es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 307 suscriptores, ocupando la posición 1 759 en la categoría Transporte y el puesto 2 546 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 307 suscriptores.

Según los últimos datos del 15 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 88, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 40.23%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.41% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 352 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 050 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 17.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 16 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 307
Suscriptores
+224 horas
+297 días
+8830 días
Archivo de publicaciones
መልካም በዓል
መልካም በዓል

የሆሳዕና - አረካ - ሶዶ መንገድ ጥገና በመጠናቀቅ ላይ ነው ሶዶ፣ ታኅሣሥ 28፣ 2018 (ኢ መ አ):- ከሆሳዕና - አረካ - ወላይታ ሶዶ ባለው ዋና መንገድ እየተካሄደ ያለው ጥገና በመጠናቀቅ ላይ ነው። የመንገድ ጥገናው 93 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ጥገናውን በራስ-ኅይል በማከናወን ላይ ይገኛል። የማማከርና ቁጥጥር ሥራውን ኢንስራድ ሲቪል ሲስተም ከሂትኮን ኢንጅነሪነግ ጋር በትብብር ያከናውናሉ። ጥገናው ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 588 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው እየተከናወነ የሚገኘው። ይህ ባለ-ድርብ የአስፋልት ወለል ንጣፍ (DBST) መንገድ ከ2000 ዓ. ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲኾን፤ በአገልግሎት እና በዕድሜ ምክንያት በመጎዳቱ ነው ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው። መንገዱ እንደ ጉዳት ዓይነቱ እና መጠኑ በወቅታዊ እና የመደበኛ ጥገና ዓይነቶች እንዲጠገን ተደርጓል። እየተከናወኑ ከሚገኙ ሥራዎች መካከልም የተጎዳውን የመንገዱን ክፍል በማንሳት በምርጥ አፈር እና ጠጠር የመተካት እንዲሁም አስፋልት የማልበስ ሥራዎች ይገኙበታል። የምርጥ አፈር እና የድንጋይ ጠጠር በቅርብ ርቀት አለመገኘት እንዲሁም አካባቢው ላይ የነበረው የተራዘመ ዝናብ ሥራውን ፈታኝ አድርጎት የቆየ ቢኾንም በተደረገው ከፍተኛ ጥረት አሁን ላይ የጥገናውን ዋና ዋና ሥራዎች ማጠናቀቅ ተችሏል። ቀሪ ከመንገድ ዳር ምልክት ተከላ፣ የመንገድ ምልክቶች የማቅለም እና ሌሎች ከመንገድ ጥንቃቄ ጋር የተያያዙ ውስን ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ይገኛል። የመንገዱ መጠገን ከዚህ በፊት ከሆሳዕና - ወላይታ ሶዶ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን ከ3 ሰዓት በላይ አድካሚ የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል። ምቹ እና ቀልጣፋ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር ከማስቻሉም ባሻገር የትራፊክ አደጋ እንዲሁም ለመለዋወጫ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን መቀነስ አስችሏል። በቀጣይም መንገዱን በዘላቂነት መልሶ ለመገንባት የዲዛይን ሥራው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ በአሁኑ ወቅት በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል። ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም ተቋማችን በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ሦስት ዞኖችን የሚያስተሳስረው የሞርካ - ጊርጫ - ጨንቻ መንገድ ግንባታ በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አርባምንጭ፣ ታኅሣሥ 25፣ 2018 (ኢ መ አ):- የጋሞ፣ ጎፋ እና ወላይታ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የሞርካ - ጊርጫ - ጨንቻ መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎችን በዚህ ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ 72 ነጥብ 666 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፤ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 82 በመቶው ተጠናቅቋል። እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከል የ63 ኪ.ሜ ሰብቤዝ፣ የ59 ኪ.ሜ ቤዝኮርስ፣ የ59 ኪ. ሜ የአስፋልት ንጣፍ ሥራዎች ይገኙበታል። የ2 ድልድዮች ግንባታ ሥራም ተጠናቅቋል። ከዚህም ባለፈ በተካሄደው ከፍተኛ የቆረጣ ሥራ ለዘመናት በመንገድ መሠረተ-ልማት እጦት ተራርቀው የነበሩትን የዲታ እና ደረማሎ ወረዳዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በመንገድ ትራንስፖርት ማገናኘት ተችሏል። የፕሮጀክቱን ቀሪ ዋና ዋና ሥራዎች በዚህ ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ፥ በግብዓት እና በማሽነሪ አቅርቦት ረገድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ዓለም-አቀፉ ቤጂንግ ኧርባን ግሩፕ ግንባታውን ያከናውናል። ሀገር - በቀሉ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ግንባታውን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥር ይሠራል። ለመንገድ ግንባታው 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግሥት በጀት ተይዞለታል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሞርካ፣ ዋጫ፣ ወይዛ፣ ጨንቻ እና መሰል ከተሞችን ማኅበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ትስስር ያጠናክራል። ባሕላዊውን የዶርዜ መንደር ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል። በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የተለያዩ የፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ የድንች፣ ገብስ እና ባቄላ ምርቶች ለማዕከላዊ ገበያ በቀላሉ እና በፍጥነት ለማድረስ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የነቀምቴ - አንገር ጉቲን -አንዶዴ ሎት 1 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 36 ነጥብ 34 በመቶ ደረሰ ነቀምቴ ፣ታህሣሥ 24 2018 (ኢ መ አ) ፡ ኦሮሚያ ክልልን ከአማራ ክልል ጋር የሚያገናኘው የነቀምቴ-አንገር ጉቲን -አንዶዴ ሎት 1 የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 36 ነጥብ 34 በመቶ ደርሷል፡፡ 86 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን መንገድ በመገንባት ላይ የሚገኘው የቻይናው ቾንግቺንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲሆን ፤ የማማከርና ቁጥጥር ሥራውን ደግሞ ረናርደት ከዩናይትድ አማካሪ መሀንዲሶች ጋር በትብብር እያከናወነ ይገኛል። በፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም የቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ፣ የስትራክቸር ፣ የሰብቤዝ ንጣፍ ፣ የአስፓልት ጠጠር መፍጨት እና የቤዝኮርስ ንጣፍ ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን ከአጠቃላይ የፕሮጀክቱ ርዝማኔ 33 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተካሂዷል። ለመንገዱ ግንባታ ጥቅም ላይ የሚውለው 1,948,446,483 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ ስድስት ሺህ አራት መቶ ሰማንያ ሶስት ) ብር ወጪ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚሸፈን ነው። መንገዱ በወረዳ 21.5 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል ። ፕሮጀክቱ ቀድሞ ከነበረው የጠጠር መንገድ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጎ አገልግሎት መስጠት ሲጀመር ምስራቅ ወለጋ ዞንን ከጉቶጊዳ ፣ ሳሲጋ ፣ ጊዳ አያና ፣ ወረዳዎች እንዲሁም የሰባት ቀበሌዎችን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በይበልጥ ያጠናክራል ። ከዚህ በፊት ይወስድ ነየበረውን የቀናት ጉዞን ወደ አርባ አምስት ደቂቃ ያሳጥራል። በተጨማሪም የዚህ መንገድ ሁለተኛ ክፍል የሆነው አንዶዴ-አጋምሳ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ዘጠና ስምንት ነጥብ አምስት በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ሶስተኛው ሎት አጋምሳ-ቡሬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመሰራት ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ኦሮሚያን ከአማራ ክልል ጋር በአቋራጭ በማገናኘት የክልሎቹን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በአካባቢው የቡና፣ የበቆሎ እና የለውዝ ምርት በስፋት የሚገኝ ሲሆን ፤ እነዚህን ምርቶች በአፋጣኝ ለገበያ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ድርሻ ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የእንጦጦ ፍተሻ - ሱሉልታ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ለማፋጠን እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ታህሳስ 21፣2018(ኢመአ) የሀገሪቱን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ ያለውን የእንጦጦ ፍተሻ - ሱሉልታ (20.3) ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ለማፋጠን ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ቀደም ሲል መንገዱ የከተማ ክፍሎችን ሳይጨምር የነበረው 10 ሜትር ስፋት ለከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት የነበረ ሲሆን ፤ ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት መንገዱ ወደ 50 ሜትር ስፋት እንዲያድግ ተደርጓል። ይህም በሁለቱም አቅጣጫዎች 28 ሜትር ከሚሸፍን የመኪና መተላለፊያ በተጨማሪ የሳይክልና የእግረኛ መሄጃዎችን ፣ የመንገዱን ጥራትና ዕድሜ የሚያራዝም ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ሥርዓት እንዲሁም የአካባቢውን ውበትና የአየር ንብረት የሚጠብቁ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን ያካተተ ነው። ግንባታው በዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ፤ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የማማከርና ቁጥጥር ሥራውን እየሰራው ይገኛል፡፡ በአሁናዊ የፕሮጀክቱ የሥራ ሂደት ላይም የአፈር ጠረጋ ፣ የቆረጣ ፣ የድልዳሎ እና የድጋፍ ግንብ ግንባታ ሥራዎች የትራፊክ ፍሰቱን በማያውክ ሁኔታ እየተከናወኑ ናቸው፡፡ የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በመስመሩ ላይ የሚታየውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ በመቅረፍ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚደረገውን ጉዞ በእጅጉ ያቀላጥፋል። ከዚህም በተጨማሪ ከሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚገቡ የግብርና ምርቶችንና የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን ወደ መሃል ሀገር ለማጓጓዝ የሚያስችል ይሆናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኮልፌ 18 ማዞሪያ - አሸዋ ሜዳ ኬላ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው አዲስ አባባ፣ ታህሳስ 16፣ 2018 (ኢመአ) አዲስ አበባን  ከተለያዩ  የክልል ከተሞች ጋር ከሚያገናኙ  ዋና ዋና  መንገዶች  መካከል   አንዱ  የሆነው  የኮልፌ 18 ማዞሪያ - አሸዋ ሜዳ ኬላ  14.73  ኪሎሜትር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  እየተከናወነ  ይገኛል። ከዚህ  ቀደም  መንገዱ  11 ሜትር  ስፋት የነበረው ሲሆን አሁን ላይ የመኪና ፣የሳይክል ፣የእግረኛ መሄጃ ፣የመንገድ አካፋይ ፣የፍሳሽ ማስወገጃ ስራዎች እና የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን አካቶ 50 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው። ይህም በመስመሩ ያለውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅን ለማስቀረት ከፍተኛ ድርሻ አለው። ግንባታውን  በማከናወን ላይ  የሚገኙት  የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  የአለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እና  ብሪጅ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በጋራ በመሆን ነው። የማማከርና  የቁጥጥር ሥራውን  የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን እየሰራው ይገኛል። በእስካሁኑ  የፕሮጀክቱ  የሥራ  እንቅስቃሴ የፍሳሽ መውረጃ ትቦ ቀበራ ፣ የድጋፍ ግንብ ስራዎች ፣ የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት ፣ የሰቤዝ ፣ የቤዝኮርስ  እና  የአስፋልት ንጣፍ  ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው ። የፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ  የመንገዱ ተጠቃሚዎች ቀልጣፍ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። በተጨማሪም  ከምእራቡ  የሃገራችን ክፍል ወደ አዲስ አበባ እና ወደ ተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የተለያያዩ  የግብርና ምርቶች እና የኢንደስትሪ ግብአቶችን ለማጓጓዝ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይታመናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

🇷🇺 ከዛሬ ጀምሮ ይህ ተቻለ። የሩሲያን ከውስጥ የሚያሳይ ቻናላችን አሁን በአማርኛ ተጀምሯል። 🇷🇺🤝🇪🇹ሩሲያና ኢትዮጵያ በዘመናት የተሸለመ ክብርና ወዳጅነት ታሪክ አላቸው። የሩሲያ ጉዳዮችን በአማርኛ የሚያቀርብ ቻናል ከዛሬ ጀምሮ ተጀምሯል። መረጃው በቀጥታ እንዲደርስ ነው። 📍"በሩሲያ በፍቅር የተቀረ" የሚባል ቻናል ስለ አገራችን ያለውን ነገር ይነግራል. — ከሞስኮና ከክልሎች የሚመጡ ዜናዎችና ቪዲዮዎች — የሰዎች ዕለታዊ ሕይወት፤ ከተሞችና ክልሎች — ፖለቲካና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች — ባህል፤ ማህበረሰብና ዘመናዊ ሩሲያ ❤️ ይቀላቀሉ፤ ስለ ሩሲያ ያውቁ - https://t.me/+qT6tcupdy0AyNjNi

አዳማ-መልካ ጂሎ ( አዳማ - ኪሎ ሜትር 60 ) የፍጥነት መንገድ አፈፃፀም 47 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2018 (ኢመአ) የአዲስ አበባ - አዳማ - አዋሽ - ድሬድዋ - ጂቡቲ የፍጥነት የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የአዳማ - አዋሽ ምዕራፍ አንድ ( አዳማ - ኪሎ ሜትር 60 ) የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀም 47 በመቶ ደረሰ ፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ጥቅም ላይ የሚውለው 6,688,456,565 (ስድስት ቢሊየን ስድስት መቶ ሰማኒያ ስምንት ሚሊየን አራት መቶ ሃምሳ ስድስት ሺ አምስት መቶ ስልሳ አምስት ብር የግንባታ ወጪ በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢፌዴሪ መንግስት የተሸፈነ ነው ፡፡ 61.55 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚያከናውነው JMC Projects (India) Ltd የስራ ተቋራጭ ከLongjian Road and Bridge Co. Ltd. በጋራ በመሆን ሲሆን ፤ LEA Associate South Asia Pvt. Ltd በንዑስ ተቋራጭነት ከUnited Consulting Engineers P.L.C በጋራ በመሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማካሄድ ላይ ይገኛሉ ፡፡ በእስካሁኑ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ፣ ብዛት ያላቸው የመኪና እና የእግረኛ መሸጋገሪያ ድልድዮች ፣ ልዩ ልዩ የስትራክቸር እንዲሁም 37 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት ንጣፍ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ ኮሪደሩ የኢትዮጵያ የገቢ እና ወጪ ንግድ /Imprort-Export/ ዋና አውታር በመሆኑ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የአገራችን የወጪ እና ገቢ ንግድ ይበልጥ ያቀላጥፋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከጎረቤት ሃገር ጅቡቲ ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መስተጋብር /Cross boarder integration with Djibouti/ ያጠናክራል፡፡ በተጨማሪም መንገዱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ለመጓጓዝ ይወስድ የነበረውን የ1 ሰዓት ጉዞ በግማሽ ያሳጥረዋል ተብሎ ይታመናል። የዚሁ መንገድ ቀጣይ አካል የሆነው የመልካጅሎ-አዋሽ 67 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችለውን የፋይናንስ ምንጭ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ለማግኘት ተችሏል ፡፡ በተጨማሪም የመኢሶ-ድሬደዋ 144 ነጥብ 5 ኪሎሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ደግሞ በዚሁ በጀት ዓመት በይፋ መጀመሩ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመንገድ እና ትራንስፖርት ፖሊሲ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 07፣ 2018 (ኢ መ አ):- የመንገድ እና የትራንስፖርት ዘርፍ የሚመራበት ፖሊሲ ረቂቅ ሰነድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ግብዓት የማሰባሰቢያ ውይይት ተካሂዳል። በውይይቱ ላይ የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክ ሚንስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢንጅነር) እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኅላፊዎችን ጨምሮ፣ የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪ ማሀንዲሶች እንዲሁም ልዩ ልዩ ማኅበራት ተሳትፈዋል። የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ፤ ከዚህ ቀደም የመንገድ ዘርፉ የሚመራበት ፖሊሲ አለመኖሩ እንዲሁም ተግባር ላይ ያለው የትራንስፖርት ዘርፍ ፖሊሲውን በየጊዜው እየጨመረ ከመጣው የሕዝብ ቁጥር፣ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ዕድገት ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ ረቂቅ ሰነዱ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ፖሊሲው በፍላጎት እና አቅርቦት መካከል የሚስተዋለውን ክፍተት ለመድፈን የሚያስችልም ነው ብለዋል። ረቂቅ ሰነዱ በመድረኩ ላይ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል። የፖሊሲው ርዕይ "በ2030 ዓ.ም ፍትሀዊ አስተማማኝ፣ የተቀናጀ ዘመናዊ እና ደኅንነቱ የተረጋገጠ የመንገድ መሠረተ-ልማት እና የትራንስፖርት አገልግሎት ለሁሉም ኅብረተሰብ ተደራሽ ኾኖ ማየት" መኾኑን ተገልጿል። ስምንት አንኳር ጉዳዩች እና የትኩረት አቅጣጫዎችን ማካተቱ የተገለጸው የፖሊሲው ረቂቅ ሰነድ፤ የመንገድ ዘርፍን በተመለከተ፤ የመንገድ መሰረተ ልማት አቅርቦት ማስፋፋት፣ የመንገድ ፕሮጀክቶች ሥራ አመራር ማጠንከር፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻል እና የመንገድ ደኅንነትን ማሻሻል የፖሊሲው ቁልፍ የትኩረት መስክ መኾኑ ተመላክቷል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የሴክተር ግንባታ ከማጠናከር ባሻገር የዘርፉን መሠረታዊ እና ውስብስብ ችግሮች በመቅረፍ ረገድ ፖሊሲው መዘጋጀቱ ተገቢ ነው ብለዋል። በየቦታው የተዘረጉ የቁጥጥር ኬላዎች፣ የመንገድ ዲዛይኖች የእግረኞች ፍላጎት፣ ባሕሪ እና ደኅንነት ጉዳዮች እና ሌሎች ጉዳዮች በፖሊሲው ላይ እንዲካተቱ ጠይቀዋል። በተለያዩ መንገዶች ግብዓት የማሰባሰብ ሥራው በቀጣይ ጊዜያትም የሚቀጥል መኾኑን በመድረኩ ላይ ተመላክቷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et