es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 692 suscriptores, ocupando la posición 8 024 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 156 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 692 suscriptores.

Según los últimos datos del 28 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 137, y en las últimas 24 horas de -5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 35.24%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 17.40% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 528 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 730 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 12.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 692
Suscriptores
-524 horas
-17 días
+13730 días
Archivo de publicaciones
photo content
+8

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአስተናጋጅ (Waiter) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር አ.ኤ.ኃ/8.4/245/18 ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስ
+3
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአስተናጋጅ (Waiter) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር አ.ኤ.ኃ/8.4/245/18 ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የፅሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ  ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

በማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል ፍላጎት በማደጉ የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ ....///…. በአካባቢው ካለው የከተሞችና የኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በሚዛን ባለ 132 ኪሎ ቮልት
+6
በማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል ፍላጎት በማደጉ የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ ....///…. በአካባቢው ካለው የከተሞችና የኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በሚዛን ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ያለው የኃይል ጭነት በፍጥነት እያደገ መምጣቱን የጣቢያው ኃላፊ ወ/ሮ ፀጋነሽ ሞላ ተናግረዋል ማከፋፈያ ጣቢያው በአሁኑ ወቅት 6 ነጥብ 3 እና 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል መሸከም የሚችሉ ሁለት ትራንስፎርመሮች ያሉት ሲሆን በ132 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል በስድስት ባለ 15 እና ባለ 33 እንዲሁም በአንድ ባለ 66 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት እያቀረበ ይገኛል። የጣቢያው ኃላፊ እንዳብራሩት በሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለሚዛን፣ ሸኮ፣ አማን ከተሞችና አካባቢዎቻቸው ኃይል የሚሰራጭ ሲሆን በ33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ደግሞ ለዲማ፣ ጨና 1 እና 2፣ ባቹማ፣ ሸዋ ቤንች ከተሞችና አካባቢዎች እስከ ጋምቤላ ክልል ድረስ ኃይል ያቀርባል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያው-የኃይል-ፍላጎት-በማደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ የካይዘን ሥርዓትን ተግባራዊ አደረገ ....///…. የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብክነትን በመቀነስ የሥራ ቅልጥፍናን የሚያሳድገውን የካይዘን የአሠራ
+5
የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ የካይዘን ሥርዓትን ተግባራዊ አደረገ ....///…. የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብክነትን በመቀነስ የሥራ ቅልጥፍናን የሚያሳድገውን የካይዘን የአሠራር ሥርዓት በተግባር ማዋል ጀመረ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት በጣቢያው የሚገኙ ልዩ ልዩ የመለዋወጫ ዕቃዎች በካይዘን ፍልስፍና መርሆዎች መሠረት በግምጃ ቤት ውስጥ በሥርዓት እንዲቀመጡና እንዲደራጁ ተደርጓል። ይህም ዕቃዎቹ ለአገልግሎት በሚፈለጉበት ወቅት ያለ ምንም እንግልትና ጊዜ ሳይባክን በቀላሉ ለማግኘት ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። ስለ አሠራሩ አስፈላጊነት አቶ ሀብታሙ ሲያብራሩ የካይዘን ሥርዓት መተግበሩ በጣቢያው የሚታዩ አላስፈላጊ የሀብትና የጊዜ ብክነቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት ይረዳል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የወላይታ-ሶዶ-ኮንቨርተር-ጣቢያ-የካይዘን 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙን ከተለያዩ የሕግና የፋይናንስ ስጋቶች ለመከላከል በትኩረት መስራት ይገባል ....///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ ተቋሙን ከተለያዩ የ
+7
ተቋሙን ከተለያዩ የሕግና የፋይናንስ ስጋቶች ለመከላከል በትኩረት መስራት ይገባል ....///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ ተቋሙን ከተለያዩ የሕግና የፋይናንስ ስጋቶች ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳሰቡ። ይህ መልዕክት የተላለፈው ተቋሙ ለሕግ ባለሙያዎቹ በሕግና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ  ሥልጠና እንዲሰጥለት ለፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በተዘጋጀው የሥልጠና ማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ላይ ነው። የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዱጉማ ነዳ ባስተላለፉት መልዕክት ሥልጠናው የሕግ ባለሙያዎቹ ከተቋሙ ነባራዊ ሁኔታና የቢዝነስ እንቅስቃሴዎች ጋር የተጣጣመ የላቀ የሕግ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል በእጅጉ ያግዛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙን-ከተለያዩ-የሕግና-የፋይናንስ-ስጋ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

የጣቢያው ሁለተኛ የግንባታ ምዕራፍ እየተከናወነ ነው ....///…. የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሁለተኛው የግንባታ ምዕራፍ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ አማካሪ ተወካይ ሪዚ
+9
የጣቢያው ሁለተኛ የግንባታ ምዕራፍ እየተከናወነ ነው ....///…. የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሁለተኛው  የግንባታ ምዕራፍ  በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ አማካሪ ተወካይ ሪዚደንት መሀንዲስ አስታወቁ:: ተወካዩ አቶ ሰለሞን ክንፈ እንደገለፁት የጣቢያው ግንባታ በሁለት ምዕራፎች የተከፈለ ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ 32 የንፋስ ተርባይኖችን በመትከል 80 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት ተችሏል። በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ባለው በሁለተኛው የግንባታ ምዕራፍ ደግሞ የ16 ተርባይኖች ተከላ ሥራ እየተሠራ ይገኛል። ይህም ጣቢያው ተጨማሪ 40 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ የሚያስችለው ሲሆን አጠቃላይ የማመንጨት አቅሙን 120 ሜጋ ዋት በማድረስ ሀገሪቱ በኃይል አቅርቦት ዘርፍ ለምታደርገው እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጣቢያው-ሁለተኛ-የግንባታ-ምዕራፍ-እየተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤ
ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤት ሀገራት በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል። ሀገራችን የምታስተናግደው ኮፕ 32 (COP 32) ጉባኤ፣ ተቋማችን የአፍሪካን አህጉር ካርቦን የመቀነስ (Decarbonization) ጉዞ በግንባር ቀደምትነት እየመራ መሆኑን ያበስራል። ንፁህ ኃይልን በመሸጥ የውጭ ምንዛሬን እናሰባስባለን፤ የአየር ንብረት ብክለትንም በጋራ እንከላከላለን! ቀጣናዊ ትስስር በታዳሽ ኃይል ልማት! #RegionalIntegration #PowerExport #GreenAfrica #COP32 #EthiopianElectricPower 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤ
ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤት ሀገራት በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል። ሀገራችን የምታስተናግደው ኮፕ 32 (COP 32) ጉባኤ፣ ተቋማችን የአፍሪካን አህጉር ካርቦን የመቀነስ (Decarbonization) ጉዞ በግንባር ቀደምትነት እየመራ መሆኑን ያበስራል። ንፁህ ኃይልን በመሸጥ የውጭ ምንዛሬን እናሰባስባለን፤ የአየር ንብረት ብክለትንም በጋራ እንከላከላለን! ቀጣናዊ ትስስር በታዳሽ ኃይል ልማት! #RegionalIntegration #PowerExport #GreenAfrica #COP32 #EthiopianElectricPower 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ማመንጫ ጣቢያው የ9 ወራት ዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ አሳካ ...///… የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 9
+6
ማመንጫ ጣቢያው የ9 ወራት ዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ አሳካ ...///… የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ:: ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙሉቀን ተሰማ እንዳስታወቁት ጣቢያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ32 ተርባይኖች 258 ነጥብ 28 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዶ 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ችሏል። አፈፃፀሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ8 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱንም ገልፀዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት የጣቢያው ዝግጁነት ወይም የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ (Plant Availability) እና ኃይል ከሚያመነጨው አቅም አንፃር ጥቅም ላይ የዋለው (Utilization Index – UI) አፈፃፀም ከዕቅዱ በላይ መሆኑን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማመንጫ-ጣቢያው-የ9-ወራት-ዕቅዱን-99-ነጥብ-1-በ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገለፀ የአጋሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተ
+5
የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገለፀ የአጋሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ ሁኔታ በማሟላት ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሞሲሳ እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው በ1980ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የነበረው የኃይል መጠን 132 ኪሎ ቮልት ብቻ ነበር። በወቅቱም በአንድ ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር እና በሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት ለአጋሮ ከተማና ለአካባቢው ውስን ማህበረሰብ ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል ያቀርብ እንደነበር አስታውሰዋል።  ይሁን እንጂ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ተከትሎ በ2008 ዓ.ም ሰፊ የአቅም ማሳደግና የማስፋፊያ ሥራዎች ተከናውነውለታል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአጋሮ-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ተጨማሪ-ደንበኞች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ያልተነካውን የፀሐይ ኃይል አቅማችንን ማልማት! ኢትዮጵያ ዐሥራ ሦስት ወራት ሙሉ የምታገኘውን የፀሐይ ብርሃን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግዙፍ የሶላር ፕሮጀክቶችን በ
ያልተነካውን የፀሐይ ኃይል አቅማችንን ማልማት! ኢትዮጵያ ዐሥራ ሦስት ወራት ሙሉ የምታገኘውን የፀሐይ ብርሃን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግዙፍ የሶላር ፕሮጀክቶችን በዕቅድ እየመራ ይገኛል። እነዚህ የአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ ፕሮጀክቶች በኮፕ 32 መድረክ ላይ ለዓለም አቀፍ አጋሮች የሚቀርቡ ዋና ዋና ማሳያዎቻችን ናቸው። ታዳሽ ኃይልን ማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምንጠቀምበት ዋናው ስትራቴጂያችን ነው። የተፈጥሮ ብርሃን ለሀገር ብልጽግና! #SolarPower #RenewableEnergy #CleanFuture #COP32Sustainable #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ከሜጋ ዋት በስተጀርባ ያሉት የብርሃን ታሪኮች! እኛ የምናመነጨው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ደረቅ ቁጥር ሳይሆን በኢንዱስትሪዎቻችን ውስጥ ለሚሰሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ለ
ከሜጋ ዋት በስተጀርባ ያሉት የብርሃን ታሪኮች! እኛ የምናመነጨው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ደረቅ ቁጥር ሳይሆን በኢንዱስትሪዎቻችን ውስጥ ለሚሰሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ለሚታደጉ ሕይወቶች ዋስትና፣ ለነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ ለሚሰንቁ ሕፃናት የብርሃን ምንጭ ነው! ኮፕ 32 በኢትዮጵያ መካሄዱ ሀገራችን የምታመነጨው አረንጓዴ ኃይል ማኅበራዊ ፍትሕንና የአየር ንብረት ጥበቃን እንዴት እያረጋገጠ እንደሚገኝ ለዓለም የምናስመሰክርበት ወሳኝ መድረክ ነው። ⚡️የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል - ሕይወትን በታዳሽ ኢነርጂ ማብራት! #HumanStory #Sustainability #CleanPower #COP32Ethiopia #EEPBrand #EmpoweringLives 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

የአየር ንብረት ለውጥን የማይበግረው የምድር ውስጥ እንፋሎት ኃይል! የአየር ንብረት ለውጥ የውሃ መጠንን በሚቀንስበት ጊዜ እንኳ ያለምንም መቆራረጥ 24/7 አስተማማኝ ኃይል መስጠት የሚችለው የጂኦተር
የአየር ንብረት ለውጥን የማይበግረው የምድር ውስጥ እንፋሎት ኃይል! የአየር ንብረት ለውጥ የውሃ መጠንን በሚቀንስበት ጊዜ እንኳ ያለምንም መቆራረጥ 24/7 አስተማማኝ ኃይል መስጠት የሚችለው የጂኦተርማል (የምድር ውስጥ እንፋሎት) ኃይል የሀገራችን ሌላኛው ትልቅ አቅም ነው። ኢትዮጵያ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ያላትን ሰፊ የጂኦተርማል ኃይል አቅም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አማካኝነት ወደ ልማት እያቀረበችው ትገኛለች። ኮፕ 32 ሀገራችን በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ (Climate-Resilient) የኃይል አማራጮችን በማስፋፋት ረገድ ያላትን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ የምታጋራበት መድረክ ነው! ⚡️ የማይበገር አረንጓዴ ኃይል ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ! #GeothermalEnergy #ClimateResilient #CleanEnergy #COP32Ethiopia #EEP

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የቀረበውን መስፈርት አሟልታችሁ የጽሁፍ ፈተና ከወሰዳችሁ መካከል ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች፤ ዕሮብ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ለሚሰጠው የቃል ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

1፡ ታሪካዊ ስኬት ለሀገራችን! ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) ለማስተናገድ መመረጧ፣ በታዳሽ ኃይል ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የደረሰችበትን የላቀ ደረ
1፡ ታሪካዊ ስኬት ለሀገራችን! ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) ለማስተናገድ መመረጧ፣ በታዳሽ ኃይል ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ ያሳያል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃ፣ ከንፋስ፣ ከፀሐይና ከእንፋሎት (Geothermal) 100% ንፁህና ለአየር ንብረት የማይበክሉ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በስፋት በመገንባት የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በግንባር ቀደምትነት እየመራ ይገኛል። ኮፕ 32 ተቋማችን የሚያመነጨውን ዘላቂ ኃይል ለዓለም አቀፍ ባለሀብቶችና ለአጋር ድርጅቶች ለማስተዋወቅ ትልቅ ድልድይ ነው! ኃይል ለኢትዮጵያ ብልጽግና፣ ንፁህ ኢነርጂ ለዓለም ደህንነት! #EthiopiaCOP32 #GreenEnergy #RenewablePower #EEP #CleanEnergy #ClimateAction 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የቀረበውን መስፈርት አሟልታችሁ የጽሁፍ ፈተና ከወሰዳችሁ መካከል ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች፤ ዕሮብ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ለሚሰጠው የቃል ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የአረፋ በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የጽናት፣ የሰ
የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የአረፋ በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የጽናት፣ የሰዋዊ መተሳሰብና ለላቀ ዓላማ የመገዛት ታላቅ ተምሳሌት ነው። ተቋማችን በሀገሪቱን እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨትና በማስተላለፍ ረገድ ሀገራዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት እየተወጣ ይገኛል። ይህን ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ ይበልጥ ወደ ላቀ ስኬት ለማሸጋገርእንደ በዓሉ እሴቶች ሁሉ የሁላችንም የጸና ቁርጠኝነት፣ የጋራ ትብብርና ሙያዊ መስዋዕትነት እጅግ አስፈላጊ ነው። ሀገራችንን የብርሐን ማማ ላይ ለማድረስ ቀን ከሌሊት ለምትተጉ መላው የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች ለምታበረክቱት ተቋማዊና ሀገራዊ ውለታ ተቋሙ ታላቅ ክብርና እውቅና ይሰጣል። የዘንድሮው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ለሀገራችን ሰላምና አንድነትን ለተቋማችን አዳዲስ ስኬቶችን ለሁላችንም ደግሞ የስራ ተነሳሽነታችንን የሚያድስ እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ። ዒድ ሙባረክ! ኢ/ር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጤት ማሳወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት/Child Caregivers /የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/169/18 የካቲት 30
የውጤት ማሳወቂያ  ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት/Child Caregivers /የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/169/18 የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ አውጥቶ ሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የፅሁፍ የተግባር ፈተና መሰጠቱ  ይታወቃል፡፡   ስሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከተራ.ቁ1 እስከ 5 የተገለጸው አመልካቾች ከግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5/አምስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ  የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማመንጫ ግድቦች በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ ይገኛሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በአስተማማኝ እና በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ጀኔሬሽን
+4
የኃይል ማመንጫ ግድቦች በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ ይገኛሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በአስተማማኝ እና በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ጀኔሬሽን ቢዝነስ የግድብ ደህንነት ክትትል እና ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤሊያስ ደላሽ እንዳስታወቁት የግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥና ሊከሰቱ ለሚችሉ ችግሮች አስቀድሞ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለመውሰድ በግድቦችና ተያዥ አካላት ላይ በየጊዜው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ ይከናወናል፡፡   በዚህም ባለፉት አስር ወራት በመበልካ ዋከና፣ በግልገል ጊቤ አንድና ሁለት፣ ጊቤ ሶስት፣ ጢስ አባይ፣ ጣና በለስ፣ ቆቃ፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ገናሌ ዳዋ፣ ተከዜ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና በኮይሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት ግድብ እና ተያያዥ ህዳጎች ላይ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማመንጫ-ግድቦች-በጥሩ-የደህንነት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

EEP Communication - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @eepcommuication