es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 528 suscriptores, ocupando la posición 8 328 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 528 suscriptores.

Según los últimos datos del 06 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 6, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 27.84%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.05% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 323 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 492 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 07 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 528
Suscriptores
-324 horas
-97 días
+630 días
Archivo de publicaciones
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!! መልካም በዓል! የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!! መልካም በዓል! የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል

ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ !!! መልካም በዓል! የኢትዮጵያ ኤክትሪክ ኃይል

የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ ……………///…………... የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ በሚደረገው ዘመቻ የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢ
+4
የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ ……………///…………... የቆቃ ሐይቅን ከእምቦጭ አረም ለመታደግ በሚደረገው ዘመቻ የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አመራሮች እና ሠራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ሊሞ ወረዳ ቆቃ ነገዎ ቀበሌ በመገኘት ተሳትፎ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መለስ ሲሎ እንደገለፁት የዘመቻው ዋና ዓላማ መጤ አረሙ በሐይቁና በግድቡ ላይ እያሳደረ የሚገኘውን ተፅዕኖ ለመቀነስ ነው፡፡ በዕለቱም አንድ ሔክታር የሚሸፍን የእምቦጭ አረም የመንቀል እና ለአረሙ ምቹ የሆኑ ደለሎችን የማፅዳት ሥራ መከናወኑንም ነው የጣቢያው ኃላፊ የተናገሩት፡፡ በሐይቁ ላይ የእምቦጭ አረም በፍጥነት እየተስፋፋ የሚሄድ ከሆነ ወደ ግድቡ የሚገባውን የውሃ መጠን በመቀነስ የሚመረተውን ኃይል ሊቀንስ ይችላል ሲሉም ኃላፊው ተፅዕኖውን ገልፀዋል፡፡ ከ50 በላይ የጣቢያውን ሠራተኞች ያሳተፈው ዘመቻ የመጤ አረሙን የመስፋፋት ጉዞ ለመግታት ያለመ ቢሆንም ችግሩ አሳሳቢ ከመሆኑ አንፃር ድጋፉ እና ርብርቡ መቀጠል እንዳለበት አቶ መለስ ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ልዩ ትኩረት በመስጠትና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍ ሐይቁን እና የኃይል ማመንጫ ግድቡን ከመጤ አረም ለመታደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ የቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ 60 ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ታህሳስ 27 ቀን 2013 ዓ/ም

ለቁፋሮ ከሚያገለግሉ ሁለት የጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኖች መካከል የአንድ ማሽን ተከላ ተጠናቋል …………..////…………… የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ ለማካሄድ ከሚያስፈልጉት ሁለት የቁፋ
+2
ለቁፋሮ ከሚያገለግሉ ሁለት የጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኖች መካከል የአንድ ማሽን ተከላ ተጠናቋል …………..////…………… የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮ ለማካሄድ ከሚያስፈልጉት ሁለት የቁፋሮ ማሽኖች መካከል የአንዱ ማሽን ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት አስታውቋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት መሐንዲስ አቶ መሳይ ፍቃዱ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት የሁለተኛው ማሽን ተከላም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ማሽኖቹ የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችን ያሟሉና ከ2 እስከ 2 ነጥብ 5 ኪ.ሜ ጥልቀት መቆፈር የሚያስችል አቅም እንዳላቸውና 350 ቶን ያህል ክብደት የመሳብ ወይም የመሸከም አቅም ያላቸው መሆኑን አቶ መሳይ ተናግረዋል፡፡ ከማሽን ተከላው ጎን ለጎን ለጉድጓድ ቁፋሮ የሚያገለግሉ እያንዳንዳቸው 4 ሚሊዮን ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የውሃ ታንከሮች ገጠማ እና የውሃ መስመር ዝርጋታ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ የውሃ መስመር ዝርጋታው እንደተጠናቀቀ የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራው በይፋ እንደሚጀመርም ነው ያስታወቁት፡፡ የፕሮጀክቱ የሠው ኃይል አስተዳደር ባለሙያ አቶ ወርቁ ዱቄ በበኩላቸው በእስካሁኑ ሒደት ከ100 በላይ ኢትዮጵያዊያን በፕሮጀክቱ የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ገልፀዋል፡፡ የቻይናው ኬሩይ /KERUI/ ኩባንያ የመቆፈሪያ ማሽኑን አምርቶ የገጠማ ስራውን በማከናወን ላይ ሲሆን የኬንያው ኬንጀን /KENJEN/ እና የቻይናው ኬሩይ ኦይል ፊልድ /KERUI Oil field/ ኩባንያዎች ደግሞ የጉድጓድ ቁፋሮውን ያከናውናሉ፡፡ የአሉቶ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፕሮጀክት ከምድር በሚወጣ ተፈጥሯዊ እንፋሎት አማካኝነት 70 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ያለመ ነው፡፡ ታህሳስ 20 ቀን 2013 ዓ.ም

ወደ ከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ተጠግተው ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኑ ..............///........ ከሰኮሩ ጊቤ 2 የሚያገናኝ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተ
+3
ወደ ከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር ተጠግተው ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኑ ..............///........ ከሰኮሩ ጊቤ 2 የሚያገናኝ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመርን ተጠግተው ለመኖሪያ ቤት ኤሌክትሪክ የዘረጉ ግለሰቦች ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ለ30 ደቂቃዎች አካባቢ በከፊል ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መቋረጥ ምክንያት ሆነዋል። ኤሌክትሪክ የተቋረጠው ግለሰቦቹ ለመኖሪያ ቤታቸው ከጎረቤት በአየር ላይ የሳቡት የኤሌክትሪክ ሽቦ ወደ ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመር በመቅረቡ በተፈጠረ የኤሌክትሪክ መሳሳብ ነው። በዚህም በተወሰኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ለግማሽ ሰዓት ሲቋረጥ አንድ የሳር ቤትና ለመሰብሰብ የደረሰ ሰብል ተቃጥሏል። የአካባቢው ነዋሪ ተረባርቦ እሳቱን ባያጠፋው ኖሮ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችል የነበረ ሲሆን ፖሊስ የድርጊቱን ፈፃሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማድረግ ላይ ይገኛል። ህብረተሰቡ ወደከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ መስመሮች ተጠግቶ ምንም ዓይነት መሰረተልማት እንዳይዘረጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል። ታህሳስ 17 ቀን 2013 ዓ/ም

ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠ ማሳሰቢያ ********************* የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የጥገና ሥራ ስለሚያከናውን እሁድ ታህሳስ 18 ቀን 2013 ዓ.ም ከጥዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በምስራቅ ኢትዮጵያ ማለትም በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በአሰበተፈሪ፣ በጅግጅጋ፣ በፊቅ ፣ በደገሃቡር፣ በአዋሽ ሰባት ኪሎ፣ በአዲጋላ፣ በሁርሶ፣ በአሰላ፣ አዳማ፣ አዳሚ ቱሉ እና ሻሸመኔ እንዲሁም በምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን በኖሪያ፣ ደብረዘይት፣ በኢላላገዳ፣ በጆርጅ ጫማ ፋብሪካ፣ በሞጆ፣ በራም፣ በጎዴ፣ በኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር እና አካባቢዎቻቸው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡ ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደረጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡

የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቀቀ ............../////........... የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቆ አ
+4
የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቀቀ ............../////........... የሻሸመኔ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፊያ ጣቢያ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሠላሳ ዓመታት በላይ ለሻሸመኔ ከተማና አጎራባች ወረዳዎች አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም በየጊዜው እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ማስተናገድ እንዳልቻለ ሪጅኑ ጠቁሟል፡፡ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር የመሸከም አቅም በነበረው አንድ ትራንስፎርመር ለከተማውና አጎራባች አካባቢዎች ኃይል ለማዳረስ ጥረት ሲደረግ ቢቆይም ፍላጎቱ ከጣቢያው አቅም በላይ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ይህም በሻሸመኔ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ኤሌክትሪክ በፈረቃ እንዲሰጥ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ አሳድሮ እንደነበር ሪጅኑ ገልጿል፡፡ ጣቢያው ያለበትን ችግር ለመቅረፍ በተሰራው ሥራ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር መሸከም የሚችል የኃይል ትራንስፎርመር በመትከልና የተለያዩ የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን አቅሙን በእጥፍ ለማሳደግ እንደተቻለ አስታውቋል፡፡ 15 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው 6 ወጪ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመቆጣጠሪያና የመከላከያ መሳሪያዎችን በአዲስ መልክ የመትከል ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡ ለማስፋፊያ እና ማሻሻያ ሥራው ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ መስጠት መቻሉን ሪጅኑ ገልጿል፡፡ ታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ/ም

በአዲግራትና ውቅሮ ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳግም ጀምሯል ................///.............. በአዲግራትና ውቅሮ ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የመብራት አገልግሎት ዛሬ ማምሻውን ጀምሯል። በህወሃት ጁንታ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በአፋጣኝ ወደ አገልግሎት ለመመለስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሲሰራ ቆይቷል። የውቅሮና አዲግራት ከተሞች የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና በመጠናቀቁ የፍተሻ ስራ ተከናውኖ ከተሞቹ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል። የሽሬ፣ አክሱምና አድዋ ከተሞች ኃይል እንዲያገኙም በቅንጅት በመሰራት ላይ ነው። ታህሳስ 08 ቀን 2013 ዓ/ም

የመቀሌ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ አግኝቷል ..................////............ የመቀሌ ከተማና አካባቢው ከሳምንታት የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቋረጥ በኋላ ዛሬ አገልግሎት አግኝቷ
የመቀሌ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ አግኝቷል ..................////............ የመቀሌ ከተማና አካባቢው ከሳምንታት የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቋረጥ በኋላ ዛሬ አገልግሎት አግኝቷል። ከአላማጣ ከተማ አንስቶ እስከ መቀሌ ድረስ ባሉ ከተሞች በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሽቦዎች( ኮንዳክተሮች) እና ስኒዎች(ኢንሱሌተሮቸ) ላይ የህወሀት ጁንታ ቡድን ባደረሰው ጥቃት በአካባቢዎቹ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱ ይታወሳል። በጁንታው ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ጠግኖ ሁሉንም የክልሉ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሁለት የጥገና ቡድኖችን አዋቅሮ ቀን ከሌት ሲሰራ ቆይቷል። በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የተሰማራው የጥገና ቡድን በመተማ፣ሁመራና ወልቃይት የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ሥራ በማጠናቀቅ ከተሞቹ ኃይል እንዲያገኙ አድርጓል። ከደሴ በመነሳት ወደሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ የተሰማራው የጥገና ቡድን ደግሞ ከቀናት በፊት የአላማጣ፣ ማይጨው፣ መሆኒነና ሰቆጣ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ያደረገ ሲሆን ዛሬ የመቀሌ፣ ኲዊሀ፣ አዲጉዶምና አካባቢው ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ማድረግ ችሏል። በስፍራው የተሰማሩ የጥገና ባለሙያዎች አስቸጋሪና ፈታኝ ሁኔታዎችን ታግለው ሌት ተቀን በመስራት ለዚህ ውጤት በመድረሳቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አልፎ ሀገርንና ህዝብን እንደማገልገል የሚያስደስት ነገር እንደማይኖር በተግባር ስላሳያችሁን በሥራችሁ ኮርተናል ሲሉ የተሰማቸውን ስሜት ገልፀዋል። ታህሳስ 04 ቀን 2013 ዓ/ም

በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሠራ ነው ..............///........ በትግራይ ክልል ስግብግቡ የህወኃት ጁንታ ጉዳት ያደረሰባቸውን የኤሌ
+1
በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሠራ ነው ..............///........ በትግራይ ክልል ስግብግቡ የህወኃት ጁንታ ጉዳት ያደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ጠግኖ ሁሉንም የክልሉ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን አስታወቁ፡፡ የጥገና ስራውን በክልሉ ሙሉ በሙሉ ለማከናወንም ከተቋሙ የተውጣጣ የቴክኒክ ባለሙያዎች ቡድን በሁለት መስመር መሰማራቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ አንደኛው ቡድን በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ በመንቀሳቀስ ከባህርዳር ተነስቶ ወልቃይት፣ሁመራ፣ ወልቃይት፣ ሽሬ፣ አክሱም እና አድዋ ለሚገኙ የኃይል መሰረተ ልማቶች የጥገና ሥራዎችን በማከናወን ላይ ሲሆን በሰሜን ምስራቅ የተንቀሳቀሰው ሁለተኛው ቡድን ደግሞ ከደሴ በመነሳት አላማጣ፣መሆኒ፣ሰቆጣ፣አሸጎዳ፣መቀሌና አዴግራት አካባቢዎች ላይ የጥገና ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ እስከአሁን በመተማ፣ሁመራ፣ወልቃይት እና ማይጨው የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ሥራ ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ከአላማጣ-ሰቆጣ የተዘረጋውን ባለ 66 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን የአላማጣ እና ሰቆጣ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ መደረጉንም ነው አቶ ሞገስ ያብራሩት፡፡ በአሁኑ ጊዜ የመቀሌ-መሆኒ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል መስመር የጥገና ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ የመቀሌ ከተማ በቅርቡ የኤሌክትሪክ ኃይል እንድታገኝ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ እስከመጪው እሁድ አብዛኞቹ የትግራይ ከተሞች ኃይል እንዲያገኙ በሙሉ አቅም ርብርብ እየተደረገ ነውም ብለዋል

photo content

photo content

ተቋሙ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን እና የፀረ ሙስና ቀን አከበረ ………../////………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሰራተኞች “እኩልነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለጋራ ብልፅግና” በሚ
+5
ተቋሙ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን እና የፀረ ሙስና ቀን አከበረ ………../////………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሰራተኞች “እኩልነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለጋራ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል 15ኛውን የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ፡፡ የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበዓሉ ላይ እንደተናገሩት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ስናከብር በህዝቦች እኩልነት ላይ የተመሰረተ እውነተኛና ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት ዲሞክራሲ ለመገንባት ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማገዝ ተቋማችን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲኖር በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሚከበረው ከሃዲው የህወሓት ጁንታ ለመደምሰስ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ባደረገው ታላቅ ተጋድሎ በተገኘው ድል ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ባሸነፈበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ በተያያዘ የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች “የትውልድ ሥነ ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን በመታገል የብልፅግና ጉዟችንን እናፋጥን” በሚል መሪ ቃል 16ኛው የፀረ ሙስና ቀን አክብረዋል፡፡ ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.

በተቋሙ የድጋፍና እንክብካቤ ትግበራ እየተከናወነ ነው ………………////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤችአይቪ መከላከልና መቆጣጠር የሥራ ክፍል የኤችአይቪ/ኤድስ ወረርሽንን ከመከላከል በተጨማ
በተቋሙ የድጋፍና እንክብካቤ ትግበራ እየተከናወነ ነው ………………////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤችአይቪ መከላከልና መቆጣጠር የሥራ ክፍል የኤችአይቪ/ኤድስ ወረርሽንን ከመከላከል በተጨማሪ የድጋፍና እንክብካቤ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡ ኤች.አ.ቪ / ኤድስ በተቋሙ እያደረሰ ያለውን ተፅዕኖ ለመከላከል በፖሊሲ የተደገፈ የድጋፍና ክብካቤ ሥርዐት ዘርግቶ እየሰራ መሆኑን የስራ ክፍሉ አስታውቋል፡፡ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ሠራተኞች ከኤችአይቪ ጋር የተያያዘ ህመም ከታከሙ ለሕክምና የሚያዋጡት የ10 በመቶ ወጪ መጋራት እንዲቀር ተደርጓል፡፡ እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ሠራተኞቹ ጤነኛ ሆነው በሥራቸው እንዲቀጥሉ የማድረግ ስራዎችም ተከናውነዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ከደመወዙ በወር ብር 5 ብር በማዋጣት በድምሩ በየወሩ እስከ ብር 35 ሺህ በኤድስ አስተዋጽኦ (Contrubtion ) አካውንት እየተሰበሰበ ይገኛል፡፡ በተሰብሳቢ ገንዘቡም ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝ 39 (ሰላሳ ዘጠኝ) የተቋሙ ሠራተኞች በየወሩ 7 መቶ ብር ከደሞዝ ጋር በአካውንታቸው እንዲገባ፣ ወላጆቻቸውን በኤች.አ.ቪ / ኤድስ ላጡ 21(ሃያ አንድ) ህፃናት በየወሩ በአሳዳጊዎቻቸው አካውንት ብር 500 እና በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ለትምህርት ቁሳቁስ መግዣ በአንድ ልጅ እስከ ብር 1650 ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ከሰራተኞች በወር 35 ሺህ ብር ቢሰበሰብም ወጪ ድጋፍ እየተደረገ ያለው ከሚሰበሰበው በላይ በመሆኑ ልዩነቱ ድጋፉ ከመጀመሩ በፊት በአካውንቱ ውስጥ ከተጠራቀመ ገንዘብ ላይ እየተከፈለ ይገኛል፡፡ ህዳር 29 ቀን 2013 ዓ.ም.

ሴቶች ከሁሉም ዓይነት ጭቆና ነፃ እስካልሆኑ ድረስ ነፃነት ተጎናጽፈናል ማለት አይቻልም! ኔልሰን ማንዴላ
ሴቶች ከሁሉም ዓይነት ጭቆና ነፃ እስካልሆኑ ድረስ ነፃነት ተጎናጽፈናል ማለት አይቻልም! ኔልሰን ማንዴላ

የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው =========////========= የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ቋሚ ሠራተኞች ሀብት የመመዝገብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በተቋሙ የሥ
የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው =========////========= የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ቋሚ ሠራተኞች ሀብት የመመዝገብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በተቋሙ የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርጋ ተረፈ እንዳስታወቁት የፌዴራል የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ሀብትና ንብረትን ለማስመዝገብ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ ሁሉም የተቋሙ ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ሀብታቸውን እያስመዘገቡ ነው፡፡ በተቋሙ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የሥራ መሪዎች እና በተመረጡ የሥራ መደቦች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች ሀብታቸውን አሳውቀው ማስመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሁሉም የመንግስት ሠራተኛ ሀብቱን እንዲያሳውቅና እንዲያስመዘግብ የተደረገው የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 ለማስፈፀም የወጣው የተሻሻለው መመሪያ ቁጥር 1/2013 ስለሚያስገድድ ነው ብለዋል፡፡ እንደ አቶ መርጋ ገለፃ በተቋሙ ሀብታቸውን ማስመዝገብ ከሚጠበቅባቸው 6 ሺህ 565 ቋሚ ሠራተኞችና አመራሮች ውስጥ ለ5 ሺህ 7 መቶ ሠራተኞች የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ ቅጽ ተደራሽ ተደርጓል፡፡ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስም ከ3 ሺህ 7 መቶ በላይ አመራሮችና ሠራተኞች ሀብትና ንብረታቸውን አስመዝግበዋል፡፡ ህዳር 25 ቀን 2013 ዓ/ም

በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖራታል .................///.................. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖራታል .................///.................. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንደሚኖራት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ አስታወቁ፡፡ ሚኒስትሩ ዛሬ በዌቢናር በተካሄደው የዩይትድ ኪንግደምና የአፍሪካ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ሲምፖዚየም ላይ እንደገለፁት በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አቅም ለመፍጠር አቅዳ እየሰራች ነው። ኢትዮጵያ እስካሁን 6ዐ በመቶ የሚሆኑት ዜጎቿ የኃይል ተጠቃሚ እንዳልሆኑና የኃይል አቅርት ችግሩ ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን እያስከተለ እንደሆነም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመቀየር መንግስት የተለያዩ እቅዶችን በማውጣት እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2025 ኢትዮጵያ በግሪድና በኦፍ ግሪድ ለዜጎች ሙሉ በሙሉ ኃይል ለማቅረብ ማቀዷን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪና ቴክኖሎጂ የሚጠይቅ በመሆኑ እንደ ዩናይትድ ኪንግደም ያሉ ሃገራት ባለሃብቶች በዘርፉ ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በሲምፖዚየሙ ላይ የኢትዮጵያ፣ የሞሮኮ፣ የግብጽ፣ የሞዛምቢክና የሞሪታኒያ ሃገራት የኢነርጂ ሚንስትሮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን 183 ባለድርሻዎችም የዌቢናር ውይይቱን ታድመውታል፡፡ ህዳር 24 ቀን 2013 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ደም ለገሱ ----------------------//------------------------ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች “ደም እንለግስ
+6
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ደም ለገሱ ----------------------//------------------------ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች “ደም እንለግስ፤ ህይወት እንታደግ” በሚል መሪ ቃል ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም የደም እጥረት ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል ደም ለግሰዋል፡፡ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ኃይል ከማመንጨት ሀገራዊ ተልዕኮው ባለፈ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል፡፡ በዛሬው ዕለትም በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸውና በደም ዕጦት ምክንያት ህይወታቸው አደጋ ላይ የወደቀ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች ደም በመለገስ አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡ የተደረገው የደም ልገሳ በጤና ተቋማት የሚያጋጥመውን የደም እጥረት ለመቅረፍ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ይታመናል፡፡ ‹ ደም ሲለግሱ ያገኘናቸው የተቋሙ ሠራተኞች ደም መለገስ በመቻላቸው እንደተደሰቱ እና በቀጣይ መሰል ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሀ ግብሩ ለሀገር የሚከፈል ዋጋን መደገፍ ነው ያሉት ሠራተኞቹ የሚለገሰው ደም ለአንድ የቤተሰብ አባል እንደሚውል በማሰብ ሁሉም ሊሳተፍበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ¬ በብሄራዊ የደም ባንክ አገልግሎት የተንቀሳቃሽ ደም ለጋሾች ባለሙያ ሲስተር ዘውዴ ግዛቸው እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በደም እጥረት ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ የበርካታ ወገኖቻቸውን ህይወት መታደግ እንደሚቻል በመረዳት በዚህ በጎ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ሊመሰገኑ ይገባል፡፡ ሌሎች ተቋማትም ይህን አርዓያ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ህዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም.

በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ከሁለት ሰዓት በላይ ተቋርጦ የነበረውን ኃይል በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ማገናኘት ተጀምሯል። ደረጃ በደረጃ የተቀሩትን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ የማድረግ ስራም በመከናወን ላይ ይገኛል። ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም

በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል ……………/////……………… ዛሬ ህዳር 15 ቀን 2013 ዓ/ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል፡፡ በቴክኒክ ችግር የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የቴክኒክ ክፍል ባልደረቦቻችን ርብርብ በማድረግ ላይ ናቸው። በቀጣይ አንድ ሰዓት ውስጥ ደረጃ በደረጃ ኃይል የማገናኘት ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል። ህዳር 15 ቀን 2013