ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 554 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 397 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 165 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 554 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.74‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 14.94‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 003 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 323 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 9.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 554
المشتركون
+124 ساعات
+87 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
የብሔራዊ ጥቅም መከበር ተቋሙ ቀጣናዊ ሚናውን እንዲወጣ ያስችለዋል- ኢንጂነር አሸብር ባልቻ  ..…..///…….. የብሔራዊ ጥቅም መከበር ተቋሙ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ሚናውን በአግባቡ ለመወጣት እንደሚያስችለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች "የብሔራዊ ጥቅምና የጂኦ ስትራቴጂ ቁመና" በሚል መሪ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አድርገዋል፡፡ በዕለቱ በውይይቱ ላይ የቀረበውን ሰነድ መነሻ በማድረግ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደገለፁት መንግሥት የውስጥና የውጭ ተጋላጭነትን ለመቀነስ ጠንካራ እና የጠራ አቋም ይዞ መንቀሳቀስ ይገባዋል፡፡ የብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር የመንግሥት ጉዳይ ብቻም ሳይሆን የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባው ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ ያነሳችው የባህር በር የባለቤትነት ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው ጥያቄው ታሪካዊ፣ ፍትሐዊ እና ህጋዊ መሰረት ያለው በመሆኑ ሁለንተናዊ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡ መንግሥት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞችን በዝርዝር ለህብረተሰቡ የማሳወቅና የባለቤትነት ስሜት እንዲሰማው የማድረግ ሥራ መስራት እንዳለበትም ተናገረዋል፡፡ በውይይቱ ላይ ለተነሱ ሃሳቦች ማብራሪያ እና የማጠቃለያ ምላሽ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በህዝብ ብዛት ከአፍሪካ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ የባህር በር እስረኛ ልትሆን አይገባም፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከውሃ፣ ከንፋስና ከቆሻሻ ከምታገኘው ኢነርጂ በተጨማሪ ከኒውክሌር እና ከተፈጥሮ ጋዝ ኃይል ማመንጨት የሚያስችላትን ርዕይ ሰንቃ ለተግባራዊነቱ እየተንቀሳቀሰች ነው ብለዋል፡፡ የባህር በር ባለቤት መሆን ተቋሙ በኃይል ልማት ዘርፉ ለሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች መሳካት አወንታዊ ሚና እንደሚኖረው ነው ኢንጂነር አሸብር የጠቆሙት፡፡ እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የተቋሙ አመራር እና ሠራተኛ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ ብሔራዊ ጥቅሞችን ታሳቢ ማድረግ አለበት፡፡ ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ የጠቀሱት ኢንጂነር አሸብር የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እንዲቻል ሁሉም አመራር እና ሠራተኛ በቁርጠኝነት እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

የነገ ብሔራዊ ጥቅማችን የሚከበረው በዛሬ ሥራችን ነው ‎.......///........ ‎የነገ ብሔራዊ ጥቅማችን መከበር በዛሬ ሥራችን ይወሰናል ሲሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ ገለጹ። ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች “ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦ ስትራቴጂ ቁመና” በሚል መሪ ሀገራዊ አጀንዳ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ የውይይቱ መነሻ  ሰነድ ያቀረቡት ኢንጂነር ውድነህ የማነ የብሔራዊ ጥቅምና ጂኦ ስትራቴጂ ምንነት፣ የብሔራዊ ጥቅም መሠረታዊ ግቦችና ዋነኛ ፈተናዎች እንዲሁም ያሳደሩት ተፅዕኖዎች እና ቀጣይ ሥራዎችን ዳሰዋል፡፡ ‎ብሔራዊ ጥቅም ከፖለቲካው አስተሳሰብ በላይ የሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ፣ ፖለቲካዊ አቅምንና ተጽዕኖ ፈጣሪነትን ማጎልበት፣ የባህል ነጻነትን መጠበቅ እንዲሁም የሕዝቡን ማህበራዊ ልማት ማሳደግ ግቡ ያደረገ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ፈተናዎች መልክዓ ምድራዊ እስረኝነት እና ጂኦ ስትራቴጂያዊ  ጉዳዮች መሆናቸውን አመልክተዋል። ‎ኢትዮጵያ አራት የባህር በሮችን የምትጠቀምበት ጊዜ እንደነበር ያስታወሱት ኢንጂነር ውድነህ ሆኖም ታሪካዊ ጠላቶችና የውስጥ ባንዳዎች ዐባይንና የቀይ ባህርን እንዳትጠቀም በሸረቡት ሴራ  የባህር በር አልባ መሆኗን ተናግረዋል፡፡ ይህም ኢኮኖሚያዊ ጉዳትን ከማስከተሉም ባሻገር የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን በማደናቀፍ እና የሕዝቦችን ማህበራዊ ፍትህ በማስተጓጎል በሀገሪቱ ላይ ከፍተኛ የሉዓላዊነት ስጋት መደቀኑን ተናግረዋል፡፡ ‎መንግሥት ችግሩን በዘላቂነት በመቅረፍና ብሔራዊ ጥቅምን በማስከበር ከጂኦ ስትራቴጂያዊ  ኩስምና ወደ ታደሰ ቁመና ለመለወጥ የኢትዮጵያ የባህር በር የባለቤትነት ጥያቄ ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ፍትኃዊ ነው በሚል ሰፊ ሥራ እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በዚህም ‎የውስጥና የውጭ ተጋላጭነትን በማስወገድ አጀንዳው ከመረሳት ወጥቶ ሕዝቡ በባለቤትነት እንዲይዘው ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የውስጥ እና የውጭ ባዳዎች ጥምረት ፈታኝ መሆኑን ያነሱት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው የተቋሙ አመራርና ሠራተኛ ሴራውን በመመከት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተጀመረው የብሔራዊ ጥቅም ስኬት በባህር በር ባለቤትነት እንዲደገም ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም የተቋሙ ሠራተኛ እና አመራር በችግሮች ባለመታሰር ሥራውን ውጤታማ በሆነ መንገድ በመፈፀም በሕዝብና በመንግሥት መካከል መታማመን እንዲፈጠር ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላይ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች "ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦ ስትራቴጂ ቁመና" በሚል መሪ ሀገራዊ አጀንዳ ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው፡፡ ‎ ‎በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ መድረኩ ሁሉም የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች በወቅታዊ፣ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቂ መረዳት ኖሯቸው ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር በሚደረገው ተልዕኮ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ለማድረግ ያለመ ነው። ‎ ‎ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ጂኦ ስትራቴጂ ቁልፍ ጉዳይ ነው። ይህም ተቋሙ በቀጣናዊ የኃይል ትስስር ላይ የጎላ ሚና እንዲጫወት ያስችለዋል ብለዋል። ‎ ‎የተቋሙ አመራር እና ሠራተኛ ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆን አለበት ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተቋሙ ከቀጣናው ባሻገር በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ውይይቱ ጠቃሚ መሆኑን ገልፀዋል። ‎ ‎የብሔራዊ ጥቅምና ጂኦ ስትራቴጂ ምንነት፣ የብሔራዊ ጥቅም መሠረታዊ ግቦች፣ የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ፈተናዎች እንዲሁም ፈተናዎች በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያሳደሩት ተፅዕኖዎችን የሚዳስስ ሰነድ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እየቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮይሻ የውሃ ኃ/ማ/ፕሮጀክት (Civil engineer I) ሲቪል መሐንዲስ I (ፒአር1) ፣ (Geologist I) ጂኦሎጂስት
+5
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮይሻ የውሃ ኃ/ማ/ፕሮጀክት (Civil engineer I) ሲቪል መሐንዲስ I (ፒአር1) ፣ (Geologist I) ጂኦሎጂስት I (ፒአር1) እና (Geothechnical Lab Technician I) ጂኦቴክኒካል ላብ ቴክኒሻን I (ኤስፒ 1) የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 10 ቀን 2018ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾች ረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

በሳይንሳዊ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ የአመጋገብ ሥርዓት ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ….///…. ወላጆች ለልጆቻቸው በሳይንሳዊ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ የአመጋገብ ሥርዓት ተግባራዊ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጤና አገልግሎት ቢሮ አሳሰበ፡፡ ቢሮው ከፍቅረ ሠላም አጠቃላይ ሆሰፒታል ጋር በመተባበር በተቋሙ የህፃናት ማቆያ ማዕከል ለሚገለገሉ ወላጆች በህጻናት አመጋገብ ሥርዓት ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ የተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሰረት ሙሉጌታ እንደገለፁት ተቋሙ የህፃናት ማቆያ ማዕከል በመክፈት የሠራተኞችን ልጆች ከመከባባከብ በተጓዳኝ ሠራተኞች የቅድመ ወሊድ ክትትልና የወሊድ ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ ነው፡፡ ወላጆች ለልጆቻቸው በሳይንሳዊ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ የአመጋገብ ሥርዓት ተግባራዊ ማድረጋቸው ልጆቻቸው ከእድሜያቸው ጋር የተስተካከለ ቁመት፣ ከብደትና የአዕምሮ እድገት እንዲኖራቸው ያስችላል፡፡  ወላጆችም በሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት በመጠቀም ልጆቻቸው በተገቢው አዕምሮአዊ እና አካለዊ እድገት እንዲጠብቁ በማድረግ ሀገራቸውን የሚጠቅሙ ብቁና ጤናማ ዜጋን በማፍራት በኩል ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ሥራ አስኪያጇ አስገንዝበዋል፡፡ በፍቅረሰላም አጠቃላይ ሆሰፒታል የህጻናት ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ገሊላ ግርማ በበኩላቸው የቅድመ ወሊድ ክትትል እስከ ድህረ ወሊድ ለህጻናቱ አካለዊ እና አእምሮአዊ እድገት ወሳኝ የሆኑ አንድ ሺህ ቀናት እንዳሉ አመልክተዋል፡፡ ወላጆች በዕውቀት ላይ በተመሰረተ የአመጋገብ ሥርዓትን በመተግበር ከእርግዝና እስከ ሁለት ዓመት ባሉት አንድ ሺህ ቀናት ብቻ እስከ 18 ዓመታቸው ድረስ የሚጠቅማቸውን 80 በመቶ አዕምሮአዊ እድገት ማሳካት እንደሚችሉ አስረድተዋል፡፡ ከሥልጠናው መጠናቀቅ በኋላ በህፃናት ማቆያ ማዕከሉ የሚገኙትን ህጻናት ከእድሜቸው ጋር የተስተካከለ ክብደትና አካላዊ ቁመና ያላቸው መሆኑን የማረጋገጥ ምልከታ ተከናውኗል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

በተቋሙ የብቃት ምዘናን ከወረቀት ንኪኪ ነጻ ለማድረግ እየተሰራ ነው …….///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብቃት ምዘና የአሰራር ሥርዓትን ከወረቀት ንኪኪ ነጻ ለማድረግ ያበለጸገውን መተግበሪያ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በበለፀገው መተግበሪያ ላይ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ባደረጉት ውይይት ላይ የዘርፉ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደተናሩት መተግበሪያው በተቋሙ በወረቀት እየተከናወኑ የሚገኙ የዕድገት፣ የዝውውር ፣የሥልጠና እና የቅጥር ሂደቶችን በወረቀት አልባ አሰራር ሥርዓት ለመቀየር ያስችላል፡፡ መተግበሪያው ተገልጋዩ ባለበት ሆኖ ፈተናውን ለመሰውድ እንደሚያስችለው እና በተቋሙ የተጀመረውን ወረቀት አልባ አሰራር በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል፡፡ ከሁሉም የሥራ ክፍሎች የፈተና ባንክ (Exam Bank) ማዘጋጀት፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግብዓቶችን ማመቻቸት፣ የፈተና ማዕከላትን ማደራጀት፣ የተለያዩ ፖለሲ እና መመሪያዎችን ማሻሻልና ማዘጋጀት እንዲሁም የአሰልጣኞች ሥልጠና የመስጠት ሥራዎች በቀጣይ በትኩረት እንደሚከናወኑ አስረድተዋል፡፡ የተቋሙ የሰው ሀብት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው እየተተገበረ የሚገኘው የብቃት ምዘና ፈተና አሰጣጥ ሥርዓት የሚስጥራዊነት ጥያቄ የሚነሳበት፣ ፈተናው በእጅ የሚታረም በመሆኑ ጊዜ የሚወስድ እና ተቋሙን ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጣ እንዲሁም ሠራተኛውን ለእንግልት የሚዳርግ ነው ብለዋል፡፡ መተግበሪያው በሥራ ላይ ሲውል ከፈተና ጋር ተያይዞ በሠራተኞች የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥቄዎችን የሚቀርፍ፣ የፈተና ጥራትን የሚያሻሽል እና ወጪ በመቆጠብ የሥራ ቅልጥፍናን የሚያሳድግ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ በወይይቱ ላይ ከዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ፣ ከኢትዮ ፓወር አካዳሚ፣ ከፖሊሲ፣ ፕሮሰስ እና የለውጥ ሥራ አመራር እንዲሁም የሠራተኛ ማህበርን ጨምሮ የተለያዩ የዘርፍ የሰው ኃይል ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ መተግበሪያውን ያበለጸጉት የጀነሬሽን ቢዚነስ ዘርፍ ባለሙያዎች ስለመተግበሪያው ገለፃ ያቀረቡ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱት ጥቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ኢትዮጵያ እምቅ የታዳሽ ኃይል ባለቤት መሆኗ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ ላይ መነቃቃትን ፈጥሯል ‎…....///….... ‎ኢትዮጵያ እምቅ የታዳሽ ኃይል ባለቤት መሆኗ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍ ላይ መነቃቃት መፍጠሩን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ። ‎ "በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ሥርዓትን ማረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀውን “ አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ 2025” የተሰኘ የአፍሪካ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንት አስመልክቶ በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ የተመራ የልዑካን ቡድን በአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አህጉራዊ ሁነቱን የማስዋወቅ ሥራ አከናውኗል። ‎የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ በርሆ ሐሰን እንደተናገሩት “አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ 2025” የተሰኘውን ኹነት በአዳማ አንድ የንፋስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለማስተዋወቅ የታሰበው ኢትዮጵያ አማራጭ የታዳሽ ኃይል አቅርቦት ያላት ሀገር መሆኗን ለማሳየት ነው። ‎ኢትዮጵያ በአፍሪካ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ እና የታዳሽ ኃይል ስብጥርን ለማመጣጠን ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኗን በኤሌክትሪክ የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ኩባንያዎች እና ባለድርሻ አካላት ለማስገንዘብ እንደሚረዳ ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ በርሆ ገለፃ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ እንደ ሀገር ለልማት እና ዕድገት ቁርጠኛ መሆናችንን ያሳየ ነው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅን ተከትሎም የተለያዩ ሀገራት ኩባንያዎች የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን እያቀረቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ለማምረት የሚያስችል የተፈጥሮ ማዕድናት ያላት መሆኗን የጠቀሱት አቶ በርሆ ይህን እምቅ አቅም ለመጠቀም የተለያዩ ግዙፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራች ኩባንያዎች በዘርፉ ለመሰማራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውንም ነው ያብራሩት። እንደ ሚኒስትር ደኤታው ገለፃ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ዘርፍን በፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመደገፍ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነች ነው። ‎በአህጉራዊ ኹነቱ ላይ የተለያዩ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና በትራንስፖርት ዘርፉ የተሰማሩ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልፀዋል። ‎በኬንያ ፓወር የኤሌክትሪክ ትራንስፖርት ዘርፍ ባለሙያ የሆኑት ሚስተር ኢያን ኪፕሩቶ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል መሆኗን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያ ለኬንያ ቀዳሚ የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጭ እየሆነች መምጣቷን የጠቀሱት ባለሙያው ታንዛኒያም የዚህ የኃይል ትስስር አካል መሆን መጀመሯን ተናግረዋል። ‎አህጉራዊ ኹነቱን አስመልክቶ ከናይሮቢ- አዲስ አበባ የ1 ሺህ 600 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ መኪና ጉዞ ማድረጋቸውን የጠቀሱት ሚስተር ኢያን ጉዞው በኤሌክትሪክ መኪናዎች አማካኝነት ቀጣናዊ የትራንስፖርት ሥርዓትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

#vacancy ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደብ መጠሪያ፡ ሹፌር 1ኛ - (ጂኤስ6) ✍️ አመልካቾች ዋናውን የትምህርት፣ የመንጃ ፈቃድ እና የስራ ልምድ ማስረጃ ከማይመለስ ኮፒ ጋር በመያዝ ኮተ
#vacancy ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደብ መጠሪያ፡ ሹፌር 1ኛ - (ጂኤስ6) ✍️ አመልካቾች ዋናውን የትምህርት፣ የመንጃ ፈቃድ እና የስራ ልምድ ማስረጃ ከማይመለስ ኮፒ ጋር በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት በአካል በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እገልጻለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የሰንደቅ ዓላማ ቀን ስናከብር ሀገራዊ ብልጽግናችንን እና አንድነታችንን በማጠናከር ሊሆን ይገባል -ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ---///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር ሀገርዊ ዕድገትን ፣ህብረት፣ ብልፅግና እና አንድነትን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን ይገባል ሲሉ የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ  ኢንጂነር  አሸብር ባልቻ ገለፁ፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ”በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት አክብረዋል፡፡ በበዓሉ ላይ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት የዘንድሮውን ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን ለየት የሚያደረገው የዳግማዊ አደዋ ተምሳሌት የሆነውን የታላቁ ህዳሴ ፕሮጀክት ግድብ ያጋጠሙትን እጅግ ውስብስብ የግንባታ ሂደቶችንና ችግሮችን በብቃት ተወጥተን በይፋ ማስመረቅ በቻልንበት ማግስት መሆኑ ነው፡፡ ይህን ሰንደቅ ዓለማ ብዙ መስዋትነት ከፍለው እዚህ እንዲደርስ ላደረጉ አባቶቻችን ክብርና ሞገስ እንደምንሰጥ ሁሉ  የታለቁን ህዳሴ ፕሮጀከት ግንባታ መስዋዕትነት ከፍለው በድል እንዲጠናቀቅ ላበቁ ወንድሞቻችንም ክብር እንሰጣለን  ብለዋል፡፡ በቀጣይም ከፊት ለፊታችን ያሉትን ታላላቅ ሀገራዊ ስራዎቻችንን በጥልቅ ሀገራዊ ስሜት፣ አንድነትና ህብረት በመፈፈፀም የሀገራችንን ዕድገትና ብልፅግና ለማስቀጠል ተባብረን መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በዓሉን በተቋሙ ዋና መ/ቤት ያሉ የተቋሙ አመራርና፣ ሠራተኞች እና የፌደራል ፖሊስ አባላት በጋራ አክብረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዛሬው ዕለት በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ኹነቶች ይከበራል፡፡ ቀኑ “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የሚከበረው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት መሰረት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት እና በሰንደቅ ዓላው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ምንድን ነው? 1. አረንጓዴው ቀለም፡- የሥራ፣ የልምላሜና የዕድገት ምልክት ነው፡፡ 2. ቢጫው ቀለም፡- የተስፋ፣ የፍትሕና የእኩልነት ምልክት ነው፡፡ 3. ቀዩ ቀለም ፡- ለነፃነትና ለእኩልነት መስፈን የሚደረግ የመስዋዕትነትና የጀግንነት ምልክት ነው፡፡ እንዲሁም በሰንደቅ ዓላማው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ከታች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ 1. ክብ የሆነው፡- ሰማያዊ መደብ ሰላምን ያመለክታል፡፡ 2. ቀጥታና እኩል የሆኑት መስመሮች፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የሐይማኖቶችን እኩልነት ያመለክታሉ፡፡ 3. ቀጥታና እኩል ከሆኑት መስመሮች የተዋቀረው ኮከብ፡- የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በመፈቃቀድ የመሠረቱትን አንድነት ያመላክታል፡፡ 4. ቢጫ ጨረሩ ደግሞ ፡- በመፈቃቀድ አንድነት ለመሰረቱት ብሔር፣ ብሔረሰቦች የፈነጠቀውን ብሩህ ተስፋ ይጠቁማል፡፡ ምንጭ:- የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

"ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!" 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስ
"ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!" 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጤት ማስታወቂያ በአይቲ ኦፕሬሽን የስፖርት ስራ መሪ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.m
+1
የውጤት ማስታወቂያ በአይቲ ኦፕሬሽን የስፖርት ስራ መሪ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም