es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 533 suscriptores, ocupando la posición 8 338 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 162 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 533 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 6, y en las últimas 24 horas de -1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.10%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.85% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 901 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 619 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 8.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 533
Suscriptores
-124 horas
-167 días
+630 días
Archivo de publicaciones
photo content
+1

በዞኑ የሚገኙ የኤሌትሪክ መሰረተ ልማቶችን በባለቤትነት እንደሚጠብቅ የዞኑ አስተዳደር አረጋገጠ ........///........ በደቡብ ክልል ጋሞ ዞኑ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከስርቆት ለመከላከል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የዞኑ አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ በርገኔ በቀለ እንደገለጹት የጋሞ ዞን ጉልህ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉበት፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ግንባታቸው የተጀመረ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሚገኙበት አካባቢ ነው። በመሆኑም በዞኑ በተለይም በአርባምንጭ ከተማና በዙሪያዋ በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ሲፈጸሙ የነበሩ የስርቆት ወንጀሎች በተቋሙ፣ በአስተዳደሩ እና በአካባቢው ማህበረሰብ የጋራ ርብርብ ማስቀረት መቻሉን አማካሪው አስታውሰዋል። የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በሚያልፉበት ኮሪደር ተቋሙ ተገቢውን ካሳ ከፍሎ ወሰኑን ቢያስከብርም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በህገ ወጥ መንገድ መልሰው ግለሰቦች መስፈራቸው አግባብ እንዳልሆነ አማካሪው አስረድተዋል። ከካሳ ክፍያና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት በማካሄድና ግንዛቤ በመፍጠር ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት በትኩረት እንደሚሰራ ልዩ አማካሪው አረጋግጠዋል። የዞኑ ኢንቨስመንትና ኢንዱስትሪ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ግርማ በበኩላቸው ዞኑን ላይ ኢንቨስት ማደረግ የሚፈልጉ ባለሀብቶች ከሚጠይቋቸው ቅድመ ሁኔታዎች መካከል አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖሩን እንደሆነ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገነባቸው አዳዲስና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች በአካባቢው ለታቀዱ የኢንዱስትሪ ፓርክና የፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችሉ ኃላፊው ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በዞኑ በግብርና፣ በአገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ከ240 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች አስተማማኝ ኃይል እያገኙ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው በእነዚህ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የሥርቆት ወንጀሎችን ከተቋሙ ጋር በመሆን ለመከላከል መምሪያቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በተከናወነለት የማስፋፊያ ሥራ የህብረተሰቡን ጥያቄ በሚገባ መልሷል ........///......... የአርባምንጭ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በተለያዩ ጊዜያት በተደረጉለት የማስፋፊያና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች በከተማዋና በአካባቢው ማህበረሰብ ሲነሱ የቆዩትን የኃይል እጥረትና መቆራረጥ ችግር በአግባቡ መፍታቱን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ጉዳዩ ምትኩ እንደገለጹት ጣቢያው በዲዝል ጀነሬተር አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች ተሰርተውለታል። ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር 2 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማቅረብ አቅም የነበረው በመሆኑ የአርባምንጭ ከተማና የጋሞ ዞንን ዕድገት ተከትሎ እያደገ ለመጣው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የማይችልበት ሁኔታ ተፈጥሮ እንደነበር ኃላፊው አስታውሰዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በጣቢያው ላይ የተከናወኑት የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች ኃይል የመጫን አቅሙን ወደ 49 ሜጋ ዋት ከፍ እንዲል አድርጎታል። በአሁኑ ወቅት ጣቢያው መስጠት ከሚችለው 49 ሜጋ ዋት ኃይል ውስጥ በአማካይ እስከ 16 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ኃላፊው ጠቅሰዋል ። ማከፋፈያ ጣቢያው ባለ 15 ኪሎ ቮልት ስድስት ወጪ መስመሮች ለከተማዋ ነዋሪዎች፣ ለአርባምንጭ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ፣ ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲና ኮሌጆች እንዲሁም ለዱቄት ፋብሪካዎች ኃይል ሲሰጥ በ33 ኪሎ ቮልት ባሉት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ ለኮንሶና አካባቢው ፣ለከንባ፣ቦረዳና ብርብር ወረዳዎች አስተማማኝ ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው አሁን ላይ የሚመጡ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎችን ማስተናገድ የሚችል 32 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ተጨማሪ አቅም እንዳለው ኃላፊው ገልጸዋል። በጣቢያው ላይ የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች በቀጣይም እንደሚሰሩ የገለጹት ኃላፊው ጣቢያውን ከብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጋር ለማገናኘት ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስፋፊያ ሥራ በቅርቡ አንደሚጀመር ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ግሪዱን ማዘመን የሚያስችል ፍኖተ ካርታ እየተዘጋጀ ነው ........///........ ብሔራዊ የኃይል ግሪድን ለማዘመን የሚያስችሉ የፍኖተ ካርታ ዝግጅትና የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን እና አቅም ማሻሻል መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ገ/እግዚአብሔር እንዳስታወቁት በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያሉ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን የማዘመንና የቴክኒክ ድጋፎችን የመስጠት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የፍኖተ ካርታ ዝግጅቱ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን እና ሠራተኛው ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀም እንደሚያግዝ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የፍኖተ ካርታ ዝግጅቱ በመጠናቀቅ ላይ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ የቴክኒክ ድጋፉ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚከናወኑ የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራዎች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓትን የተከተሉ እንዲሆኑ ያግዛል ብለዋል። እንደ አቶ ዳዊት ገለፃ ግሪዱን ለማዘመን እየተከናወነ ባለው ሥራ ላይ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እየሰሩ የሚገኙ ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን ታቅዷል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያግዙ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን የመትከል፣ በአግባቡ መስራታቸውን የመከታተልና የመገምገም እንዲሁም የትራንስፎርመር ዘይቶችን የመፈተሽ ሥራዎች እንደሚሰሩም ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። በቴክኒክ ድጋፍ ሥራው በሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የማዘመን ሥራዎች እንደሚከናወኑ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የተቋሙ ሥራ አመራር የልምድ ልውውጦችንና ተሞክሮዎችን እንዲያገኙ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት እንደሚዘረጋም ጠቁመዋል። የፍኖተ ካርታ ዝግጅቱና የቴክኒክ እገዛ ሥራው ከፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ በተገኘ  የ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ውስጥ 4 መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላሩ  ለግሪድ ፍኖተ ካርታ ዝግጅት እንዲሁም 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላሩ ደግሞ በሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተግባራዊ ለሚደረግ የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች የሚውል ነው ተብሏል። የፍኖተ ካርታ ዝግጅትና የቴክኒክ ድጋፍ ሥራው አር ቲ ኢ ኢንተርናሽናል (RTE International) በተሰኘ የፈረንሳይ ኩባንያ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ እና ሥራዎች ሲጠናቀቁም ችግር ፈቺ ግብዓቶች ይገኙበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ዳዊት አስታውቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በስርቆት ምክንያት የተቋረጠውን የኃይል አቅርቦት ለመመለስ ጥረቶች ተጀምረዋል ………////………. ከመንዲ አሶሳ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሙሉ በሙሉ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡ በክልሉ መንደር 48 በተለምዶ አንበሳ ጫካ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ በተፈፀመ ስርቆት መስመሩን የሚሸከሙ ሁለት የብረት ምሰሶዎች ወይም ታወሮች ወድቀዋል፡፡ በዚሁ የተነሳ ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መዲና አሶሳ ከተማ እና የአሶሳ ዞን ወረዳዎች በሙሉ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል። ከዚህ በፊትም በክልሉ ባምባሲ በተባለ አካባቢ በሥርቆት የተነሳ ኃይል ተቋርጦ የነበረ ሲሆን አሁን ለኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆነው አካባቢ ከአሶሳ ከተማ ወደ 30 ያህል ኪሎ ሜትሮች ርቀት እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የወደቁ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶዎች ለመተካት ጥረቶች የተጀመሩ ሲሆን ጥገናውን አጠናቆ ለአካባቢዎቹ ኃይል ለመስጠት እስከ ሦስት ቀን ድረስ ሊወስድ ይችላል፡፡ የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶችን መጠበቅ በየደረጃው ያሉ የሁሉም መስተዳድር አካላት ኃላፊነት በመሆኑ የመስተዳድር አካላቱ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ እያደረግን ጥገናው ተጠናቆ ወደአገልግሎት እስኪመለስ ድረስ ህብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቀን እንጠይቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ……...///…..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጠት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋሙ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ክትትል ኮሚቴ አስታወቀ። ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በደቡብ ኦሞ ዞን ባሉ አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ የተነሳ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ያደረገውን የአስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታና ድጋፍ ሥርጭት አፈፃፀም ኮሚቴው ያካሄደውን የመስክ ምልከታ አጠናቋል። የኮሚቴው ሰብሳቢ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለፁት ተቋሙ በአራቱ ወረዳዎች ያደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የነዋሪዎቹን ወቅታዊ ችግር ታሳቢ ያደረገ ነው። የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱን ያከናወነው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዘርፉ ልምድ ያለው ተቋም መሆኑን ያሳየበት በመሆኑ በወቅቱ ድጋፉ ለተጠቃሚዎቹ እንዲደርስ አድርጓል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ለሥርጭቱ መሳካት የተቋሙ፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም የጎሳ መሪዎችና የማህበረሰብ ተወካዮች የነበራቸው አስተዋጽኦ የጎላ ነው። የኮሚቴው አባል ወ/ሪት ሜሮን ዮሐንስ በበኩላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ በአራቱ ወረዳዎች የሚኖሩ እናቶች፣ ህፃናት እና አቅመ ደካሞች ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። ተቋሙ በመንግሥት ከተሰጠው ተልዕኮ ባሻገር በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ችግር ላይ ለወደቁ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ በማድረግ የህዝብ ተቋም መሆኑን አስመስክሯል ያሉት ደግሞ የኮሜቴው አባል አቶ ዋለ ታምሬ ናቸው። በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አማካኝነት በወረዳዎቹ የተከናወነውን የሥርጭት ሥራ ተዟዙረው መመልከታቸውን ያነሱት አቶ ዋለ የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ የታለመለትን ዓላማ ማሳካቱን ተናግረዋል። እንደ አቶ ዋለ ገለፃ የእርዳታ ሥርጭት አፈፃፀሙን ተዟዙረው ከተመለከቱ በኋላ በአንዳንድ አካባቢዎች ከፀጥታና መሰል ችግሮች ጋር በተያያዘ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭቱ ላይ መጠነኛ ችግሮች እንደነበሩ መታዘባቸውን ገልፀዋል። ሌላው የኮሚቴው አባል አቶ ግዛቸው ደሳለኝ በበኩላቸው ተቋሙ በወረዳዎቹ ለሚገኙ አርብቶ አደሮች በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል። የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭቱ በአራቱ ወረዳዎች ለሚኖሩ አርብቶ አደሮች መደረጉ የተቋሙን መልካም ገፅታ ከመገንባት አንፃር አወንታዊ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል። በመስክ ምልከታው ወቅት በወረዳዎቹ ከሚገኙ አመራሮችና አርብቶ አደሮች ጋር በተደረጉ ውይይቶች በአካባቢው የሚስተዋሉትን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት ተቋሙ የማህበራዊ ልማት ጥናት ዕቅድ ለማዘጋጀት እንቅስቃሴዎች መጀመሩ ተገልጿል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም