EEP Communication
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication
تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 697 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 062 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 174 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 697 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 01 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 139، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 28.75%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.42% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 513 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 578 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“EEP Communication”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 02 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.
15 697
المشتركون
+124 ساعات
+277 أيام
+13930 أيام
أرشيف المشاركات
15 698
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች የአመራርነት ሥልጠና ሲሰጡ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፦
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለዘመናዊነት ቆርጠን መነሳታችን ማሳያ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምሰሶና የብሔራዊ አንድነት መገለጫ ነው።
💡 ግድቡ ኢትዮጵያውያን ማህበራዊ ስብራቶቻችንን በመጠገን በትናንት ብቻ የምንኮራና በዛሬ የምናፍር እንዳንሆን የሚያደርግ ታሪካዊ ድል ነው።
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአንድ ወገን የበላይነትን እና ለብቻ ተቆጣጥሮ የመጠቀም ፍላጎት እንዲያከትም በማድረግ በቀጠናው ፍትሐዊ የውሃ አጠቃቀም ሥርዓት እንዲዘረጋ ፈር የቀደደ ነው።
💡ግድቡ ኢንዱስትሪንና እና ዘመናዊ ግብርናን በማስፋፋት የማህበረ ኢኮኖሚ ዕድገት እንዲኖር ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሀገራዊ ውክልና/ National symbol/ እንዲሁም በማመንጨት አቅሙ የሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የማዕዘን ድንጋይ ነው።
💡ግድቡ የሚያመነጨውን ያህል ኢነርጂ ለማመንጨት ይወጣ የነበረን ወደ 2 ሚሊዮን ቶን ካርቦንዳይኦክሳይድ በማስቀረት ለዓለም ከባቢ አየር አወንታዊ አስዋጽኦ ያበረክታል።
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በዘመናት መካከል ግጥም እየገጠሙ ዘፈን እየዘፈኑ ቁጭታቸውንና አለመቻላቸውን በሚገልጹበት አባይ ላይ መገንባቱ የተለየ ትርጉም አለው።
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የማንሰራራት ትርክት፣የአንድነት፣የዘመናዊነት እና የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ኩራት መገለጫ ነው። ግድቡ ኢትዮጵያውያን የኢነርጂ ሉዓላዊነታቸውን ለማረጋገጥ ቁርጠኛ መሆናቸውን ማሳያ ጭምር ነው።
💡ኢትዮጵያ አፈሯን እየወሰደ እያየችው ምንም ማድረግ ላልቻለችውና ተቀምጣበት የእሷ መሆን ባልቻለው ሽፍታው አባይ ላይ ግድብ መገንባቷ፤ ኢትዮጵያውያን ተፈጥሮን በተለይም ውሃን መቆጣጠር አይችሉም፣ውሃ እያላቸው ውሃ የሚጠሙና የሚራቡ ህዝቦች ናቸው የሚለውን የጸና ትርክት አሽቀንጥሮ በመጣል የትውልድ የመቻል ማሳያ ነው።
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በላይኛውና በታችኛው ተፋሰስ ጸንቶ የቆየውን ታችኞቹ ይጠቀማሉ ላይኞቹ ውሃውን ይልካሉ የሚለውን ትርክት የበጣጠሰ ነው። በተለይም ውሃ እያላቸው መጠቀም ላልቻሉ የዓለም ህዝቦች የማንቂያ ደወል ነው።
💡የግድቡ መገንባት የናይል ተፋሰስ ሀገራት ጩኸት የቁራ ጩኸት ሆኖ ሰሚ እንዳያገኝ ሲደደረግ የነበረውን የዘመናት ሴራ በአፍ ጢሙ የደፋ ነው።
💡ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የኢንጂነሪንግ አቅም እንዲሁም የሀገሪቱ የፖሊሲ፣የኮሙዩኒኬሽን እና የዲፕሎማሲ ጥረት ትልቅ ማሳያ ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
የኢነርጂ ተደራሽነት ከሀገራዊ ብልጽግና ጋር ይያያዛል
.......///......
የኢነርጂ ተደራሽነት ከሀገራዊ ብልጽግና እና ተሰሚነት ጋር እንደሚያያዝ የአፍሪካ የአመራር ልቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ተናገሩ።
ፕሬዝዳንቱ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ እንደተናገሩት በኢነርጂ ዘርፍ የሚደረገው ሽግግር ወደ ሥልጣኔ የሚደረግ ሽግግር ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ወሳኝ ለውጦች በኢነርጂ ታግዘው የመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኃይል ቀውስ መከሰት የፖለቲካ አለመረጋጋት እንዲፈጠር እና መንግስታት እንዳይፀኑ ስለሚያደርግ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንስተዋል።
እንደ አቶ ዛዲግ ገለፃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግር የተቋሙ ችግር ብቻ ተደርጎ የሚወሰድ ባለመሆኑ ለውጥ በሚያመጣ መልኩ መስራት ያስፈልጋል።
የቀጣዩ ዘመን የኃይል ምንጭ ውሃ፣ ንፋስ፣ ነዳጅ ወይም ኢነርጂ ሳይሆን ርዕይ ነው ብለዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
“የህዳሴው ግድብ ከአንገት መድፋት ወደ ደረት መንፋት አሸጋግሮናል” ዛዲግ አብርሃ
.......///......
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከአንገት መድፋት ወደ ደረት መንፋት አሸጋግሮናል ሲሉ የአፍሪካ አመራት ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ።
ፕሬዝደንቱ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች በተቋሙ ዋና መ/ቤት የአመራርን ስልጠና ሲሰጡ እንደተናገሩት የህዳሴ ግድብ ከኃይል ማመንጫነት ባሻገር ለኢትዮጵያውያን ያለው ትርጉም የላቀ ነው።
“የህዳሴ ግድብ የሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የማዕዘን ድንጋይ ነው።” ያሉት አቶ ዛዲግ ግድቡ ለሀገር ከሚያስገኘው የኢኮኖሚ ጥቅም በላይ ለዓለም የከባቢ አየር ጥበቃ ድርሻው ጉልህ መሆኑን ተናግረዋል።
የውሃ ኃይል ግድቦች በሩቅ ምስራቋ ቻይና በዓለም የመጀመሪያው ሀገረ መንግስት ግንባታ እንዲጀመር መሰረት መሆናቸውን ጠቅሰው የሚመነጨው ኃይል ከኢኮኖሚ ጥቅም በላይ መሆኑን አሳይቷል ብለዋል።
አቶ ዛዲግ እንዳሉት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የብሄራዊ ኩራት ምንጭ በመሆኑ ግድቡ ከታሪካዊ ማንነታችን ጋር በጥብቅ በተሳሰረው የአባይ ወንዝ ላይ መገንባታችን ኩራቱን ከፍ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።
ግድቡ በሚያመነጨው ኃይል፣ በሚያስገኘው የውጭ ምንዛሪ እና በሚፈጥረው ትስስር ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት የወሳኝነት ሚና እንዲጎለብት የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል።
የአባይን ውሃ እንዳንጠቀም ብዙ ሴራ ቢሸረብብንም ያንን ሁሉ አልፈን የወሰንነው ውሳኔ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እርምጃ ነው ሲሉ የግድቡን የሉዐላዊነት መገለጫነት አስረድተዋል።
ግድቡ ኢትዮጵያ ልማቷን ለማረጋገጥ የምትሄደውን ረዥም ርቀት ያሳየም ነው ብለዋል።
ስለትውልዳዊ ቅብብሎሽ ሲያነሱም “ጀምሮ ያለመጨረስ ታሪካችን የሁል ጊዜም አለመሆኑን በህዳሴው ግድብ አረጋግጠናል” ሲሉ ተደምጠዋል።
ይህ ትውልድ ከአፄ ዳዊት ጀምሮ የነበረውን አባይን የመገደብ ህልም ከግብ ማድረስ የቻለ አኩሪ ትውልድ መሆኑን የተናገሩት አቶ ዛዲግ “የቀደመውን ትውልድ ህልም ተቀብሎ እውን የማድረግ ተግባር አስቀጥለን ለትውልድ ማስተላለፍ ከቻልን ኢትዮጵያን ለሁልጊዜም የታላላቅ ጅምሮች እና የታላላቅ ፍጻሜዎች ሀገር እናደርጋታለን” ሲሉ እምነታቸውን ገልጸዋል።
በኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ አቅም አውጥቶ መጠቀም እንደሚገባ የገለጹት ፕሬዝደንቱ ይህንን ለማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትልቁን ኃላፊነት እንደሚወስድ አስረድተዋል።
በመሆኑም የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ እያንዳንዱ ቤት የሚገባ በመሆኑ አፈጻጸሙ በሀገረ መንግስት ግንባታው ላይ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
“የኤሌክትሪክ ኃይልን ተጠቃሚነት ማሳደግ ኢትዮጵያ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ለምታደርገው ሽግግር ወሳኝ በመሆኑ ለኢኮኖሚያችን መዋቅራዊ ሽግግር መክፈቻ ቁልፉ መብራት ኃይል ጋር ነው ያለው ማለት ይቻላል” ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም ተቋሙ ወደ ውጪ ሀገራት በሚልከው ኢነርጂ ምክንያት የዲፕሎማሲ ሥራ እየሰራ ነው ሊባል እንደሚችል ጠቅሰዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
ለተቋሙ የሥራ መሪዎች በተቋም ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየተሰጠ ነው
........///.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር በአመራር እና የተቋም ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረ የሦስት ቀን ሥልጠና ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች መስጠት ጀመሯል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይና የጀነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ገብረ ኪዳን በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገሪቷ እና ለቀጣናው አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው።
አመራሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጣ እና የመፈጸም አቅሙ እንዲጎለብት ሥልጠና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
ስለሆነም አመራሩ ሥልጠናውን በንቃት በመከታተል የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል አቅም እንዲገነባ አሳስበዋል።
ሥልጠናው ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛዲግ አብርሃ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የመሪነት ሚና ላይ ያተኮረ ሥልጠና በመስጠት ላይ ናቸው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
ፕሮጀክቱ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የማህበራዊ ኃላፊነት ድጋፍ አደረገ
.......///......
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች እና ሠራተኞችን በማስተባበር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ከ600 ሺህ ብር በላይ የማህበራዊ ኃላፊነት ድጋፍ ማድረጉን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌቱ ያደታ እንዳስታወቁት በፕሮጀክቱ ዙሪያ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ውስጥ ለሚኖሩ 33 ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው አቅመ ደካሞች የስንዴ፣ ጤፍ፣ የኤሌክትሪክ ምጣድ፣ ዘይት እና የድንችድጋፍ ተደርጓል።
ድጋፉ ፕሮጀክቱ በኢተያ ወረዳ በዕቅድ ከሚያከናውናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች በተለየ በሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች እና ሠራተኞች በጎ ፈቃደኝነት ላይ ተመስርቶ የተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአካባቢው ማህበረሰብ ለፕሮጀክቱ ግንባታ መጠናቀቅ አወንታዊ አስተዋፅኦ በማበርከቱ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ለማህበረሰቡ ያላቸውን አጋርነት በተግባር ያሳዩበት እንደሆነም ነው ያብራሩት።
በቀጣይም መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው የዞንና የወረዳ መስተዳድር አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ሥራ አስኪያጁ አረጋግጠዋል።
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት 20 ተርባይኖችን ወደ ሥራ በማስገባት 69 ሜጋ ዋት ኃይል ወደ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ቋት በማስገባት ላይ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
+3
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ
......///......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 1ኛ እና በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ሰኔ 05 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም በፋርማሲስት 1ኛ እና በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተራ ቁጥር 1 (አንድ) ላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ከነሐሴ 09 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ እና የሙያ ፈቃድ (License) ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል
..…..///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት የመንግስት የልማት እና ኢነርጂ ፖሊሲዎችን ታሳቢ ያደረገ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ተቋሙ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብቻ በኃይል ማመንጨት ዘርፉ ላይ ያከናወናቸው ሥራዎች በ128 ዓመታት ከተከናወኑ ሥራዎች የ48 በመቶ ድርሻ አላቸው፡፡
ተቋሙ ባለፉት ስድስት ዓመታት ባከናወናቸው የግንባታ ሥራዎች ሀገራዊ የማመንጨት አቅሙን በ3 ሺህ 784 ሜጋ ዋት ማሳደግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት የፕሮጀክት አስተዳደር አቅምን በማሳደግ ተቋሙ ግንባታቸው የተጀመሩ የማመንጫ፣ የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን በመከታተል እና በመቆጣጠር እንዲሁም የተጠናቀቁትን ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን እና የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር የአይሻ፣ የኮይሻ እና የአሉቶ ጅኦተርማል ፕሪይም ፕሮጀክቶችን በመከታተልና በመቆጣጠር አፈፃፀማቸውን ለማሻሻል ዕቅድ ተይዞ ለተግባራዊነቱ እንቅስቃሴ መጀመሩን አብራርተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ፣ የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን፣ የባህር ዳር-ወልድያ- ኮምቦልቻ እና የአዋሽ-ወልዲያ የባቡር ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክቶችን ጨምሮ አስር የማስተላለፊያ መስመሮችን እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ግንባታ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት እንደሚሰራ ነው ያነሱት፡፡
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የኢትዮ-ጂቡቲ 2ኛ ሰርኪዩት እና የጎንደር-ዳንሻ-ሁመራ-ባዕከር አግሮ ኢንዱስትሪ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የመቀሌ-ዳሎል የኃይል ማስተላለፊያ መስመርን ጨምሮ የሰባት ፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማስጀመር ዕቅድ ተይዟል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ የኃይል አማራጮች 38 ሺህ 120 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት መታቀዱንና ከዚህም ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የ45 ነጥብ 21 በመቶ ድርሻ እንደሚኖረው ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ደንበኞች 31 ሺህ 600 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማቅረብ እንዲሁም ከልዩ ልዩ ገቢዎች በአጠቃላይ 109 ነጥብ 54 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡
ተቋሙ ለ2018 በጀት ዓመት ለሥራ ማስኬጃ 251 ቢሊየን ብር በጀት የያዘ ሲሆን 55 ነጥብ 1 ከመቶ ከኃይል ሽያጭና ልዩ ልዩ ገቢዎች፣ 31 ነጥብ 4 ከመቶ ከሀገር ውስጥ ብድርና እርዳታ እንዲሁም 13 ነጥብ 5 ከመቶ ከዓለም አቀፍ ብድርና እርዳታ እንደሚሸፈን ተገልጿል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከተያዘው 251 ቢሊየን ብር ውስጥ 71 በመቶ ለፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ እንደሚውል የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው 118 ቢሊዮን ብር በግንባታ ሂደት ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች፣ 29 ቢሊዮን ብር ለአዳዲስ ፕሮጀክቶች ማስጀመሪያ እና 10 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመልሶ ግንባታ ሥራ እንዲሁም ቀሪው 17 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብሩ ለመለዋወጫ ዕቃዎች ግዥ እና ለሲቪል ጥገና ክፍያዎች መመደቡን አብራርተዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት የተነሳ በምዕራብ ጎንደር ዞን ኃይል ተቋርጧል
……..///…….
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ጭልጋ ከተማ አካባቢ በስርቆት ምክንያት በከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ።
በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት ከአዘዞ-ሸኽዲ በተዘረጉ ሦስት ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡
በዚህም ምክንያት ከሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በሙሉ የኃይል አቅርቦት በጊዜያዊነት እንደተቋረጠባቸው ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ በላይነህ ገለፃ ከአዘዞ-ሸኽዲ በተዘረጉ አስር ተጨማሪ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የስርቆት ወንጀል በመፈፀሙ የመውደቅ አደጋ ላይ ናቸው፡፡
በአሁኑ ወቅት የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች ዳግም ለመጠገን እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የወደቁትን ሦስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በአፋጣኝ መልሶ በመትከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የኃይል አቅርቦቱን ለማስቀጠል ጥረት ይደረጋል፡፡
በመሆኑም ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ የአካባቢው ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የአዘዞ-ሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ከፍተኛ የሥርቆት ወንጀል እየተፈጸመ እንደሆነ ገለፁት ሥራ አስኪያጁ ህብረተሰቡና የፀጥታ አካላት ለኃይል መሠረተ ልማቱ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በዞኑ በስርቆት እና ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ለ20 ቀናት ተቋርጦ የቆየውን ኃይል በጊዜያዊነት በ87 የእንጨት ምሰሶዎች በመተካት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ መደረጉ አይዘነጋም፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሁናዊ ገፅታ
📌 ከአፍሪካ ሙሉ በሙሉ ታዳሽ ኃይል በመጠቀም 3ኛ የግሪድ አስተዳዳሪ ተቋም ነው።
📌 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴን እና አሰላ የንፋስ ኃይል ፣ማመንጫን ጨምሮ 20 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል።
📌 ከ20 ሺህ 700 ሰርኪዩት ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው 308 የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን አሉት።
📌 ከ132 ኪሎ ቮልት እስከ 500 ኪሎ ቮልት የቮልቴጅ መጠን ያላቸው 145 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በኦፕሬሽን ላይ ይገኛሉ።
📌 በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከ31 ሺህ 400 በላይ ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው 361 ትራንፎርመሮች አሉት።
📌 ከ40 ሺህ በላይ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች አሉት።
📌 በአሁኑ ወቅት ካፒታሉ 586 ቢሊየን ብር እንዲሁም አጠቃላይ ሀብቱ ደግሞ 709 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
📌 ከአፍሪካ ከውኃ ኤሌክትሪክ ኃይልን በማመንጨት አቅም አንደኛ ነው።
📌 በ2017 በጀት ዓመት 7 ሺህ 910 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም የነበረው ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም
15 698
የማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመር ተጠግኗል
…..///…...
ለወራት ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ የቆየው የለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 1 አስታወቀ፡፡
የሪጅኑ ዳይሬክተር ኢንጂነር ደረጀ ገዛኸኝ እንደተናገሩት በማከፋፈያ ጣቢያው አቅራቢያ በሚጣለው ቆሻሻ ላይ የሚሰባሰቡ አሞራዎች የጣቢያው አንድ ትራንስፎርመር እንዲቃጠል አድርገው ነበር።
በዚህ እና ከስርጭት መስመር ጋር በተያያዙ ቴክኒካል ችግሮች በተደጋጋሚ ኃይል ይቋረጥ እንደነበር ኢንጂነር ደረጀ አንስተዋል።
የኃይል መቋረጡን በዘላቂነት ለመፍታት እና የጣቢያውን አቅም ለማሳደግ አንድ መቶ ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፔር ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለመትከል የማጓጓዝ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።
ትራንስፎርመሩ ተጓጉዞ ማከፋፈያ ጣቢያው እንዲደርስ እገዛ ያደረጉትን የአዲስ አበባ እና የሸገር ከተማ ፖሊስን አመስግነዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም
