es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 537 suscriptores, ocupando la posición 8 357 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 537 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 22, y en las últimas 24 horas de 4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.24%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 921 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 563 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 537
Suscriptores
+424 horas
-357 días
+2230 días
Archivo de publicaciones
photo content
+4

ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ኃይል እንዲያስተላልፍ የወሰን ማስከበር ችግሮች መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል …….///…… የአዳማ 2 ባለ 230 ኪሎቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ኃይል ማስተላለፍ እንዲችል የወሰን ማስከበር ችግሮች በአፋጣኝ መፋትሔ እንዲሰጣቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ጠየቁ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክና ለአዳማ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የተገነባ ቢሆንም መስመሩ በሚያልፍበት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ዸካ አዲ በሚባል ቀበሌ ላይ ባለው የወሰን ማስከበር ችግር ምክንያት የሚጠበቅበትን ኃይል እያስተላለፈ አይደለም። በመስመሩ ሥር መነሳት ካለባቸው 17 ቤቶች መካከል የአዳማ ከተማ አስተዳደር የካሳ ክፍያ ይገባቸዋል ብሎ ላቀረባቸው 13 ቤቶች በካሳ አዋጁ መሠረት ክፍያው ቢፈፀምም ቤቶቹ እስከ አሁን ሊነሱ እንዳልቻሉ ነው ሥራ አስፈፃሚው የጠቆሙት። የወሰን ማስከበር ችግሩ መፍትሔ ሳይሰጠው ሙሉ በሙሉ ኃይል ማስተላለፍ ቢጀመር መስመሩ በተዘረጋበት ኮሪደር ላይ በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ አደጋ ሊያደርስ ስለሚችል ችግሩ እስኪፈታ መጠበቅ ግድ ሆኗል ብለዋል። ስለሆነም ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ኃይል እንዲያስተላልፍ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ለወሰን ማስከበር ችግሩ አፋጣኝ እልባት እንዲሰጡ አቶ ክብሮም ጠይቀዋል። መስመሩ በሚያልፍበት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ዸካ አዲ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ላይ ቤት ገንብተው ከሚኖሩ ነዋሪዎች መካከል አቶ ከበደ ነጋሽ እና አቶ ደበሌ ደቻሳ እንደተናገሩት ለቤታቸው የካሳ ግምት ክፍያ ከአንድ ዓመት በፊት ቢሰጣቸውም ምትክ ቦታ በወቅቱ ባለማግኘታቸው ከአካባቢው ሊነሱ አልቻሉም። ፕሮጀክቱ የሀገር ልማት በመሆኑ እንደሚደግፉት የተናገሩት ነዋሪዎቹ ምትክ ቦታ ከተሰጣቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከአካባቢው እንደሚነሱ አረጋግጠዋል። የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ ሌንሴኔ ሙሐመድ በበኩላቸው ካሳ የተከፈላቸውን ነዋሪዎች ከቦታው ለማስነሳት ምትክ ቦታ ለመስጠት ከቀበሌ መላክ የነበረበት መረጃ ወደ ከተማው ተሟልቶ ባለመምጣቱ በወቅቱ ችግሩን መፍታት አልተቻለም ብለዋል፡፡ የወሰን ማስከበር ችግሩን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመፍታት እንደሚሰራ የተናገሩት ምክትል ከንቲባዋ ችግሩ በምን ያህል ጊዜ እንደሚፈታ ከመናገር ግን ተቆጥበዋል፡፡ 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ የተገነባው ይህ ፕሮደክት በሙሉ አቅሙ ኃይል ማቅረብ ሲጀምር በአዳማ ከተማ እየተስተዋለ ያለውን የኃይል መቆራረጥ እና በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለው የኃይል እጥረት ይቀርፋል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል። እስከ 225 ሜጋ ዋት ኃይል የማስተላለፍ አቅም ያለው የአዳማ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ሲ ኤን በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተገነባ ሲሆን የማስተላለፊያ መስመሩ ደግሞ በራስ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ቢሮ ተከናውኗል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 11 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

የለውጥ ሥራዎችን ለመተግበር ሁሉም በኃላፊነት ሊሰራ ይገባል ........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሁለተኛውን ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም በአግባቡ ለመተግበር ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተውጣጣ የተቋማዊ ለውጥ ሥራ አመራር ቡድን በይፋ ሥራ ጀመረ፡፡ ቡድኑ ሥራውን ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም የጀመረ ሲሆን በዕለቱም ስለሚያከናውናቸው ሥራዎችና ስለተሰጠው ኃላፊነት እንዲሁም ሥራዉን ስለሚያከናውንበት መንገድ በተመለከተ ውይይት አካሂዷል፡፡ በተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ የለውጥ ሥራ አመራር ቡድኑ ሥራውን በይፋ በጀመረበት ወቅት እንደተናገሩት በምዕራፍ አንድ ትግበራ ላይ ከለውጥ ሥራ አመራር ዕይታ አንጻር ተቋሙ ሲመራበት የነበረው መንገድ ክፍተት ነበረበት፡፡ ሁለተኛውን ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም በአግባቡ ለመተግበር እና ከተቋማዊ የለውጥ ሥራ አመራር ጋር በተያያዘ የታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት የባለሙያዎች ቡድን በማቋቋም ወደ ሥራ መግባት እንዳስፈለገም ተናግረዋል፡፡ የተቋቋመው ቡድን ሲስተሙን ለመተግበር በሚሰራው ሥራ ላይ ሲስተሙ ይዞት የሚመጣውን ለውጥ እና ለውጡ የሚተገበርበትን አቅጣጫ በማመለከት ረገድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን የማከናወን ኃላፊነት እንደተሰጠው አመልክተዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘለት መርሃ ግብር ለመተግበር እያንዳንዱ የቡድኑ አባል ለተወከለበት ሥራ ቅድሚያ ሰጥቶ ሥራውን በተነሳሽነትና በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበትም አቶ አታላይ አሳስበዋል፡፡ በኢትዮጵያ አየር መንገድና ሲስተሙን በሚያለማው የህንዱ ኦሪዮን ኩባንያ በኩል የፕሮጀክቱ የተቋማዊ ለውጥ ሥራ አመራር ቡድን መሪ ወ/ሮ ቤተልሔም መንግስቱ በበኩላቸው የሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲሰተም በአግባቡ እንዲተገበር ለማድረግ ከሁለቱ ተቋማት የተቋቋመው ቡድን በቅንጅት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ቡድኑ አሁን ያሉ አሰራሮችን በማጥናት በፕሮጀክቱ ሂደትና በኋላ የሚመጡ የአሰራርና የፖሊሲ ለውጦችን ለተቋሙ ማህበረሰብ በማሳወቅ የተሻሻሉና በሳፕ ትግበራ የሚመጡ አዳዲስ አሰራርሮች ትግበራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንዲ አሳስበዋል፡፡ እንደ ቡድን መሪዋ ገለፃ ለተቋማዊ ለውጥ ሥራ የባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ሚና ወሳኝ በመሆኑ የባለድርሻ አካላት ልየታም በተገቢው ትኩረት ሊከናወን ይገባል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋማዊ ትራንስፎርሜን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱአለም ኪዳኔ በበኩላቸው ከሳፕ ፕሮጀክት ትግበራ ጎን ለጎን ሰዋዊና የሥራ ሂደቶች ላይ ያሉ ለውጦችን በአግባቡ ለማስተዳደር እየተሰራ እንደሚገኘ ጠቅሰዋል። የተቋማዊ ለውጥ ሥራ አመራር ቡድኑ ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ከሚተገበርባቸው የሥራ ክፍሎች እና ለሲስተሙ መተግበር ግብዓት ከሚሰጡ አካላት መዋቀሩን ገልጸዋል፡፡ ቡድኑ ከሳፕ ትግበራ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጉዳዮችን ለመለየትና በሥራ ሂደቶች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ቡድኑ ስለ ለውጡ ወሰን በመረዳት ለውጡ በባለድርሻ አካላት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ እና ባለ ድርሻ አካላት የሚኖራቸውን ድርሻ የመለየት ሥራ እንደሚያከናውንም ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ውጤታማ እንዲሆን ለባላድርሻ አካላት በተለያዩ መንገዶች የማስተዋወቅ ሥራ ለማከናወን የድርጊት መርሃ ግብር በማዘጋጀት እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡ ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ከመጀመሪያው ምዕራፍ የቀጠሉ የፋይናንስ መተግበሪያ ሞጁሎችን ጨምሮ በሰው ሀብት አስተዳደር፣ በግዥ፣ በተሸከርካሪ አስተዳደር፣ በማመንጫ ጣቢያ የጥገና ሥራ አስተዳደር እና ከሌሎች የአገልግሎት ትግበራዎች ጋር የተያያዙ ሞጅሎች ይኖሩታል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 10 ቀን 2015 ዓ.ም  

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

photo content
+2

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሮ ሜካኒካል የስራ መደብ ከቅጥር በፊት ስልጠና ለመውሰድ መጋቢት 30 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በምትኖሩበት አቅራቢያ ፈተና የወሰዳችሁ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ አብላጫ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ስለሆነ በተቋሙ ማሰልጠኛ መመሪያ መሰረት ከስልጠና በኃላ በተመደባችሁበት የስራ ቦታ ለመሄድ ፈቃደኛ የሆናችሁ ከግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 /አምስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት በዋናው መ/ቤት ሜክሲኮ በሚገኘው ኬኬር ህንጻ 2ኛ ፎቅ የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ ዋናውን የትምህርት ማስረጃችሁን እና ዋስ ይዛችሁ በመቅረብ የስልጠና መግቢያ ፎርም እንድትሞሉ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ  የስራ ቦታ ቅያሪ የምትፈልጉ እርስ በርሳችሁ ስልክ በመደዋወል መቀያየር የምትችሉ ሲሆን ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-58-06-23 በመደወል መረጃ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡

photo content

የጡረታ ክፍያን ወደ ሁለት ወር ደመወዝ ማሳደጉን ማህበሩ አስታወቀ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጡረታ ለሚወጡ የማህበሩ አባላት የወር ደመወዛቸውን እስከ 150 በመቶ ሲከፍል የነበረ ሲሆን ከጥር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ክፍያውን ወደ 200 በመቶ ማሳደጉን አስታውቋል፡፡ የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት ማህበሩ አባላቱን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የጡረታ ክፍያን ከፍ ማድረግን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከተቋሙ በጡረታ ለተሰናበቱ 55 የማህበሩ አባላት 1 ነጥብ 47 ሚሊዮን ብር ክፍያ መፈፀሙን ሊቀመንበሩ ተናግረዋል፡፡ በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ክፍያው የሚከናወነው ለአንድ ጊዜ ብቻ ሆኖ የክፍያው የገንዘብ መጠንም የማህበሩ አባል ጡረታ ሲወጣ የሚያገኘውን ደመወዝ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ሊቀመንበሩ አስታውቀዋል፡፡ በዚህ የአባልነት ማዕቀፍ በርካታ የተቋሙ ሠራተኞች ተጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ መኮንን በህመም፣በሞት እና ከሥራ በሚታገዱበት ወቅት ችግር እንዳይገጥማቸው የተለያዩ የክፍያ ሥርዓቶች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ የጡረታ ስንብት ክፍያ እንደ ሠራተኞቹ የአገልግሎት ዘመን እና የአባልነት ቆይታ የሚለያይ ሲሆን በዚህ በጀት ዓመት እንኳ ለአንድ የማህበር አባል 78 ሺህ ብር የጡረታ ስንብት ክፍያ መፈፀሙን አቶ መኮንን አረጋግጠዋል፡፡ በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ተመስርቶ ለአባላት ከሚያቀርበው አገልግሎት በተጨማሪ ከተቋሙ ጋር በቅርበት እና በትብብር በመስራት የደመወዝ፣ የቦነስ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች እንዲከበሩ ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ማህበሩ አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር እንደአዲስ ከተመሰረተ ስምንት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን ከአራት ሺህ በላይ አባላት ያሉት አንጋፋ ማህበር ነው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 09 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢትዮጵያ ግዙፉን ህንፃ ሊያስገነባ ነው ........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ በርዝመቱ የመጀመሪያ የሆነ ባለ 62 ወለል የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ለመገንባት የሚያስችለውን ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ (Dar Al Handasah Shair and Partners) የኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሚስተር ታሪቅ አል ቃኒ ተፈራርመዋል፡፡ በስምምነቱ መሰረት ዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ የህንፃውን ዲዛይን ዝግጅት እንዲሁም በግንባታ ወቅት የቁጥጥር ሥራዎችን ያከናውናል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ከሚገነቡ ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን ገልፀው ሥራው በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲከናወን አሳስበዋል፡፡ የዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ የኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሚስተር ታሪቅ አል ቃኒ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢነርጂ ዘርፍ በምስራቅ አፍሪካ ግዙፉ ኩባንያ መሆኑን ገልፀው ተቋሙን የሚወክል ዲዛይን እንደሚዘጋጅ ተናግረዋል። የህንፃውን ዲዛይን እና የቁጥጥር ሥራ በጥራትና በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡ በ197 ሺህ 800 ካሬ ሜትር መሬት ላይ የሚያርፈው ይህ ግዙፍ ህንፃ ግንባታው ሲጠናቀቅ 327 ነጥብ 5 ሜትር ርዝመት ይኖረዋል፡፡ 445 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት የተመደበለት ይህ ፕሮጀክት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለህንፃው አገልግሎት ኃይል የሚያቀርቡ የንፋስና የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ይኖሩታል፡፡ የዲዛይንና የቁጥጥር ሥራውን የሚያከናውነው ዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ በዓለም ላይ ዘመናዊ እና ግዙፍ የሆኑትን እንደ ማካህ ሮያል ክሎክ ታወር፣ አይከኒክ ታወር እና አብራ አል ባይት ዘምዘም ታወርን ጨምሮ በርካታ ህንፃዎችን የዲዛይን ሥራዎች ያከናወነ ሲሆን በዘርፉ በዓለም ላይ ከሚገኙ 10 ምርጥ ኩባንያዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 08 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በጀት ዓመቱ አስር ወራት የአስር ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራ ተከናውኗል ……….///………. የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለፀ። በዘርፉ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ማስተባበሪያ 1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን እንደገለፁት ተቋሙ አዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ከመገንባት ጎን ለጎን የነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። አቅም የማሳደግ ሥራው በጣቢያዎቹ ትራንስፎርመሮች እና ሲዊችጊሮች ላይ እንደሚከናወን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም የኃይል መቆራረጥ እና አቅርቦት ችግሮችን በመፍታት ለህብረተሰቡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። የጣቢያዎችን አቅም የማሳደጉ ሥራ ጣቢያዎቹ በሚገኙበት አካባቢ ያለውን የኃይል ፍላጎት መሠረት በማድረግ እንደሚከናወን እና ሥራውም ከጊዜ ወደ ጊዜ በአስተማማኝ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሆነ አቶ ፀጋዬ አመልክተዋል። ባለፉት ሦስት ዓመታት በ28 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ አቅም የማሳደግ ሥራ እንደተከናወነ ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የ2015 በጀት ዓመት በ11 ጣቢያዎች ላይ አቅም የማሳደግ ሥራ ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ ባለፉት አስር ወራት የአስር ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራ ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል ። የቀሪ የአንዱ ማከፋፈያ ጣቢያ አቅም የማሳደግ ሥራ ከ50 በመቶ በላይ መድረሱንም ጠቁመዋል። የደብረ ብርሃን፣ ነፋስ መውጫ፣ አዘዞ፣ ሰበታ፣ መካኒሳ፣ ጂግጅጋ፣ ለገጣፎ፣ ሐረር፣ ወልቂጤ እና ወልዲያ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን የከሚሴው ደግሞ በመከናወን ላይ ይገኛል። በበጀት ዓመቱ ለማከናወን በዕቅድ ከተያዙት በተጨማሪ የበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም የማሳደግ ሥራ ማከናወን እንደተቻለም አቶ ፀጋዬ ተናግረዋል። የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራ በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ በዲጂታላይዜሽንና አቅም ማሳደግ መምሪያ (በራስ ኃይል) የሚከናወን ሲሆን ለሥራው የሚያስፈልገው በጀትም በተቋሙ እየተሸፈነ ይገኛል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 08 ቀን 2015 ዓ.ም

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት ላይ ላይ ከተደቀኑት ፈተናዎች መካከል አንዱና ዋንኛው ስርቆት ነው፡፡ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶዎች ላይ ስርቆት የሚፈፀመውን ስርቆት መከላከል ለአንድ ተቋም የሚተው ባለመሆኑ የሁሉንም ጥረት ይፈልጋል፡፡ በዚህ በኩል መሰረተ ልማቶቹ የሚገኙባቸውና አቋርጠው የሚያልፏቸው ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ለመሆኑ የስርቆት ወንጀሉ ምን ይመስላል? ምንዓይነት ተጽዕኖዎች እያሳደረ ነው? የሚመለከታቸው የመንግስት ኃላፊዎች ምን እየሰሩ ነው? በዩቲዩብ ቻናላችን ላይ የጫንናቸው ሁለቱ ፕሮግራሞች መልስ ለመስጠት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ክፍል አንድ https://www.youtube.com/watch?v=cY8jKSmKRcw ክፍል ሁለት https://www.youtube.com/watch?v=z0-ACwsHazw “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 08 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በቀጣዮቹ አስር ዓመታት የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ሽፋን ወደ 96 በመቶ ለማድረስ ታቅዷል ……....///………. በቀጣዮቹ አስር ዓመታት የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት ሽፋን ወደ 96 በመቶ ለማድረስ መታቀዱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የኃይል ማመንጫዎች ስትራቴጂና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ማርዓለም አምደብርሃን እንዳስታወቁት በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ሙሉ ለሙሉ ለማሟላት በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ከተለያዩ ታዳሽ የኃይል ምንጮች የኤሌክትሪክ ኃይልን ማምረት የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቷል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኤሌክትሪክን የመጠቀም ፍላጎት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት ተቋሙ ከተለያዩ ታዳሽ የኃይል ምንጮች አዳዲስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን በመገንባት ሀገራዊ ተልዕኮውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም ሀገሪቱ ለወጠነቻቸው የልማት ግቦች ስኬት የሚያግዝ ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለማቅረብ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የማመጨት አቅሟ 5200 ሜጋ ዋት ደርሷል፡፡ በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ውስጥ የኢኮኖሚውን ፍላጎት ማሟላት የሚችል ኃይል ከውሃ ፣ ከንፋስ ፣ ከፀሀይ እና ከከርሰምድር እንፋሎት ለማመንጨት የሚያስችል ዕቅድ ተጠናቋል ብለዋል። ይህም ሀገሪቱ ካላት እምቅ የተፈጥሮ ሀብት አኳያ ከተለያዩ ታዳሽ ኃይሎች ጥራቱን የጠበቀ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት የሚስችል ዕቅድ ነው። በዕቅዱ ለተለዩ ፕሮጀክቶችም እንደ አስፈላጊነታቸው እና የአዋጭነት ቅደም ተከተላቸው የትግበራ ዕቅድ በማዘጋጀት የፋይናንስ አማራጮችን የማፈላለግ ሥራ እየተሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ ምንጮች ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል የምታመነጭ ሀገር በመሆኗ እንደሀገር ከምታገኘው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባሻገር የአየር ንብረት ለውጥን ተጽዕኖን በመከላከል እና በመቀነስ በኩል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተች መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ከባንኩ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ዕውቀትና ልምድ እንደሚያገኝ ተስፋ አለው .........///.......... በዓለም ባንክ አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት በአካባቢ፣ ማህበራዊ እና የሙያ ደህንነት እንዲሁም በግዢ አስተዳደር ላይ አተኩሮ ሲካሄድ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ። በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ተቋሙ በሁለቱ ቀናት ትልሞቹን ለባንኩ ለማሳወቅ እና በርካታ ነገሮችን ለመማር ዕድል አግኝቷል። ከባንኩ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ዕውቀትና ልምድ እንደምናገኝ ተስፋ አለን ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተቋሙ የተሻለ ነገር በመስራት ከባንኩ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ይሰራል ብለዋል። በዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ፕራክቲስ ማናጀር ኤሪክ ፈርንስትሮም በበኩላቸው ባንኩ ከተቋሙ ጋር በመልካም ግንኙነት ላይ የተመሰረተ የልማት አጋር በመሆኑ ኩራት እንደሚሰማው ተናግረዋል። የዓለም ባንክ ቡድን እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች የተሳተፉበት ሥልጠና በቴክኒካል ጉዳዮች ላይ ዝርዝር ውይይት በማካሄድ በስኬት ተጠናቋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

#የፕሮግራም ጥቆማ# የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተልማት ለማስፋፋት የሚደረገው ጥረት በተፈለገው መንገድ እንዳይጓዝ ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል የወሰን ማስከበርና የካሳ ጉዳይ ይጠቀሳሉ። የወሰን ማስከበር
#የፕሮግራም ጥቆማ# የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተልማት ለማስፋፋት የሚደረገው ጥረት በተፈለገው መንገድ እንዳይጓዝ ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል የወሰን ማስከበርና የካሳ ጉዳይ ይጠቀሳሉ። የወሰን ማስከበር ጉዳይ ለፕሮጀክት ትግበራ እንቅፋት ሊሆን የሚችለው እንዴት ነው? በወሰን ማስከበርና በካሳ ምክንያት አንድ ፕሮጀክት መዘግየቱ የሚያመጣው ጫና ምንድነው? ዛሬ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በኢቲቪ ዜና ቻናል የሚተላለፈው ፍኖተ ብርሃን ፕሮግራም ምላሽ ለመስጠት ይሞክራል።በተጨማሪም በኢቲቪ የኦሮምኛ ቻናል ከምሽት 12:10 ጀምሮ በኦሮምኛ ቋንቋ የሚተላለፈውን ፕሮግራም የሚያነሳቸው የተለያዩ ጉዳዮች ይኖራሉ። ፕሮግራሞቹን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4