተተ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ በሶስት ዓመት ከስድስት ወራት ተጠናቆ ለህዝቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል። የጅግጅጋ ገለለሽ ደጋሃመዶ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጂጋ ከሚወስደው ዋና መንገድ ጋር ዘመናዊ በሆነ አስፋልት መንገድ ተደራሽ በማድረግና በአካባቢው ያሉትን አርብቶ አደር የማህበረሰብ ክፍሎሽ እንሰሳቱን በቀላሉ እና በተሻለ ዋጋ ወደ ማእከላዊ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ። ዛሬ የግንባታ ስራው የተጀመረው የጅግጅጋ ገለለች ደገሀምዶ እንዲሁም በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙት እና ቀጣይ ክፍል የሆኑት ከሰገግ እስከ ደነን የሚዘልቁት መንገድ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ከዚህ ቀደም ወደ ጎዴ ለመጓዝ በጅግጅጋ አድርጎ ደገሀቡር እና ደነን ከተሞችን አልፎ ጎዴ ይደረግ የነበረውን ጉዞ እነዚህ ፕሮጀክቶች የተሻለ አማራጭ ከመሆናቸውም ባለፈ 100 ኪ.ሜ በማሳጠር የትራንስፖርት ጊዜንና ወጪን የሚቀንስ ጠቀሜታው ከፍ ያለ መንገድ ነው። በተያያዘ ዜና በእለቱ ግንባታ ስራው የተጠናቀቀውን የጅግጅጋ-ገለለሽ 55.4 ኪ.ሜ ኮንትራት አንድ አስፋልት መንገድ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ተደርጓል። የአስፋልት መንገዱን በአንድ ቢሊዮን ብር የገነባው ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ድርጅት ሲሆን ዳና ኮንሰልቲንግ የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር ተሳትፏል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የጎዴ - ቀላፎ ሎት 1 ፣ የጎዴ-ሐርጌሌ ሎት-1እና ሰገግ ገርቦ -ደነን ሎት 3 /ሎት ሶስት /የመንገዶች ግንባታ ስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ። በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ በተካሄደው የመንገዶቹ ግንባታ ጅማሮ መርሃ ግብር ላይ የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ፣የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ፣የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ፣ የብልጽግና ፖርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱ አለም የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ ጨምሮ የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። በድምሩ 277.6 ኪ. ሜ እርዝማኔ ያላቸው እነዚህ ሶስት የመንገድ ፕሮጀክቶችን በአስፋልት ደረጃ መገንባት ከሀገርም አልፎ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ቀጠናዊ የንግድ እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከማሳደግ አንጻር ፋዳቸው የጎላ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ተናግረዋል። በተለይም የሀገራችን ከፍተኛ ወጪ ገቢ ንግድ የሚስተናገድበት ጅቡቲ ወደብ ሆነ በኮሪደሩ ላይ ይፈጠር የነበረውን የትራፊክ ጫና ከመቀነስ አኳያ ፕሮጀክቶቹ ሁነኛ አማራጭ ይሆናሉም ብለዋል ። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ለአመታት የዘለቀውን የክልሉን የመሰረተ ልማት ጥያቄ ለመመለስ መንግስ እየሰራ ያለውን ስራ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ፕሮጀክቶቹ ከክልሉም አልፍ የሃገሪቱን የወጪ ገቢ ንግድን በማቀላጠፍ የጎላ ሚና አላቸው ብለዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚደረግባቸው የጎዴ - ቀላፎ ፣ የጎዴ-ሐርጌሌ ሎት-1 እና የያአሌ-ደነን መንገዶች ግንባታ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እና የጥራት ደረጃ ለማጠናቀቅ ከመንገድ ወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ በመንገዶቹ ክልል ውስጥ ያሉ ንብረቶች በቶሎ ማንሳት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው። የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። ፕሮጀክቶቹ ካላቸው ኢኮኖሚያዊ እና መህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር የመንገድ ግንባታ ስራውን የሚያከናውኑት የስራ ተቋራጭ ድርጅቶች እና ጥራቱን የሚቆጣጠሩት አማካሪ ድርጅቶች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበው። የባለስልጣኑ መ/ቤትም አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። በዛሬው እለት የመንገድ ግንባታ ስራቸው በይፋ የተጀመሩት የጎዴ - ቀላፎ ፣ የጎዴ-ሐርጌሌ ሎት-1 መንገዶች በጠጠር መንገድ ደረጃ ያሉ ሲሆን ሎላኛውና የመንገድ ግንባታ ስራው በዛሬው እለት የተጀመረው የያአሌ - ደነን መንገድ ከዚህ ቀደም ምንም አይንት የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረው አካባቢ ሲሆን በቀጣይ ሁሉም መንገዶች ደረጃቻቸውን ከፍ በማድረግ በአስፋልት የሚገነቡ ይሆናል። የጎዴ ቀላፎ መንገድ ፕሮጀክት 94.8 ኪ ሜ እርዝማኔ አለው ፡፡ መንገዱን ለመገንባት ጨረታውን በብር አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን ብር (1 ,530,000 ,000.00 ) አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው ቻይና ሬል ዌይ ስቨን ግሩፕ ነው። የምህንድስና እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ እስታድያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ከጂ እና ዋይ አማካሪ ድርጅት ጋር በጋራ ያከናውኑታል ፡፡ የጎዴ - ሀርገሌ ሎት 1 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 100 ኪ .ሜ እርዝማኔ አለው ፡፡ ለአጠቃላይ ግንባታው መንግስት አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሀምሳ ዘጠኝ ሺ ሶስት መቶ ሰማኒያ ስድስት .ከሰባ አራት ሳንቲም 1,893,759,386.74 ወጪ መድቦለታል፡፡ መንገዱን ለመገንባት ጨረታውን አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አገር በቀሉ የሥራ ተቋራጭ ፋል ጀነራል ኮንትራክተር ነው፡፡ መንገዱ በውል ስምምነት መሰረት አራት ዓመት የግንባታ ግዜ ተሰጥቶታል፡፡ ሶስተኛው መንገድ ዮአሌ-ደናን ሎት 3 ሲሆን የፊቅ ሰገግ ገርቦ ደነን ፕሮጀክት አካል ነው፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ 82.84 ኪሜ ርዝመት አለው ። መንገዱን በአስፋልት ደረጃ የሚገነባው የሥራ ተቋራጭ አገር በቀሉ ክሮስ ላንድ ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ የኮንትራት ውሉ 1,119,417,453.44 አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን አራት መቶ አስራ ሰባት ሺ አራት መቶ ሀምሳ ሶስት ከ አርባ አራት ሳንቲም ብር ነው ፡፡ የመንገዱ ስራ በ3 ዓመት ከ6 ወር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል፡ ሳባ ኢንጂነሪንግ መንገዱን በማማከር እና በመቆጣጠር ተሳታፊ ይሆናል፡፡ የሶስቱ መንገድ ፕሮጀክቶች የጎን ስፋት በገጠራማው ክፍል 10 ሜትር ፣በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ 19 ሜትር እንዲሁም በዞን 21.5 ሜትር ነው ፡፡ መንገዶቹ ሲጠናቀቁ ሁለተናዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳዎችን የሚያጎናፅፉ ናቸው።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የጊምባ-ተንታ-ተንታ-መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ። በተንታ ወረዳ በአጅባር ከተማ በተካሄደው የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ብናልፍ አንዱአለም ፣የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና እና የክልል የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል። መንግስት በመደበው ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የጊምባ -ተንታ-ተንታ መገንጠያ 80.2 ኪ. ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የህዝቡን የአመታት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ። ለረዥም ዓመታት የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የዚህ አካባቢ ነዋሪ በከፍተኛ ሁኔታ ሲቸገር እንደቆየም ተናግረዋል። ይህ ታሪክ ሊሆን በመቃረቡ ለመላው ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁመልክታቸውንአስተላልፈዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አካባቢውን ፣ ከክልሉ፣ ክልሎችን ከሀገሪቱ የወጪ ገቢ ንግድ ጋር የሚያስተሳስሩ ሌሎች በርካታ ፕሮጀክቶችን ደረጃ በደረጃ እንዲተገበሩ መንግስት አቅጣጫ ማስቀመጡንም አብራርተዋል። ይህ ፕሮጀክትም ከተያዘለት ጊዜ በፊት እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የአመራር አካላት በብርታትና በጥንካሬ ከተቋራጮቹ ጋር በመሆን የሚያጋጥሙ የወሰን ማስከበር ችግሮችን ቀድመው እንዲፈቱም አሳስበዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው ፕሮጀክቱን በስኬት ለማጠናቀቅ ተገቢውን የድጋፍ፣ የክትትል እና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያደርግ ገልፀዋል። መላው የአካባቢው ነዋሪ ፣የሥራ ተቋራጩም ሆነ የአማካሪ ድርጅቱ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሀላፊነት በብቃት እንዲወጡም አስገንዝበዋል ። እንዲሁም ግንባታውን የሚያከናውነው የስራ ተቋራጭ የድርጅቱ ተወካይ በገቡት የኮንትራት ውሉ መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን ገንብቶ ለማስረክብ ቃል ገብተዋል። አጠቃላይ ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ደቡብ ወሎ ዞን ውስጥ ይገኛል። የጊምባ-ተንታ-ተንታ መገንጠያ የመንገድ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ 568 ኪ. ሜትር ይርቃል። የፕሮጀክቱ ስም ፦ ጊምባ-ተንታ-ተንታ መገንጠያ ርዝመት ፦     80.2 ኪ. ሜትር          የሥራ ተቋራጭ፡-             ጂያንግዢ ዘ ሰከንድ ኮንስትራክሽን የቻይና ስራ ተቋራጭ ነው። የግንባታው አይነት ፡-        DBB አማካሪ ድርጅት፡-    ሲቪል ወርክስ ኢንጂነርስ፣የኮሪያ ካምፓኒ ዮሺን ኮርፖሬሽን እንዲሁም ጂ እና ዋይ በጋራ በመተባበር      የግንባታ ወጪ፡-         2,185,228,256.12    የግንባታው ወጪ ሽፋን፡-   የኢትዮጵያ መንግስት የግንባታው ደረጃ ፦    አስፋልት ኮንክሪት     ለግንባታው የተሰጠው ጊዜ፡- 3 ዓመት መንገዱ የሚያቋርጥባቸው           ወረዳዎች ፦ ለጋምቦ፣ተንታ፣ደላንታ በርካታ ቀበሌዎች                     በመንገድ ፕሮጀክቱ ውስጥ የሚካተቱ ስራዎች የአፈር ቆረጣና ሙሌት ሥራ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ሥራ የሁለት ድልድዮች ስራ ትንንሽና መካከለኛ የተፋሰስ ስራዎች የመንገድ ዳር ትራፊክ ምልክቶች ግንባታ ሥራ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ሥራዎች የመንገድ ፕሮጀክቱ መገንባት ሁለንተናዊ ፋይዳ በጠጠር ደረጃ የነበረው የመንገዱ ግንባታ ተገንብቶ በሚጠናቀቅበት ወቅት ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ  ህብረተሰቡ ተሸከርካራዎችን ተጠቅሞ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ከዚህ ቀደም ከደሴ ተነስቶ ተንታ ለመድረስ በመንገዱ መበላሸት ሳቢያ ይደርስ የነበረውን የዙሪያ ጥምጥም መንገድ በአንድ ሰዓት ተኩል ይቀንሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ መገንባት ግንባታው ከሚካሄድበት አስራ አምስት ኪ. ሜትር ወደ ጎን ተገንጥሎ መቅደላ የሚገኘውን የአጼ ቴዎድሮስ ታሪካዊ የጀግንነት ሰፍራ እንዲሁም ለትግል ሲጠቀሙበት የነበረውን ሴባስቴፖል መድፍ ለመጎብኘት ለቱሪስት ምቹ ሁኔታን ከመፍጠርም አልፎ የቱሪዝም ፍሰቱን በመጨመር የውጭ ምንዛሬን ከማምጣት አኳያ ሃገራዊ ፋይዳው የጎላ ነው። የአካባቢው ነዋሪዎች  የሰብል ምርቶችን እንደ ጤፍ፣ገብስ፣ባቄላ እንዲሁም የቁም እንስሳት ውጤቶች ትራንስፖርትን ተጠቅመው  ወደ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ነዋሪው  ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ በመስመሩ የሚገኙ ዞኖች ወረዳዎች እና ቀበሌዎች በአስፋልት መንገድ በቅርበት ያስተሳስራል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የሀይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ። በወረባቦ ወረዳ በቢስቲማ ከተማ ላይ በተካሄደው የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ብናልፍ አንዱአለም ።፣የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና እና የክልል የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል። መንግስት በመደበው ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የሀይቅ- ቢስቲማ -ጭፍራ 74.3 ኪ. ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የህዝቡን የአመታት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ። ለረዥም ዓመታት የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የዚህ አካባቢ ነዋሪ በከፍተኛ ሁኔታ ሲቸገር እንደቆየም ተናግረዋል። ይህ ታሪክ ሊሆን በመቃረቡ ለመላው ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁመልክታቸውንአስተላልፈዋል። መንገድ መጀመር አንድ ትልቅ ምዕራፍ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተያዘለት ጊዜ በፊት እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የአመራር አካላት በብርታትና ጥንካሬ ከተቋራጮቹ ጋር በመሆን የሚያጋጥሙ የወሰን ማስከበር ችግሮችን ቀድመው እንዲፈቱም አሳስበዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ፕሮጀክቱ የህዝቦችን ጥያቄ ምላሽ የሰጠና ሀገራዊና ክልላዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ የበኩላቸውን ድጋፋና ክትትል እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው ተቋማቸው የሀይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ መንገድ ፕሮጀክትን በስኬት ለማጠናቀቅ ተገቢውን የድጋፍ፣ የክትትል እና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያደርግ ገልፀዋል። መላው የአካባቢው ነዋሪ ፣የሥራ ተቋራጩም ሆነ የአማካሪ ድርጅቱ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሀላፊነት በብቃት እንዲወጡም አስገንዝበዋል ። ። የመንገድ ግንባታውን ፓወርኮን ኃላ.የተ. የግል ማህበር እና አሰር ኮንስትራክሽን ኃላ.የተ. የግል ማህበር በሽርክና በመሆን የሚገነቡት ነው። የሀይቅ- ቢስቲማ -ጭፍራ ጠጠር መንገድ ለረጅም ጊዜ በአገልግሎ ሳቢያ በከፍተኛ ሁኔታ የተበላሸ ሲሆን መንገዱን ለመገንባት የሚወጣው ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል። አሁናዊው የመንገዱ ሁኔታ ከ 6 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋት ያለውና ጠባብ ሲሆን በእስፋልት ደረጃ ሲገነባ በወረዳ 19 ሜትር ፣ በቀበሌ 15ሜትር እንዲሁም በገጠር 1ዐ ሜትር ስፋት ይኖረዋል፡፡ የመንገዱ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት ከዚህ በፊት ከደሴም ይሁን ከሀይቅ ወደ ጭፍራ ለመሄድ በወልድያ በኩል በሚሌ-ጭፍራ ይደረግ የነበረውን የዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት በአቋራጭ በቀጥታ ከሀይቅ በቢትሰማ አድርጎ ጭፍራ ዘመናዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ስለሚያስችል የትራንስፖርት ጊዜን ከመቀነስ አኳያ ትልቅ ፋይዳ ያለው መንገድነው። እንዲሁም በመስመሩ የሚገኙትን ዞኖችና ወረዳዎች በቅርበት በማስተሳሰር ከዚህ ቀደም 74 ኪ.ሜትሩ ን በትራንስፖርት ለመጓዝ ይፈጅ የነበረውን አራት ሰዓት ከግማሽ በታች ያሳጥረዋል። ከዚህም ባለፈ የቁም እንስሳት ውጤቶች ፣ፍራፍሬና ሌሎችንም ምርቶችን ወደገብያ አውጥቶ በመሸጥ አምራቾችንና ሸማቾችን የጋራ ተጠቃሚ ያደርጋል። ፕሮጀክቱ የውል ስምምነት መሰረት በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ።

በባህርዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራ እየተፋጠነ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱን የስራ እንቅስቃሴ እና የባህርዳር ጢስ እሳት የመንገድ ግንባታ ስራን በዛሬው እለት በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኘ እና የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኝቷል። አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ 380 ሜትር ርዝመት እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ድልድይ ነው። በጉብኝቱ ወቅት ፕሮጀክቱ ላይ በዋነኛነት የድልድይ ተሸካሚ ምሰሶዎችን (piers) ለአርማታ ሙሌት ስራ ማመቻቸት እንዲሁም የድጋፍ ግንቡን ከመሬት በታች የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች (Abutment piles) ቁፋሮ እና አርማታ ሙሌት ስራ ነው እየተከናወነ የሚገኘው፡፡ ለድልድዩ ከሚያስፈልጉት 4 ቋሚ የድልድይ ተሸካሚ ምሶሶውች የመሰረት ስራቸው ከነ ማቀፊያው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል:: በተጨማሪም የአንዱ ድልድይ ተሸካሚ ምሶሶ የኮንክሪት ሙሌት ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ የቀሪዎቹ ሶስት ድልድይ ተሸካሚ ምሶሶ ሙሌት ስራም በመጪዎቹ ሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ከመሬት በታች የሚቀበሩት የክብ ቅርፅ ያላቸው የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች በዲዛይኑ መሰረት ከዝቅተኛው 14 ሜትር እስከ ከፍተኛው 23 ሜትር ድረስ ጥልቀት ያላቸው ሲሆኑ የአንዱ የቋሚ ተሸካሚ መሰረት የመሀል መለኪያ ስፋት በድልድዩ የድጋፍ ግንብ ጋር 1.5 ሜትር ሲሆን የመካከል ተሸካሚዎች ጋር ደግሞ 1.8 ሜትር ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራ ፕሮጀክት በእስካሁኑ አፈፃፀም በአጠቃላይ ድልድዩን ለመሸከም ከሚያስፈልጉ 88 የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች ውስጥ 54 የሚሆኑት የቁፋሮ እና የአርማታ ሙሌት ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቁ የቀሪዎቹን የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶችም በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የድልድዩ ስራ አሁናዊ የግንባታ ስራዎች አራት ቋሚ ተሸካሚ ምሶሶዎች የኮንክሪት ሙሌት እና የብርት ማሰር ስራዎች ተከናውነዋል። የድልድዩን ዋና ዋና ስራዎችን በእቅዱ መሰረት ለማከናወን አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ በመፍጠን ላይ መሆኑ በስራ ሃላፊዎቹ ተገምግሟል። የስራ ሃላፊዎቹ በቀጣይ የሚጠበቁ ጉልህ ስራዎችን ኮንትራክተሩ በገባው ውል መሰረት በጥራት እንዲሰራም ቀጣይ የስራ አቅጣጫን ሰተዋል። ድልድዩ በግራና በቀኝ በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን በተጨማሪም 5 ሜትር የእግረኛ መንገድ እንዲሁም የብስክሌት ተጠቃሚዎችን መስመር ባካተተ መልኩ ነው እየተገነባ የሚገኘው ፡፡ በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 1.4 ቢሊዮን ብር ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ የተባለው ተቋራጭ ነው። በባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እየተገነባ ያለው ይህ ዘመናዊ ድልድይ ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ጎን ለጎን ምቹ የሆነ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር በማድረግና መስመሩን ከአደጋ የፀዳ እንዲሆን ከማስቻሉ ባሻገር ከተማዋ ተጨማሪ ውበት እንድትላበስ ብሎም የሀገሪቱ ወጪና ገቢ ንግድ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋዕፆ ያበረክታል፡፡ በተያያዘ ዜናም የስራ ሃላፊዎቹ በዛሬው የመስክ ጉዞቸው የባህርዳር ጢስ እሳት መንገድ ፕሮጀክትን ቃኝተዋል ። ፕሮጀክቱ ወደ ጢስ አባይ ፏፏቴ ቱሪስት መዳረሻ የሚወስድ ሲሆን 22.3 ኪሎሜትር እርዝመት ያለው ነው። የዚህ መንገድ መገንባት የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ጎብኚዎች ከዚህ ቀደም ይፈጠርባቸው የነበረውን እንግልት በማስቀረት ለአካባቢውም ሆነ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭን ይፈጥራል፡፡ የመስክ ቅኝቱ በዋነኝነት የፕሮጀክቶቹን አፈጻጸም ለመገምገምና እና በግንባታ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ከወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮችን እየቀረፉ የግንባታ ስራቸውን ማፋጠን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሚመለከታቸው ጋር ለመምከር ነው።