es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 537 suscriptores, ocupando la posición 8 357 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 537 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 22, y en las últimas 24 horas de 4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.24%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 921 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 563 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 537
Suscriptores
+424 horas
-357 días
+2230 días
Archivo de publicaciones
#የፕሮግራም ጥቆማ# የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተልማት ለማስፋፋት የሚደረገው ጥረት በተፈለገው መንገድ እንዳይጓዝ ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል የወሰን ማስከበርና የካሳ ጉዳይ ይጠቀሳሉ። የወሰን ማስከበር
#የፕሮግራም ጥቆማ# የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተልማት ለማስፋፋት የሚደረገው ጥረት በተፈለገው መንገድ እንዳይጓዝ ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል የወሰን ማስከበርና የካሳ ጉዳይ ይጠቀሳሉ። የወሰን ማስከበር ጉዳይ ለፕሮጀክት ትግበራ እንቅፋት ሊሆን የሚችለው እንዴት ነው? በወሰን ማስከበርና በካሳ ምክንያት አንድ ፕሮጀክት መዘግየቱ የሚያመጣው ጫና ምንድነው? ዛሬ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በኢቲቪ ዜና ቻናል የሚተላለፈው ፍኖተ ብርሃን ፕሮግራም ምላሽ ለመስጠት ይሞክራል።በተጨማሪም በኢቲቪ የኦሮምኛ ቻናል ከምሽት 12:10 ጀምሮ በኦሮምኛ ቋንቋ የሚተላለፈውን ፕሮግራም የሚያነሳቸው የተለያዩ ጉዳዮች ይኖራሉ። ፕሮግራሞቹን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

ለአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷል .........///.......... በፕሮጀክት ትግበራ ወቅት ለአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው የዓለም ባንክ ባዘጋጀው የግዢ፣ አካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች አስተዳደር ሥልጠና ላይ እንደገለፁት ተቋሙ የአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ጉዳዮች ዓለምአቀፍ ተቀባይነት ባላቸው ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት ስለመተግበራቸው ክትትል እያደረገ ነው። የሥራ ክፍሉንም የሰው ኃይል በማሟላትና የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በማዘጋጀት ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በግል አልሚዎች በሚለሙ ፕሮግራሞች ላይም የአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ጉዳዮች በአግባቡ ስለመተግበራቸው ክትትል ይደረጋል። በሥልጠናው ላይ ሀሳባቸውን የገለፁት የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው የሙያ ደህንነት ጉዳይ ከተቋሙ ዕሴቶች መካከል አንዱ ሆኖ መቀረፁ የተሰጠውን ትኩረት ያሳያል ብለዋል። በትግበራ ወቅት የሚስተዋሉ ችግሮችም በሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጣቸው አሳስበዋል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በይፋ ተጀመረ .........///.......... ለበቆጂ ከተማና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ለሚገነባው የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡  በፕሮግራሙ ላይ የበቆጂ ከተማ ከንቲባ አቶ ሁሲያ አሚን እና የከተማው የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች፣ የአካባቢው አባ ገዳዎችና የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ የፕሮጀክት ማኔጅመንት 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ ተድላ ሰይፉ በግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ ነው። የበቆጂ እና የደብረታቦር ከተሞች የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክትን ግንባታን ለማስጀመር ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ ከተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ጋር በቅንጅት ሲሰራ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተድላ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቅ ለከተሞቹ እና በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ወረዳዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያግዛሉ ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘለት በጀት፣ ጊዜና እና ጥራት አጠናቆ ለማስረከብ ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶት እንደሚሰራ በመግለፅ የአካባቢው ህብረተሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደትግ ጠይቀዋል። የበቆጂ ከተማ ከንቲባ አቶ ሁሲያ አሚን በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በአካባቢው የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችና የኢንቨስትመንት ሥራዎች እንዲስፋፉ ለማድረግ እና ለአካባቢው ወጣቶች ሥራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታ በመርሃ ግብሩ መሠረት ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፋ እና ክትትል እንደሚያደርግም ከንቲባው አረጋግጠዋል። ለበቆጂ እና ደብረታቦር የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ዕቃ የሚያቀርበው ሻንጋይ ሲዩአን የተባለው የቻይና ኩባንያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሊ ይንግጁን እንደተናገሩት ኩባንያቸው ለፕሮጀክቶቹ የሚያገለግሉ ግብዓቶችን በስምምነቱ መሠረት ለማቅረብ በትኩረት ይሠራል። በአሁኑ ወቅት ለግንባታ ሥራው የሚያስፈልጉ አንዳንድ ዕቃዎችን የማምረትና የማጓጓዝ ሥራ እንደተጀመረ ሥራ አስኪያጁ ገልፀው ኩባንያውፕሮጀክቱ ላይ የሚተከሉ ሁሉንም ዕቃዎች በመርሃ ግብሩ መሠረት እንደሚያቀርብ አረጋግጠዋል። የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ 89 ሜጋ ዋት  የመሸከም አቅም ያለው ሲሆን ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር፣ ሁለት ባለ 230ኪሎ ቮልት ገቢ እና አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ይኖሩታል። በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የሚገነባው የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ከመልካ ዋከና - ቆቃ ከተዘረጋዉ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠልፎ( line in and line out) የሚከናወን የ1 ኪሎ ሜትር ማስተላለፊያ መስመር ይዘረጋለታል፡፡ ፕሮጀክቱን የሚገነባው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ሲሆን የማማከር ሥራውን የሚሰራው የተቋሙ ኢንጂነሪንግ ዘርፍ ይከናወናል፡፡   ለፕሮጀክቱ ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪልና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ  እንዲሁም ለማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ የዕቃ አቅርቦት ወጪን ሳይጨምር ከ216 ነጥብ 31 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦለታል። ወጪውም ሙሉ በሙሉ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚሸፈን ነው ተብሏል። የዚህ ፕሮጀክት አካል የሆነውና ከዓለም ባንክ በተገኝ ብድር የሚገነባው የደብረ ታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በቅርቡ እንደሚካሄድም  ከፕሮጀክት ቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ቁልፍ አጋር ሆኖ እየሰራ ነው ........///..... የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ቁልፍ አጋር በመሆን የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ጥሪ አቀረቡ። ባንኩ በግዢ፣ በአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች አስተዳደር እንዲሁም በተቋሙ ስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት ነጥቦች ላይ ያዘጋጀውን ስልጠና ሲከፍቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደተናገሩት ተቋሙ በዓለም ባንክ ድጋፍ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እየተገበረ ነው። በመሆኑም የጀመራቸውን ቁልፍ ድጋፎች አጠናክሮ እንዲቀጥል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠይቀዋል። በዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ፕራክቲስ ማናጀር ኤሪክ ፈርንስትሮም በበኩላቸው ባንኩ ከ56 ሚሊየን የሚልቁ ኢትዮጵያውያንን ከጭለማ ለማውጣት በተለይ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ሥራዎቹ በመልካም ግንኙነት እየተተገበሩ ቢሆንም የሚያጋጥሙትን ማነቆዎች በቅርበት በመነጋገር መፍታት ይገባል ብለዋል። የተዘጋጀው ስልጠናም ስልታዊ ዕሳቤ ለማሳደግና በጋራ ለመስራት እንደሚያግዝ ገልፀዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አንዷለም ሲዓ ተቋሙ በሦስት ዓመታት ውስጥ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ መስመር እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ለማከናወን የያዘውን ዕቅድ አቅርበዋል። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሥልጠና ላይ በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግበ ከተያዘው መርሐግብር መረዳት ተችሏል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

photo content
+2

መምሪያው እያደረጋቸው ያሉ የአይ ሲ ቲ ድጋፎች ሥራዎችን ለማቀላጠፍ እያገዙ ነው ……..///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአይ ሲ ቲ መምሪያ በተቋሙ ለሚገኙ የሥራ ክፍሎች እያደረጋቸው ያሉ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎች ሥራዎችን በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ፡፡ በተቋሙ የምርምርና ልማት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሚራጅ ፈረጃ፣ በገበያና ቢዝነስ ልማት መምሪያ የፕራይሲንግ እና ሪቫሉዌሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ በለጠ፤ በኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ዘርፍ ባለሙያ የሆኑት ራሄል አርዓያ፣ በግዥ መምሪያ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታቸው ጎጃም እንዲሁም የኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ጉቱ እንደተናገሩት የተቋሙ አይሲቲ መምሪያ እያደረጋቸው ያሉ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎች ሥራዎችን በማቀላጠፍ በኩል ፋይዳቸው የጎላ ነው፡፡ ሠራተኞች እንደተናገሩት ለሥራ የሚያገለግሉ ፕሪንተሮችና ኮምፒውተሮች ላይ እንዲሁም ከኔትወርክ እና ከሲስተም ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲያጋጥሙ የተቋሙ የአይሲቲ ባለሙያዎች በሚያደርጉት ድጋፍ ችግሮች እየተቀረፉ ይገኛሉ፡፡ ይህም ሠራተኛው ሥራውን በአግባቡ በማከናውን ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ ያግዛል ነው ያሉት፡፡ ችግር ሲያጋጥማቸውና የባለሙያ ድጋፉ ሲፈልጉ ጥያቄውን በአካል፣ በስልክ እንዲሁም የውስጥ ማስታወሻ ደብዳቤ በማጻፍ እንደሚጠይቁ የተናገሩት ሠራተኞቹ ተጠቃሚው አካል ድጋፉን ለማግኘት ሲፈልግ በሥራ ቦታው ላይ በመሆን ድጋፍ የሚጠይቅበት ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት (ኦን ላይን) መዘርጋት እንዳለበት ጠይቀዋል፡፡ በተቋሙ የአይ ሲ ቲ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ብዙአየሁ አክሊሉ በበኩላቸው የሥራ ክፍሉ ከሲስተም አጠቃቀም፣ ከሃርድ ዌር ጥገና እና ከኔትወርክ ጋር በተያየዘ የሥራ ክፍሎች በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት ድጋፎች እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ የአሰራር ቅልጥፍናን ይፈልጋል ያሉት ዳይሬክተሩ ይህን ለማድረግ ሲስተሞችን ከማዘጋጀት ጀምሮ ከአጠቃቀምና ከኔትወርክ ችግር ጋር በተያያዘ በሥራው ላይ ተጽዕኖ እንዳይኖር የተለያዩ ድጋፎች እንደሚደረጉ ጠቁመዋል፡፡ በሥራ ክፍሉ እየተደረጉ ያሉ ድጋፎች በተጠቃሚው ላይ ያመጣውን ውጤት ለመገምገም፣ ድጋፍ የሚፈልጉ አካላት ጥያቄያቸውን ወጥነት ባለው መልኩ እንዲያቀርቡ ለማድረግ እና ድጋፉንም ወጥነት ባለው መልኩ ለመስጠት የሚያስችል አሰራር ለመዘርጋት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የሚዘረጋው አሰራር የአይ ሲ ቲ ድጋፍ ጥያቄዎችን በመልዕክት፣ በስልክ፣ በኢሜይል እና ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ለማቅረብ እንደሚግዝ ተናግረዋል፡፡ አሰራሩ ሲተገበር የድጋፍ ፈላጊውን እንግልት በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ብዙአየሁ ገለጻ አሰራሩ ባለሙያው ድጋፉን በአግባቡ መስጠቱን ከተጠቃሚው በቀላሉ እርካታ ለመቀበል እና ድጋፉ የሚሰጠውን ሠራተኛ ለመቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡ ባለሙያው የድጋፍ ሥራዎችን በአግባቡ እንዲያከናውን የተለያዩ የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠናዎችን በመስጠት የእውቅና ማረጋገጫ እንዲያገኙ ( ሰርቲፋይድ እንዲሆኑ) ተደርጓል ነው ያሉት፡፡ ዳይሬክተሩ እንዳሉት መምሪያው ለተቋሙ የሥራ ክፍሎች እያደረገ ካለው ድጋፍ በተጨማሪ ለብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል እና ለኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ዘርፍ የተለያዩ ሶፍትዌሮችን አልምቷል፡፡ በተቋሙ እየተተገበረ ያለው የሳፕ ሲስተም ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ድጋፍ ሲደረግ እንደነበር የጠቆሙት አቶ ብዙአየሁ በአሁኑ ወቅት በተቋሙ በኩል የሥራ ኃላፊ በመመደብ ድጋፉ በራስ አቅም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 04 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሁለተኛ ሆኖ አጠናቀቀ .......///......... አስራ ሶስት ክለቦች በተሳተፉበት የ2015 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሁለተኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 61 ነጥብ በመሰብሰብ አንደኛ ሆኖ የዋንጫ ባለቤትነቱን ሲያረጋግጥ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ52 ነጥብ ሁለተኛ፣ ሐዋሳ ከነማ ደግሞ በ51 ነጥብ ሶስተኛ በመሆን አጠናቀዋል፡፡ በሐዋሳ እና ባህርዳር ከተሞች በተካሔደው የሁለት ዙር ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካደረጋቸው 24 ጨዋታዎች 16 ጨዋታዎችን በማሸነፍ፤ በአራቱ አቻ ወጥቶ እንዲሁም በአራት ጨዋታዎች ተሸንፎ በድምሩ 52 ነጥብ እና 36 ንፁህ ጎል መሰብሰብ ችሏል፡፡ በውድድር ዓመቱ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጠቃላይ 11 ጎሎች ብቻ ተቆጥረውበት ከሁሉም የሊጉ ክለቦች ዝቅተኛ ጎል በማስተናገድ ጠንካራ የተከላካይ ክፍል ያለው መሆኑን አስመስክሯል፡፡ ክለቡ ካስቆጠራቸው ጎሎች መካከል ትንቢት ሳሙኤል ዘጠኝ ጎሎች ከመረብ በማሳረፍ የክለቡ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ስትሆን ምንትዋብ ዮሐንስ በስምንት ጎል ትከተላታለች፡፡ ባለፈው እሁድ በተከናወነው የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ ለአሸናፊ ክለቦች የዋንጫ እና የሜዳሊያ ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ለምስጉን ዳኞች እና ኮሚሽነሮች እንዲሁም ለሊጉ ውጤታማነት አስተዋጽኦ ላደረጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል፡፡ በውድድር ዘመኑ ሁሉም ተጫዋቾች እንደቡድን በጋራ በመጫወት እንዲሁም የአሰልጣኞች አባላትም ተናበው በመስራት ይህ ውጤት እንዲመጣ ጉልህ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሲሆን የክለቡ ቦርድ አመራሮች፣ የክለቡ ጽ/ቤት፣ ደጋፊዎችና መላ የስፖርት ቤተሰቡ የማይተካ ሚና ተጫውተዋል፡፡ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ክለብ ባለፈው ዓመት በተካሔደው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ በተመሳሳይ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et ግንቦት 02 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በጥገና ሥራ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማዳን ተችሏል ---///--- በአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ አቅም በተከናወነ የጥገና ሥራ ከ250 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በላይ ማዳን መቻሉን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ፡፡ ኃላፊዋ ወ/ሮ ዓይናለም ወ/ሚካኤል እንደተናገሩት በተለያዩ ችግር ምክንያት ቆመው የነበሩ የንፋስ ተርባይኖችን በተቋሙ የጥገና ባለሙያዎች መጠገን ተችሏል። የንፋስ ተርባይኖቹን ለጥገና ከባድ የሚያደርጋቸው በ 65 ሜትር ከፍታ በመገኘታቸውና ለመውጣትና ለመውረድ አስቸጋሪ በመሆኑ ነው፤ ይህንንም 20 ፎቅ ያለውን ህንፃ ቀጥ ባለ መሰላል ከመውጣትና መውረድ ጋር አነጻጽረውታል፡፡ ተርባይኖቹ ሁልጊዜም ኃይል ማመንጨት እንዲችሉ ችግሮች ከመከታቸው በፊት የቅድመ መከላከል የጥገና ሥራ እንደሚሰራ፣ ችግሮች እንደተከሰቱ ወዲያውኑ የሚከናወን የጥገና ሥራ መኖሩን እና ችግሮቹ ከተከሰቱ በኋላም ሳምታዊ የፍተሻ እንደሚካሄድ ኃላፊዋ ገልፃዋል፡፡ እንደ ኃላፊዋ ገለፃ ጣቢያው ባሉት 38 ቴክኒሺያንና መሐንዲስ የጥገና ባለሙያዎች የጥገና ሥራውን በማከናወኑ ለውጭ ባለሙያዎች ሊያወጣ የሚችለውን ከ250 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በላይ ማዳን ተችሏል። ጣቢያው ያዳነው ወጪ ኃይል ማመንጫው ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ቢሆንም በዋናነት ግን ከባለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ በተደረጉ የጥገና ስራዎች መሆኑን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል፡፡ የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሀገራችን ካሉ የነፋስ ኃይል ማመንጫዎች ቀዳሚ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዋ እያንዳንዳቸው 1 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የሚያመነጩ 34 ተርባይኖች ሲኖሩት በድምሩ 51 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። አዳማ አንድ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ህዳር 22 ቀን 2005 ዓ.ም. በቀድሞ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃ/ማርያም ደሣለኝ ተመርቆ ሥራ መጀመሩ ይታወሣል:: “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 02 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

በስርቆት የተነሳ በቢሾፍቱ ከተማ በከፊል እንዲሁም በዙሪያው ባሉ ፋብሪካዎች ደግሞ ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጧል ………////……… ከቢሾፍቱ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ከተማዋና በከተማዋ ወዳሉት ፋብሪካዎች የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ሁለት ምሰሶዎች በሌቦች ተቆርጠው በመውደቃቸው ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የማዕካላዊ ሪጅን 2 ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንዳስታወቁት ምሰሶዎቹ ተቆርጠው በመውደቃቸው በቢሾፍቱ ከተማ በከፊል እንዲሁም በዙሪያው ያሉ ፋብሪካዎች ደግሞ ሙሉ በሙሉ ኃይል አጥተዋል። በመሆኑም ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ ለቢሾፍቱ ከተማ በከፊል፣ በአካባቢው ካሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች መካከል ለስቲሊ አር ኤም፣ ሲ ኤንድ ኢ እና አቢሲኒያ የብረት ፋብሪካዎችን ጨምሮ ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ እና ወደ ኢላላ ገዳ የሚሄዱ መስመሮች ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን አቶ አለማየሁ ገልፀዋል፡፡ ምሰሶዎቹ ተቆርጠው የወደቁበት አካባቢ ከመኖሪያ መንደር እና ከአንድ የብረት ማቅለጫ ፋብሪካ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ መሆኑ ድርጊቱን አስደንጋጭ እንዳደረገው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊቶችን በየአካባቢው ያሉ የመስተዳደር አካላት መከላከልና ማስቆም የማይችሉ ከሆነ ዝርፊያ የተፈፀመባቸው አካባቢዎች ለረጅም ጊዜ ኃይል ሊያጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል ብለዋል። የኃይል መቋረጡን በጊዜያዊነት የእንጨት ምሰሶዎችን በመትከል ለማስተካከል ጥረት መጀመሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ ችግሩ እስኪቀረፍ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የፋብሪካ ባለቤቶች በትዕግስት እንዲጠብቁ እና ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ የክትትልና ድጋፍ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ………///……… ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የሚገነባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ፣ ወጪና ጥራት እንዲከናወን ለማድረግ ተገቢው የክትትልና ድጋፍ ሥራ እንዲሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉማሜ ወረዳ ሞጆ ከተማ አካባቢ በተቋሙ ራስ ኃይል እየተገነባ የሚገኘውን የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሥራ እንቅስቃሴ በመስክ ተገኝተው ገምግመዋል። የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ከዚህ በፊት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ሲከናወኑ ከነበሩበት አሰራር በመውጣት በአዲስ የአሰራር ሥርዓት ማኑዋል መሠረት የተጀመረ በመሆኑ ሂደቱን በቅርበት በመከታተል በወቅቱ መፍትሔ ለመስጠት የመስክ ጉብኝቱ መካሄዱን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ፕሮጀክቱን ውጤታማ ለማድረግ የግንባታ ሥራው በማኑዋሉ ላይ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት መከናወን አለበት። ፕሮጀክቱን በስምምነቱ ላይ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ማጠናቀቅ ከተቻለ በቀጣይ ከፋይናንስ አቅራቢዎች ገንዘብ በማፈላለግ ሌሎች ሥራዎች ለውጭ ሥራ ተቋራጮች ሳይሰጡ በራስ አቅም እንዲከናወኑ ለማድረግ እና በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ለመስራት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ፕሮጀክቱ ከጅምሩ በጥሩ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው ከግንባታ ሥራው በተጓዳኝ የሠራተኞችን ደህንነትና ጤንነት ለመጠበቅ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል። የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ፣ ንብረቶችን የማስተዳደር፣ የቢሮና የዕቃ ግምጃ ቤቶችን የማደራጀቱ ሥራ አዲሱን ማኑዋል መሠረት ባደረገ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል። እስከ አሁን ድረስ ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሃ ግብርና በጀት መሠረት እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ፕሮጀክቱ የሚከናወንበትን ቦታ የማጽዳት፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍሉ የሚገነባበት ቦታ የመሬት ቆረጣ እና የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤት ቁፋሮ ሥራ መጠናቀቁንና የስዊችያርድ እና ሌሎች የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የሚተከሉበት የመሠረት ቁፋሮ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያው ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በተቋሙ የራስ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ቢሮ የሚከናወን ሲሆን በማማከር ሥራው ላይ ደግሞ የተቋሙ ኢንጂነሪንግ ቢሮ እየተሳተፈ ይገኛል። የግንባታ ሥራውን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን ለዚህም በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን የሚሸፈን ከ259 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለታል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 30 ቀን 2015 ዓ.ም

በድጋሚ የወጣ የሥራ ማስታወቂያ
+1
በድጋሚ የወጣ የሥራ ማስታወቂያ

EEP Communication - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @eepcommuication