es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 381 suscriptores, ocupando la posición 1 753 en la categoría Transporte y el puesto 2 533 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 381 suscriptores.

Según los últimos datos del 22 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 128, y en las últimas 24 horas de 5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 39.03%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.24% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 221 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 039 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 23 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 381
Suscriptores
+524 horas
+737 días
+12830 días
Archivo de publicaciones
የተቋማችን የመንገድ ምርምር ማዕከል ከጃፓን ድርጅት/ JICA/ ጋር በመተባበር አውደ ጥናት አካሄደ አዲስ አበባ፣ ህዳር 27/2017 ዓ.ም (ኢመአ) ፦ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል ከጃፓኑ አለም አቀፍ የልማት ድርጅት /JICA/ ጋር “Establishing competence in Geotechnics and landslides management towards mitigating landslide hazards in road infrastructures” በሚል አርዕስት አውደ ጥናት አካሄደ። JICA ለኢትዮጵያ የመንገድ ዘርፍ ልማት በተለያየ መልኩ አስተዋጽዖ ከሚያደርጉ የልማት አጋሮች መካከል አንዱ ነው። የአውደ ጥናቱ ዋና አላማ በመሬት መንሸራተት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን አስመልክቶ ለመወያየት የሚያስችል መድረኮችን መፍጠር ነው። በመረሃ ግብሩ ላይ በቁጥር ስድስት የሚሆኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበዋል ። እነዚህ ጥናታዊ ጽሁፎች በፌደራል መንገድ መሰረተ ልማት ላይ በየጊዜው እያጋጠሙ ላሉ የመሬት መንሸራተት መንስኤዎች ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በመድረኩ ላይ የቀረበዉን ጥናት በተመለከተ ተሳታፊ ከሆኑ ባለድርሻ አካላት ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች በጥናቱ አቅራቢዎች ምላሽ ተሰጥቶበታል። ከዚህም በተጨማሪ በዘርፉ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የመሬት መንሸራተትን ለመቀነስ የሚያስችሉ እርምጃዎች እና የወደፊት ተግባራትን አስመልክቶ በቡድን በመከፋፈል ተወያይተዋል፡፡ የኢመአ የጂኦቴክንክ እና የመሬት መንሸራተት ጥናት ቡድን ከJICA ጋር በመተባበር የመሬት መንሸራተት መቆጣጠሪያ መመሪያዎችን አስመልክቶ በዘርፉ ላሉ ባለሙያዎች እያደረገ ያለው የአቅም ግንባታ እና ልምድ ልውውጥ ስራ አመርቂ ውጤቶችን አሳይቷል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከተለያዩ ዩንቨርስቲ የተውጣጡ ባለሙያዎች ፣ አማካሪ ድርጅቶች እና በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።

የሻሸመኔ - ሐዋሳ አስፋልት መንገድ ወቅታዊ ጥገና በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። ሐዋሳ፣ ኅዳር 25፣ 2017 (ኢ መ አ):- ከሻሸመኔ እስከ ሐዋሳ ባለው ዋና መሥመር እየተከናወነ የሚገኘው ወቅታዊ የአስፋልት መንገድ ጥገና በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። መንገዱ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ባለመኾኑ ነው ጥገናው ያስፈለገው። የመንገድ ጥገናው 13 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፥ በከባድ ጥገና ደረጃ እድሳት እየተደረገለት ይገኛል። አሁን ላይ 10 ኪሎ ሜትር የሚኾነውን የመንገድ ክፍል ሙሉ በሙሉ በማንሳት አስፋልት የመደረብ እና የመንገድ ትከሻ ሥራዎች ተሠርተዋል። ይህም በመኾኑ አሸከርካሪዎችን እንዲሁም  ኅብረተሰቡን ለእንግለትና ለትራንስፖርት መጉላላት ይዳርጉ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ  ተችሏል።  የመንገድ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንግዶች አስተዳደር የሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል እያከናወነ ይገኛል። ለጥገናው 122 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል። የመንገድ ጥገናው አደጋን ከመቀነስ እና ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር፣ በርካታ ሀገራትን የሚያስተሳስረው ግዙፉ የትራንስ አፍሪካን ሀይዌይ ፕሮጀክት አካል በመኾኑ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው። ይህ በእንዲህ እንዳለ የመስመሩን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ይበልጥ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ማስተናገድ የሚያስችል የሞጆ - ሐዋሳ ፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት አካል የኾነው ባቱ - አርሲ ነገሌ - ሐዋሳ መንገድ ግንባታ ላይ መኾኑ ይታወቃል። ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጠሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ተቋማችን ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በጎዴ - ቀላፎ - ፈረፈር ምዕራፍ አንድ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ስራ በመካሄድ ላይ ነው አዲስ አበባ፣ ኅዳር 20፣ 2017 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል ሸበሌ ዞን የጎዴ - ቀላፎ - ፈረፈር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ የአስፋልት ንጣፍ ስራ እየተካሄደ ነው። በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ የሚገኘው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ 97 ነጥብ 06 ኪሎሜትር ርዝመትን ይሸፍናል። በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ37 ነጥብ 63 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ተከናውኗል። በተጨማሪም የቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ጠጠር የማምረት ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የአነስተኛ የውኃ መተላለፊያ ቱቦዎች ፣ ከልቨርቶች እንዲሁም የድልድይ ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ አሁናዊ አጠቃላይ አፈጻጸም 66 ነጥብ 66 በመቶ ወይም 64 ነጥብ 51 ኪሎሜትር ደርሷል። ግንባታውን በተቀመጠለት ጊዜ ለማጠናቀቅም በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ተቋማችን በግንባታ ሂደት ወቅት የሚገጥሙ ውስንነቶችን በመለየት መፍትሄ ለመስጠት አስፋላጊውን ድጋፍ እና ክትትል እያደረገ ይገኛል። ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው ዓለም-አቀፉ ቻይና ሬይል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ነው። የፕሮጀክቱን የምህንድስና ማማከር እና የመቆጣጠር ስራ ደግሞ ስታድያ የምህንድስና ሥራዎች አማካሪ ከንዑስ አማካሪ ጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ጋር በጣምራ በማከናወን ላይ ይገኛሉ። ለግንባታው የሚውለው 1,530,000,000.00 (አንድ ቢልዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን) ብር ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። መንገዱ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የክልሉን የመንገድ መሠረተ ልማት አውታር ከማስፋቱም ባሻገር በመስመሩ የሚገኙትን የጎዴ እና ቀላፎ ወረዳዎች ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ይበልጥ ያሳልጣል። ከዚህም ባሻገር በመንገድ ክልል ውስጥ የሚገኙ አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ አጋጣሚን ይፈጥራል። በተጨማሪም የሸበሌን ወንዝ ተከትለው የሚመረቱትን የግብርና ምርቶች በጥራትና ፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የአርሶ አደሩን ይበልጥ ተጥቃሚነት ያረጋግጣል። እንዲሁም በፍየል ፣ ግመል እንዲሁም በመሰል የቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦች ምቹ የገበያ ትስስርን እንደሚፈጥር ይታመናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Workshop on Landslide Distribution - Addis Ababa University - Addis Ababa Science and Technology University - Adama Science and Technology University - Arbaminch University - Bahir Dar University - Jimma University - Mekele University - Ethiopian Association of Civil Engineers (EACE) - Ethiopian Consulting Engineers and Architects Association (ECEAA) - Ethiopian Disaster Risk Management Commission (EDRMC) - Ethiopian Geological Institute (GIE) - Ethiopian Geotechnical Society (EGS) - AEC Consulting Engineers Plc - AIC Progetti S.P.A. - ALERT Engineering Plc - Beza Engineers Kenya Limited (Kenya) - Best Consulting Engineer Plc - Civil Works Consulting Engineers Plc (CWCE) - Consulting Engineers Group Ltd - CORE Consulting Engineers Plc - CRTE Consultancy - Ethiopian Engineering Corporation (EEC) - G & Y Engineering Consulting Plc - Gondwana Engineering Plc - Hong-IK Engineering and Consultants Co. Ltd. - IMS Engineering Inc. - LEA Associates South Asia Pvt Ltd - Net Consulting Engineers Plc - Omega Consulting Engineers Plc - Prominent Engineering Solution Plc - Pure Consulting Engineers Plc - STADIA Engineering - YLS Engineering Plc.

call for abstract
call for abstract

የመካነ ኢየሱስ/እስቴ - ስማዳ መንገድ ግንባታ በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ ኅዳር 10፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን'ን ከደቡብ ወሎ ዞን ጋር የሚያገናኘው የመካነ ኢየሱስ/እስቴ - ስማዳ መንገድ ግንባታ በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። 50 ነጥብ 4 ኪሎሜትር የሚሸፍነው የመንገድ ፕሮጀክቱ፣ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ የ47 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተሠርቷል። በቀሪው የፕሮጀክቱ ክፍል ማለትም ወገዳ ከተማ ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውኃ ማፋሰሻ፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ። በተጨማሪም የአምስት ድልድዮች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። የመንገድ ግንባታው አጠቃላይ አፈጻጸም አሁን ላይ 90 ነጥብ 9 በመቶ የደረሰ ሲኾን፣ ቀሪ ሥራዎችን በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል። በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር ለፕሮጀክቱ መቋረጥ ምክንያት የነበረ ቢኾንም፤ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከየአካባቢው የመስተዳድር አካላት ጋር ባደረገው ጥረት ግንባታውን  ወደ ተሻለ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ማድረስ ተችሏል። ግንባታውን ዓለም አቀፉ 'ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ' እያከናወነ ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው 1,925,451, 264.41 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ አምስት ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ) ብር በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው። 'ፕሮሚናንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽንስ' ግንባታውን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ እየሠራ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ከእስቴ ወደ ስማዳ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ በግማሽ ያሳጥረዋል። በሥፍራው የሚገኙትን ትንንሽ መንደሮች ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማገናኘት ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን በማሳለጥም የተለያዩ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮችን ያጠናክራል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ሽንብራ፣ ኑግ፣ ባቄላ፣ ጓያ፣ ድንች እና መሰል የግብርና ምርቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በፍጥነት እና በጥራት ማድረስ ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መንግስት መንገድ ለማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ እና ለሀገር ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ በመገንዘብ፣ ለመንገድ መሠረተ-ልማት ዝርጋታ በየጊዜው ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ፈሰስ ያደርጋል፡፡ ከፍተኛ የሀገር ሀብት የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል፡፡ መንገዶችን ለብልሽት ከሚዳርጉ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛው ከተፈቀደው ክብደት በላይ በመጫን መጓዝ ነው። በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በመላው ሀገሪቱ ባቋቋማቸው 14 የክብደት እና መጠን መቆጣጠሪያ ጣቢያዎቹ በኩል ቁጥጥር ያደርጋል፡፡ የተሽከርካሪዎችን ክብደት የመቆጣጠር ዋና ዓላማ በመንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸዉ የአክስል ክብደት መጠን በላይ ጭነት ጭነዉ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የመንገድ አውታሮች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል እንዲሁም መንገዶች እና ድልድዮች ዲዛይን ለተደረጉበት የአገልግሎት ጊዜ በጥሩ ሁኔታ ላይ ሆነው አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረግ ነዉ፡፡ ከዚህም አኳያ ተቋሙ የተሽከርካሪ ክብደትና መጠንን ለመወሰንና ለመቆጣጠር በወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 491/2014 አንቀጽ 20 ንዑስ አንቀጽ 6 መሰረት “በዚህ ድንብ ላይ የተሽከርካሪ ክብደትን በመተላለፍ ለተቀመጡት ቅጣቶች የሚከፈል ክፍያ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሚከፈል ሲሆን የተሽከርካሪ መጠንን በመተላለፍ ለተቀመጡ ቅጣቶች የሚከፈል ክፍያ ለሚኒስቴሩ ይከፈላል” በሚል በግልፅ እንደተመለከተው ትርፍ የጫነ ተሽከርካሪ ለጫነው ትርፍ ጭነት ቅጣት ተቀጥቶ፣ ቅጣቱን ኢ.መ.አ. ለዚሁ አገልገሎት በከፈተው ሂሳብ ቁጥር ገቢ የሚደረግ ሲሆን፣ ትርፍ የጫነ ተሽከርካሪ ጉዞውን መቀጠል የሚችለው ጭነቱን ካስተካከለ በኋላ ብቻ ነው። በደንቡ አንቀጽ 3 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት “ይህ ደንብ በማናቸውም የኢትዮጵያን መንገድ በሚጠቀሙ ጠቅላላ ክብደታቸዉ ከ3,500 ኪሎ ግራም በላይ በሆኑ ተሽከርካሪዎች፣ የተጣመሩ ተሽከርካሪዎች እና ተሳቢዎች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል” በሚል የደንቡን ተፈፃሚነት ወሰን አስቀምጧል:: በደንቡ አንቀጽ 9 መሰረት ለእያንዳንዱ አክስል የተፈቀደ ከፍተኛ ክብደት የሚከተለው ነው፡- I. የነጠላ አክስል (Axle) ሁለት ወይም ሶስት ጎማዎች የተገጠሙለት ተሽከርካሪ የፊት እና የኋላ የአክስል (Axle) ክፍሎች ጠቅላላ የክብደት መጠን የሚከተለዉ ነዉ፡- ሀ) የፊት አክስል (የመሪ አክስል) Steering Axle የክብደት መጠን ከ7.7 ቶን (77 ኩንታል) መብለጥ እንደሌለበት፤ ለ) ከመሪዉ አክስል (Steering Axle) ዉጪ ሆኖ ነጠላ ጎማ የተገጠመለት ተሸከርካሪ ከሆነ ጠቅላላ ክብደቱ ከ8 ቶን (80 ኩንታል) መብለጥ እንደሌለበት፤ ሐ) የኋላዉ የአክስል ክፍል አራት ጎማዎች የተገጠሙለት ከሆነ የአክስል ክብደቱ ከ10 ቶን (100 ኩንታል) መብለጥ እንደሌለበት፡፡ II. የተሸከርካሪዉ የአክስል ክፍል ባለ ሁለት (Tandem Axle Unit) ወይም ባለሶስት (Tri-dem axle) ሲሆን፣ ለተሽከርካሪዉ የማይፈቀድ የአክስል (Axle) ክብደት መጠን እንደሚከተለዉ ነዉ፡- ሀ) ስምንት ጎማዎች ለተገጠሙለት የጥንድ አክስል (Tandem Axle) ጠቅላላ የአክስል ክብደቱ በአንድ ላይ ተደምሮ ከ18 ቶን (180 ኩንታል) መብለጥ እንደሌለበት በሕጉ ላይ ተቀምጧል፡፡ ለ) እያንዳንዳቸው አክስሎች ላይ አራት ጎማ የተገጠመላቸው ባለ ሶስት አክስል ክፍል (Tri-dem axle) ጠቅላላ የአክስል ክብደቱ በአንድ ላይ ተደምሮ ከ24 ቶን (240 ኩንታል) መብለጥ እንደሌለበት በሕጉ ላይ ተቀምጧል፡፡ በደንቡ መሰረት በሚደረግ የአክስል ክብደት ቁጥጥር ላይ በሚታዩ ተግዳሮቶች የቁጥጥር ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅኖ እየፈጠሩ የሚገኝ ሲሆን፣ ለዚህም ከምንግዜውም በላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እና በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ነገር ግን ደንቡን ለማስፈፀም ከፍተኛ ሚና ያላቸው እና ሚዛን ጣቢያዎቸ በተተከሉብት አካባቢ የሚገኙ አንዳንድ የመስተዳደር አካላት በሚፈለገው ልክ ድጋፍ እያደረጉ ባለመሆኑ በትርፍ ጭነት ቁጥጥር ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እየፈጠረብን ይገኛል፡፡ ስለሆነም ከፍተኛ መዋለ ንዋይ የወጣባቸ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ እድገት ጉልህ ሚና ያላቸው የመንገድ እንዲሁም ድልድይ ሀብታችንን በትርፍ ጭነት ምክንያት ከሚደርስ ጉዳት ለመከላከል በጋራ እንድንሰራ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሀገራዊ ጥሪያችንን እያቀረብን በተለይም የፀጥታ እንዲሁም የክልልና ዞን መስተዳድር አካላት የምንጊዜም ትብብራችሁ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ስንል እንጠይቃለን፡፡ በቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ የሚስተዋሉ ማንኛውም ችግሮች ካሉ፣ ተገልጋዮች ከሥር በተቀመጡት የጥቆማ አማራጮች እንዲያሳውቁን እንጠይቃለን። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

20ኛውን የሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራዊ ኮንፈረንስ  አስመልክቶ ጋዜጣዊ  መግለጫ ተሰጠ አዲስ አበባ፣ ህዳር 5 \2017 ዓ.ም በመጪው ግንቦት   ወር  የሚካሄደውን 20ኛው የሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራዊ ኮንፈረንስ  አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጠ። የ20ኛው አህጉራዊ ኮንፈረንስ  አስቸጋሪ ሁኔታዎችን የሚቋቋም እና ከችግር ቶሎ ማገገም የሚችል እንዲሁም ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር መላመድ የሚችል ማህበረሰብ በመገንባት  አሁንም ወደፊትም የሰው ልጅን የማይተካ ሚና በሚሹ በርካታ የስራ ዘርፎች ዙሪያ የልምድ ልውውጦች የሚካሄዱበት እና  የፖሊሲ ግብዓት የሚገኝበት  ጉባኤ ነው፡፡ ኮንፈረንሱ “የበለጠ የሰው ኃይል በሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት አማራጮች  ጠንካራ ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢን እንፍጠር” (Resilient Communities and Healthy Environment: the Employment Intensive Investment Program approach) በሚል መሪ ሃሳብ  ነው የሚካሄደው፡፡ በመጪው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የምታስተናግደዉ ይኸው አህጉራዊ  ኮንፈረንስ  በዘላቂ የልማት ግቦች ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ለማምጣት ፣ ድህነትን እና ረሃብን ለማጥፋት እንዲሁም ሌሎች የተቀመጡ ግቦችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ  በማሳካት ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ መድረክ መንግስታት ፣ የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች፣ ፋይናንሰሮች እና የልማት አጋሮች ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በሚፈጥሩ እና ክህሎታቸውን በሚያሳድጉባቸው የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና ተያያዥ መስኮች  ላይ ምክክር ያደርጋሉ፡፡ በ20 ኛው አህጉራዊው ኮንፈረንስ ላይ የልማት አጋሮች ፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮች ፣ ምሁራንና ተመራማሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን ሰፊ የስራ እድል በሚፈጥሩ የመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ውጤታማ የሃሳብና የልምድ ልውውጦች  ይካሄዱበታል። በተጨማሪም ሀገራት በመሠረተ ልማቶች ዝርጋታ እንዲሁም ሌሎች የኢንቨስትመንት መስኮች ለዜጎች ጥራት ያለው የሥራ ዕድል በስፋት ሊፈጥሩ የሚችሉባቸውን መንገዶች በተመለከተ የተለያዩ ጥናቶች ይቀርባሉ ፣ የመስክ ጉብኝቶች ይካሄዳሉ ፣ የአገራት ተሞክሮ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።   ይህ ኮንፈረንስ ከላይ የተጠቀሱትን ዓላማዎች ከማሳካት ባሻገር በተጓዳኝ በሚካሄዱ ኩነቶች አማካኝነትን  ሀገራችን  የማስተዋወቅ ዕድል የሚፈጥር ከመሆኑም ባሻገር  የዲፕሎማቶች መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ ተመራጭ የኢንቨስትመንት እና የቱሪስት መዳረሻ መሆኗን በተጨባጭ ለማሳየት ትልቅ እድል የሚፈጥር ነው፡፡ በዚህም መሰረት ሀገሪቷ በከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሌሎች የኮንስትራክሽንና መሠረተ ልማት ሥራዎች ረገድ ያሳካቻቸውን ውጤቶች እና ያላትን ተሞክሮ የምታካፍልበት እንዲሁም እንደ ህዳሴ ግድብ ያሉ አገራዊ ሜጋ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሚኖራቸውን አገራዊና አህጉራዊ ፋይዳ ጭምር የበለጠ የምታስተዋውቅበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። ኢትዮጵያም ከዚህ ቀደም 17ኛውን አህጉራዊ ኮንፈረንስ በስኬት ማካሄዷ የሚታወስ ሲሆን  የዘንድሮውንም በተሳካ መልኩ ለማዘጋጀት የመንግስት ተቋማትን እና ባለድርሻ አካላትን ያካተተ አገራዊ አዘጋጅ ኮሚቴ ተቋቁሟል። ፕሮግራሙን የዓለም ሥራ ድርጅት (ILO) የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እንዲሁም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  በጋራ የሚያዘጋጁት ሲሆን ፣ ፕሮግራሙን  ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተካሄዱ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የድሬደዋ የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት የተለያዩ የጥገና ስራዎችን በማካሄድ ላይ ነው አዲስ አበባ፣ ህዳር 3 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ) ፡- በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በድሬደዋ የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት በበጀት ዓመቱ ሶስት ወራት 121 ኪሎ ሜትር የመደበኛ እና ወቅታዊ ጥገና ለማካሄድ ታቅዶ 106,076,851 ብር ወጪ በማድረግ ከዕቅድ በላይ 171 ኪሎ ሜትር የጥገና ስራ ለማካሄድ ተችሏል፡፡ በሩብ አመቱ በአገልግሎት ብዛት ለብልሽት የተዳረገዉ የደንገጎ-ሐረር መንገድ ዳግመኛ በአስፋልት ደረጃ የተጠገነ ሲሆን ፣ በሜኢሶ-ድሬዳዋ መስመር ለትራፊክ አስቸጋሪ በሆኑ የመንገድ ክፍሎች ላይ የመደበኛ እና የከባድ ጥገና ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ከአየር ንብረት ለዉጥ ጋር በተያያዘ የድልድይ እና የመንገድ መዘጋት እንዳይከሰት የቅድመ መከላከል ስራ የተከናወነ ሲሆን ፣ ከዚህ ቀደም በሚፈለገው ደረጃ የጥገና ሽፋን ያላገኙ የጎዴ-ሀርገሌ ፣ እና ቀብሪደሀር-ሺላቦ መንገዶች በተገቢው ሁኔታ ተጠግነዋል፡፡ በተጨማሪም በዲስትሪክቱ ስር ያሉ የሴክሽን ካምፖችን ይዞታ በማረጋገጥ በተለይም የአዋሽ ሴክሽንን የማደራጀት እና የቢሮ ግንባታ ስራ ተከናውኗል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት ቀሪ ወራቶችም የበጀት አመቱን የመንገድ ጥገና ስራዎች በቀሪ ወራት በጥራት የማካሄድ ፣ በአገልግሎት ብዛት ለብልሽት የተዳረጉ የመንገድ ክፍሎችን በበቂ ሁኔታ የመጠገን ፣ የሀገሪቱ ገቢ እና ወጪ ንግድ የሚከናወንበት የኢትዮ-ጅቡቲ የመንገድ ክፍል እንዳይስተጓጎል ቅድመ መከላከል ስራ የማከናወን እና ከመንገድ ተጠቃሚዉ ለሚነሱ የመንገድ ጥገና ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ የመስጠት ስራዎች ይከናወናሉ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads