es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 553 suscriptores, ocupando la posición 8 395 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 164 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 553 suscriptores.

Según los últimos datos del 22 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 5, y en las últimas 24 horas de 1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.99%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.38% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 043 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 393 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 23 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 553
Suscriptores
+124 horas
+47 días
+530 días
Archivo de publicaciones
በጣቢያው የተተከለው ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል .........///....... በአዳማ ቁጥር ሁለት የማከፋፈያ ጣቢያ የተተከለው ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በአዳማ የሚስተዋለው የኢንዱስትሪና የከተማ መስፋፋት የኃይል ፍላጎት እንዲጨምር አድርጓል። ማከፋፈያ ጣቢያው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ማስተናገድ የማይችልበት ደረጃ ላይ በመድረሱ የአቅም ማሳደግ ሥራ መስራት እንዳስፈለገ ተናግረዋል። ጣቢያው በ132/15 ኪሎ ቮልት አገልግሎት የሚሰጡ ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች እንደነበሩት ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። ለአዳማ ኢንደስትሪ ፓርክ በ33 ኪሎ ቮልት አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ተጨማሪ ትራንስፎርመር መተከሉን ገልፀዋል። በሪጅኑ በራስ አቅም የተከናወነው የትራንስፎርመ ማስቀመጥ ሥራ የጣቢያውን አቅም በ50 በመቶ ከማሳደግ ባለፈ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ያለ ተፈጥሮ ወንዝና ግድብ ከውሃ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሙከራ፤ .....///..... አንድ አሜሪካዊ ያለ ተፈጥሯዊ ወንዝ ወይም ግድብ የሚሰራ “ዝግ-ሉፕ” የተሰኘ የውሃ ኃይል ማመንጫን ሙከራ አድርጓል፡፡ ማመንጫው ተፈጥሯዊ ወንዝ ወይም ግድብ የሌለው ሲሆን የመሬት ስበትን፣ ከፍታን እና ጥቅም ላይ የዋለ ውሃን በመጠቀም በደረቃማና ግድብ በሌላቸው አካባቢዎች ጭምር የማያቋርጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ነው። ይህ ግኝት ከአሁን ቀደም የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ያልነበሩ አካባቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ተብሏል። ማመንጫው በቀን ውስጥ የፀሐይ ኃይልን ወይም የንፋስ ኃይልን በመጠቀም ውሃን ወደ ከፍተኛ ከፍታ ማጠራቀሚያ ቦታ በመውሰድ የሚሰራ ሲሆን ከፍተኛ ፍላጎት በሚኖርበት ወይም ፀሐይ በምትጠልቅበት ስዓት ደግሞ ውሃውን ወደ ታች በተርባይኖች በመልቀቅ እንደ ውሃ ኃይል ማመንጫዎች ኤሌክትሪክ ያመነጫል። ከዚያም ውሃው በታችኛው የተፋሰስ ቦታ ላይ ተሰብስቦ በፓምፖች አማካኝነት እንደገና ጥቅም ላይ እንዲውል የሚያስችል ሲሆን ኃይልን እንደ ባትሪ ማከማቸት እና ለግሪድ ፍላጎቶች ወዲያውኑ ምላሽ ለመስጠትም የሚረዳ ነው ተብሏል። ይህ ግኝት ብዙውን ጊዜ የጎርፍ አደጋን ከሚያስከትሉ፣ ነዋሪዎችን እና የዱር እንስሳትን ከሚያፈናቅሉ ግድቦች በተቃራኒ የአካባቢ ተጽዕኖ የሌለው፣ የተፈጥሮ ወንዞችን አቅጣጫ የማያስቀይር፣ በዓሳን ሀብት የተሰማሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የማይጎዳ እና ግዙፍ የግንባታ ሥራዎችን የማይፈልግ ነው። በተጨማሪም ማመንጫው በረሃን ጨምሮ ጥቅም ላይ ባልዋለ መሬት እና አነስተኛ የነዋሪ ቁጥር ባላቸው ቦታዎች በመገንባት በአካባቢው ያለውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት ያስችላል። ያለ ተፈጥሮ ወንዝና ግድብ ከውሃ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሙከራው በአሜሪካ በአሪዞና እና ኔቫዳ ግዛቶች ተሞክሮ ከ80 በመቶ በላይ ውጤታማ በመሆን ከሊቲየም ባትሪዎች እኩል አቅም እንዳለው ተረጋግጧል። ግኝቱ ግዙፍ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ ሳይፈልግ እና ጥቅም ላይ የዋለ ውሃን በመጠቀም ታዳሽ ኢነርጅን ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ማከፋፈያ ጣቢያዉ የአካባቢዉን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ እየሰራ ነዉ ………///…….. የቱለፋ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢዉ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች እና ለነዋሪዎች የኃይል ፍላጎት ተደራሸ ለማደረግ እየሰራ መሆኑን የጣቢያዉ ኃላፊ አስታወቁ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ አዲሱ ከፍአለ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዉ በአካባቢዉ ያለዉን የኢንቨስትመንት ፍሰት መሰረት አድርጎ በ2012 ዓ.ም ወደ ሥራ መግባቱን ገልፀዋል። ጣቢያዉ በ132 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል የመሸከም አቅም ባለው ትራንስፎርመር አማካኝንት ለቡልጋ ከተማ፣ አሌልቱ፣ ጨፌ ዶንሳ፣ ሰንዳፋ እና ሸኖ ከተሞችና አካባቢያቸው ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ አዲሱ ተናግረዋል።  እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያው በአካባቢው ያለውን የኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎት መሰረት አድርጎ የተቋቋመ በመሆኑ በቡልጋ ከተማ መስተዳድር እና አካባቢዉ የተሰማሩ 59 ፋብሪካዎችን የኃይል ተጠቃሚ ማደረግ ችሏል። በሌላ በኩል ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያዉ በደብረ ብርሃን ቁጥር ሁለት እና ለገጣፎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል ላይ በመገኘቱ የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥም በቅንጀት በመስራት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መቻሉንም አክለዋል። በአካባቢዉ የሚስተዋለውን የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የማከፋፈያ ጣቢያ ለመገንባት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ተንቀሳቃሸ ማከፋፈያ ጣቢያው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል …..…///…..… የገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቅርቡ ወደ ሥራ ያስገባዉ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩን የጣቢያዉ ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊዋ ወ/ሮ አበበች ሸዋለም እንደገለፁት ጣቢያው በ230 ኪሎ ቮልት ከፊንጫ፣ ጌዶ 1 እና 2፣ ሰበታ፣ ሱሉልታ እና ሸጎሌ በስድስት ገቢ መስመሮች ኃይል ያገኛል፡፡ ጣቢያዉ በሁለት ባለ 50 እና ሁለት ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ፓወር ትራንስፎርመሮች ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀዋል። እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በቅርቡ ወደ ሥራ የገባው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በ15 ኪሎ ቮልት በገፈርሳ ዙሪያ ለሚገኙት አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ኃላፊዋ ተናገረዋል። እንደ ኃላፊዋ ገለፃ ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያው በዙሪያው ያሉ ግለሰብ የኃይል ተጠቃሚ እና የንግድ ቤት ደንበኞችን ጨምሮ በዙሪያው የሚገኙ ከ400 በላይ ትንንሽና ትልልቅ አምራች ኢንደስትሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በአካባቢዉ ለተሰማሩ የኢንቨስትመት ዘርፎች በበቂ ሁኔታ ኃይል እየቀረበ ነዉ .....…///…..… በቡራዩ ከተማ እና አካባቢው የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎትን ያገናዘበ በቂ አቅርቦት መኖሩን የከተማው ምክትል ከንቲባ አስታወቁ። ምክትል ከንቲባው አቶ ሽብሩ ዓለሙ እንደተናገሩት በቡራዩ ከተማ እና አካባቢዉ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ 356 ባለሀብቶች መካከል 276ቱ ወደ ምርት የገቡ ሲሆን 86ቱ ሥራ ለመጀመር በሂደት ላይ ናቸዉ፡፡  የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ መስፋፋት የማይተካ ሚና እንዳለው የጠቀሱት ምክትል ከንቲባው አቶ ሽብሩ ከተማዋ ለኢንደስትሪ ተመራጭ በመሆኗ ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልጋት ጠቁመዋል። 60 ዓመታት ያስቆጠረው የገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅሙን በማሳደግ ያከናወናቸዉ ተግባራት እያደገ የመጣዉን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ አስችሎታል ብለዋል።  በቡራዩ ከተማ እና አካባቢዉ ለሚገኙ ከ270 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት ተደራሽ በማድረግ ለበርካታ የአካባቢዉ  ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ምክትል ከንቲባው አመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ስለ ገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጥቂት እውነታዎች 📌     በ1954 ዓ.ም. ግንባታዉ ተጀምሮ በ1958 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ 📌     ከፊንጫ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ230 ኪሎ ቮልት መስመር ኃይል ተቀብሎ ለአስኮ እና አካባቢዉ እንዲሁም ለአዲስ ዓለም እና ፍቼ ከተሞች ኤሌክትሪከ በማቅረብ ነው ሥራ የጀመረው፡፡ 📌     በማዕከላዊ 1 ሪጅን ከሚገኙት 21 ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል አንጋፋ ጣቢያ ነው፡፡ 📌     በአሁኑ ወቅት በ230 ኪሎ ቮልት ከፊንጫ፣ ጌዶ 1 እና 2 ፣ ሰበታ፣ ሱሉልታ እና ሽጎሌ ኃይል ተቀብሎ በ132 ኪሎ ቮልት 4 ወጪ መስመር፣ በ15 ኪሎ ቮልት 20 ወጪ መስመር፣ በ45 ኪሎ ቮልት አንድ ወጪ መስመር እንዲሁም በ66 ኪሎ ቮልት አንድ ወጪ መስመር በአጠቃላይ በ26 ወጪ መስመሮች ኃይል እየሰጠ ይገኛል። 📌     ጣቢያው ከአንድ ማመንጫ ጣቢያ ኃይል በመቀበል በአንድ አዉቶ ትራንስፎርመር እና አንድ ፓወር ትራንስፎርመር ኃይል ሲያከፋፍል ቆይቷል፤ በአሁኑ ወቅት አቅሙን በማሳድግ  500 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል የመሸከም አቅም ፈጥሯል፡፡ 📌     ትራንስፎርመሮቹ  በ230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀበለዉ በ132 ኪሎ ቮልት ኃይል ሊሰጡ የሚችሉ 4 አዉቶ ትራንስፎርመሮች እንዲሁም በ132 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን የሚያስተናግዱ 4 ፓወር ትራንስፎርመሮች ናቸው፡፡ 📌     የሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን እና ጥገና ኃላፊ አቶ ጌትነት ተስፋዬ ጣቢያው የደንበኞቹን የኃይል ፍላጎትን ለማሟላት ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን እያሳደገ መምጣቱን ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን መፈተሽ ያስፈልጋሉ ……..///…….. ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን መፈተሸ እንደሚገባ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዎን ጤሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። አፍሪ-ራን በተሰኘው እና ምክንያታዊ የናይል ወንዝ አጠቃቀም እና ቀጣናዊ ውህደት በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ምክክሩ በአካባቢው ትብብርን ለማጠናከር ጥሩ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል። ለዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማት፣ ለሥራ ፈጠራ እና ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አስተማማኝ እና ፍትሃዊ የኃይል አቅርቦት መሰረት ሆኖ ማገልገል አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ይህንን ለማሳካት የጋራ መሰረተ ልማት፣ የተጣጣሙ ፖሊሲዎች እና ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ንግድ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳን እቅዶች ለማሳካት ወሳኝ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአፍሪካ ሚሊየኖች የኤሌክትሪክ አገልግሎት የማያገኙ በመሆናቸው ቤቶች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ፣ ኢኮኖሚን ለማነቃቃት እና ወጣቶችን ወደ ሥራ ለማሰማራት የጋራ ፍላጎትን ማሰባሰብ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋትና  ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለማጠናከር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮች እንደሚያስፈልጉ ገልጸዋል። አፍሪራን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም መርህ የናይል ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ገዢ መርህ በማድረግ በናይል ወንዝ ፍትሐዊነት ማረጋገጥ እንዲቻል ዓላማ ይዞ የተቋቋመ ዓመታዊ ቀጣናዊ ኮንፈረንስ  ሲሆን ዘንድሮ በዋናነት ትኩረቱን የመንግሰትና የግል ሴክተር ትብብር የፋይናንስ ምንጮች ላይ አድርጎ መክሯል። "ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለአካታችና ዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

esti check afirgew

ቀጠናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን መፈተሽ ያስፈልጋሉ ……..///…….. ቀጠናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን መፈተሸ እንደሚገባ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዎን ጤሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። አፍሪ-ራን በተሰኘው እና ምክንያታዊ የናይል ወንዝ አጠቃቀም እና ቀጣናዊ ውህደት በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ምክክሩ በአካባቢው ትብብርን ለማጠናከር ጥሩ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል። ለዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማት፣ ለሥራ ፈጠራ እና ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አስተማማኝ እና ፍትሃዊ የኃይል አቅርቦት መሰረት ሆኖ ማገልገል አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ይህንን ለማሳካት የጋራ መሰረተ ልማት፣ የተጣጣሙ ፖሊሲዎች እና ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ንግድ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳን እቅዶች ለማሳካት ወሳኝ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአፍሪካ ሚሊየኖች ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጪ በመሆናቸው ቤቶች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ፣ ኢኮኖሚን ለማነቃቃት እና ወጣቶችን ለማነቃቃት የጋራ ፍላጎትን ማሰባሰብ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። በተጨማሪም ቀጠናዊ የኃይል ትስስር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን እንደሚፈልግ ገልጸዋል። አፍሪራን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም መርህ የናይል ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ገዢ መርህ በማድረግ በናይል ወንዝ ፍትሐዊነት ማረጋገጥ እንዲቻል አላማ ይዞ የተቋቋመ አመታዊ ቀጣናዊ ኮንፈረንስ ሲሆን በዚህ አመት በዋናነት ትኩረቱን የመንግሰትና የግል ሴክተር ትብብር የፋይናንስ ምንጮች ላይ መክሯል። "ቀጠናዊ የኃይል ትስስር ለአካታችና ዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

photo content
+4

በአካባቢው ያለውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ለመመለስ በቅንጅት እየተሰራ ነው …...///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቢሾፍቱ ከተማና አካባቢው ያለውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡ በተቋሙ የቢሾፍቱ ቁጥር ሦስት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ አይቼው እንደገለፁት ቢሾፍቱ ከፍተኛ የኃይል አቅርቦትን የሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎችና የቱሪስት መዳረሻዎች ያሉባት ከተማ ናት። ማከፋፈያ ጣቢያው ከገላን ማከፋፈያ ጣቢያ በባለ 400 ኪሎ ቮልት በጥምር መስመር ኃይል ተቀብሎ 400/230 ኪሎ ቮልት የሚቀይሩ 1200 ሜጋ ቮልት አምፔር ወይም 960 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች አሉት ብለዋል። ጣቢያው በ230 ኪሎ ቮልት በጥምር መስመር ለዱከም፣ ለቢሾፍቱ እና ለሞጆ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እያቀረበ ሲሆን ጣቢያው ካለው ከ960 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ውስጥ ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው 140 ሜጋ ዋት ብቻ መሆኑንም ገልፀዋል። ጣቢያው አገልግሎት መስጠት በጀመረበት ወቅት ለቢሾፍቱ ከተማና ኢንዱስትሪዎች ታስበው የተተከሉት 100 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመሮች ብቻ እንደነበሩት የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ በአካባቢው በ 33 ኪሎ ቮልት የኃይል ጥያቄ በመኖሩ 100 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ተጨማሪ ፓወር ትራንስፎርመሮች መተከላቸውን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት አስር ባለ 15 ኪሎ ቮልት እንዲሁም አስራ ሁለት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እንዳሉትና ከእነዚህም ውስጥ ዘጠኝ ባለ 15 ኪሎ ቮልት እና ስምንት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለከተማውና ለኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ቀሪዎቹ መስመሮች ደግሞ ለዳታ ማይኒግ ድርጅት ኃይል እያቀረቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ የጣቢያው ባለ 33 ኪሎ ቮልት ፖወር ትራንስፎርመር በሙሉ አቅሙ እየሰራ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሲሳይ ከፋብሪካዎችና ከኢንዱስትሪዎች የሚቀርበውን ተጨማሪ የኃይል ጥያቄ ተቀብሎ ለማስተናገድ መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡ በቢሾፍቱ ከተማና አካባቢው ከፍተኛ የኃይል አቅርቦትን የሚጠይቁ ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎች ፍሰት እየጨመረ በመምጣቱ የኃይል ፍላጎቱ የጣቢያው ግንባታና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ሲከናወኑ ይመጣል ተብሎ ከታሰበው በላይ በፍጥነት እያደገ መምጣቱን አብራርተዋል። ስለሆነም እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአግባቡ ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት ደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ዳምጠው በበኩላቸው የኃይል ብክነትን በቀነሰ መልኩ ለደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ በቢሾፍቱ ከተማ ከሚገኙት ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጋር ተቀናጅተው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአካባቢው ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ያለ በመሆኑ ይሄን ታሳቢ በማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ሊሰሩ እንደሚገባ አስታውሰዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ 1. ፋርማሲስት I 2. ፋርማሲስት II ✍️ አመልካቾች ዋናውን የትምህርት፣ የስራ ልምድ እና የታደሰ የስራ ፈቃድ /Licence/ ማስረጃ ከማይመለስ ኮፒ ጋር በመያዝ ኮተ
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ 1. ፋርማሲስት I 2. ፋርማሲስት II ✍️ አመልካቾች ዋናውን የትምህርት፣ የስራ ልምድ እና የታደሰ የስራ ፈቃድ /Licence/ ማስረጃ ከማይመለስ ኮፒ ጋር በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት በአካል በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እገልጻለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ……..///……. በአዳማና በሞጆ ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን በከተሞቹ በሚገኙ ፋብሪካዎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሆኑ ሠራተኞች ገለፁ፡፡ በአዳማ ከተማ በሚገኘው አብርሃም አበበ ፒፒ ከረጢት እና ፒፒሲ ኤች ዲፒ ፋብሪካ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሆኑት ወ/ሮ መሰለች ዓሊ ረመዳን እና ወ/ሮ አማከለች መኮንን እንደገለፁት በድርጅቱ በመቀጠር በሚያገኙት ገቢ ራሳቸውና ቤተሰቦቻቸውን እያስተዳደሩ ነው፡፡ ድርጅቱ ካሉት ከ110 በላይ ሠራተኞች አብዛኞቹ ሴቶች መሆናቸውን እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በአካባቢው በመኖሩ በርካታ ሴቶች በተከፈቱ ፋብሪካዎች ከቤተሰብ ሳይርቁ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ባይኖር ድርጅቱ ስለማይኖር የሥራ እድል ተጠቃሚ አንሆንም ነበር ያሉት ሠራተኞቹ ማህበረሰቡ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በእኔነት ስሜት መጠበቅ እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡ የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ አበበ ድርጅቱ ምርቶቹን ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ የሚያቀርብ በመሆኑ የኃይል አቅርቦት ለፋብሪካው የህልውና መሰረት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በሞጆ ከተማ በሚገኘው የሲ ኤንድ ኢ ወንድማማቾች ብረታ ብረት ፋብሪካ ሠራተኛ የሆኑት አቶ ሽመልስ ፍቃዱ እና አቶ ሻረው አለማየሁ በበኩላቸው በድርጅቱ ከአስር ዓመት በላይ መስራታቸውን ይናገራሉ፡፡   በፋብሪካው ከመቀጠራቸው በፊት ትምህርት ጨርሰው ያለሥራ ተቀምጠው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሽመልስ በድርጅቱ ሥራ ከጀመሩ በኋላ የትምህርት ደረጃቸውን ከዲፒሎማ ወደ ዲግሪ አሻሽለውና ዕድገት አግኝተው ትዳር በመመስረት ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከ680 በላይ ሠራተኛ በፋብሪካው በቀጥታ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት ባለሙያው በተዘዋዋሪ ግብዓት ለሚያቀርቡና የፋብሪካውን ምርት ለሚወስዱ በርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል፡፡ በአካባቢው ያለው የኃይል አቅርቦት የተሻለ በመሆኑ ብዛት ያላቸው ፋብሪካዎች እንደሚገኙ የጠቆሙት አቶ ሻረው ከሥራ ዕድል ፈጠራው በተጨማሪ የቴክኖሎጂ እና የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ማድረጉንም ገልፀዋል፡፡ የሞጆ ከተማ የሎጅስቲክስና የኢንዱስትሪ ማዕከል በመሆኗ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ ፋብሪካው የማስፋፊያ ሥራ እያከናወነ እንደሆነና ማስፋፊያው ሲጠናቀቅ ለበርካታ ዜጎች ተጨማሪ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም