EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 22,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 921 次浏览,首日通常累积 2 563 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
+424 小时
-357 天
+2230 天
帖子存档
15 537
#የፕሮግራም ጥቆማ#
የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተልማት ለማስፋፋት የሚደረገው ጥረት በተፈለገው መንገድ እንዳይጓዝ ከሚያደርጉት ጉዳዮች መካከል የወሰን ማስከበርና የካሳ ጉዳይ ይጠቀሳሉ። የወሰን ማስከበር ጉዳይ ለፕሮጀክት ትግበራ እንቅፋት ሊሆን የሚችለው እንዴት ነው? በወሰን ማስከበርና በካሳ ምክንያት አንድ ፕሮጀክት መዘግየቱ የሚያመጣው ጫና ምንድነው? ዛሬ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በኢቲቪ ዜና ቻናል የሚተላለፈው ፍኖተ ብርሃን ፕሮግራም ምላሽ ለመስጠት ይሞክራል።በተጨማሪም በኢቲቪ የኦሮምኛ ቻናል ከምሽት 12:10 ጀምሮ በኦሮምኛ ቋንቋ የሚተላለፈውን ፕሮግራም የሚያነሳቸው የተለያዩ ጉዳዮች ይኖራሉ። ፕሮግራሞቹን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 06 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ለአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷል
.........///..........
በፕሮጀክት ትግበራ ወቅት ለአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው የዓለም ባንክ ባዘጋጀው የግዢ፣ አካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች አስተዳደር ሥልጠና ላይ እንደገለፁት ተቋሙ የአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ጉዳዮች ዓለምአቀፍ ተቀባይነት ባላቸው ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት ስለመተግበራቸው ክትትል እያደረገ ነው።
የሥራ ክፍሉንም የሰው ኃይል በማሟላትና የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በማዘጋጀት ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በግል አልሚዎች በሚለሙ ፕሮግራሞች ላይም የአካባቢ፣ ማህበራዊና የሙያ ደህንነት ጉዳዮች በአግባቡ ስለመተግበራቸው ክትትል ይደረጋል።
በሥልጠናው ላይ ሀሳባቸውን የገለፁት የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው የሙያ ደህንነት ጉዳይ ከተቋሙ ዕሴቶች መካከል አንዱ ሆኖ መቀረፁ የተሰጠውን ትኩረት ያሳያል ብለዋል።
በትግበራ ወቅት የሚስተዋሉ ችግሮችም በሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 06 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በይፋ ተጀመረ
.........///..........
ለበቆጂ ከተማና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ለሚገነባው የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የበቆጂ ከተማ ከንቲባ አቶ ሁሲያ አሚን እና የከተማው የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች፣ የአካባቢው አባ ገዳዎችና የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ የፕሮጀክት ማኔጅመንት 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ ተድላ ሰይፉ በግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ ነው።
የበቆጂ እና የደብረታቦር ከተሞች የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክትን ግንባታን ለማስጀመር ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ ከተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ጋር በቅንጅት ሲሰራ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተድላ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቅ ለከተሞቹ እና በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ወረዳዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያግዛሉ ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱን በተያዘለት በጀት፣ ጊዜና እና ጥራት አጠናቆ ለማስረከብ ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶት እንደሚሰራ በመግለፅ የአካባቢው ህብረተሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደትግ ጠይቀዋል።
የበቆጂ ከተማ ከንቲባ አቶ ሁሲያ አሚን በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በአካባቢው የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችና የኢንቨስትመንት ሥራዎች እንዲስፋፉ ለማድረግ እና ለአካባቢው ወጣቶች ሥራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ በመርሃ ግብሩ መሠረት ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፋ እና ክትትል እንደሚያደርግም ከንቲባው አረጋግጠዋል።
ለበቆጂ እና ደብረታቦር የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ዕቃ የሚያቀርበው ሻንጋይ ሲዩአን የተባለው የቻይና ኩባንያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሊ ይንግጁን እንደተናገሩት ኩባንያቸው ለፕሮጀክቶቹ የሚያገለግሉ ግብዓቶችን በስምምነቱ መሠረት ለማቅረብ በትኩረት ይሠራል።
በአሁኑ ወቅት ለግንባታ ሥራው የሚያስፈልጉ አንዳንድ ዕቃዎችን የማምረትና የማጓጓዝ ሥራ እንደተጀመረ ሥራ አስኪያጁ ገልፀው ኩባንያውፕሮጀክቱ ላይ የሚተከሉ ሁሉንም ዕቃዎች በመርሃ ግብሩ መሠረት እንደሚያቀርብ አረጋግጠዋል።
የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ 89 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያለው ሲሆን ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር፣ ሁለት ባለ 230ኪሎ ቮልት ገቢ እና አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ይኖሩታል።
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የሚገነባው የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ከመልካ ዋከና - ቆቃ ከተዘረጋዉ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠልፎ( line in and line out) የሚከናወን የ1 ኪሎ ሜትር ማስተላለፊያ መስመር ይዘረጋለታል፡፡
ፕሮጀክቱን የሚገነባው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ሲሆን የማማከር ሥራውን የሚሰራው የተቋሙ ኢንጂነሪንግ ዘርፍ ይከናወናል፡፡
ለፕሮጀክቱ ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪልና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታ እንዲሁም ለማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ የዕቃ አቅርቦት ወጪን ሳይጨምር ከ216 ነጥብ 31 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦለታል። ወጪውም ሙሉ በሙሉ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚሸፈን ነው ተብሏል።
የዚህ ፕሮጀክት አካል የሆነውና ከዓለም ባንክ በተገኝ ብድር የሚገነባው የደብረ ታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በቅርቡ እንደሚካሄድም ከፕሮጀክት ቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
"ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 05 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ቁልፍ አጋር ሆኖ እየሰራ ነው
........///.....
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ቁልፍ አጋር በመሆን የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ጥሪ አቀረቡ።
ባንኩ በግዢ፣ በአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች አስተዳደር እንዲሁም በተቋሙ ስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት ነጥቦች ላይ ያዘጋጀውን ስልጠና ሲከፍቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደተናገሩት ተቋሙ በዓለም ባንክ ድጋፍ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እየተገበረ ነው።
በመሆኑም የጀመራቸውን ቁልፍ ድጋፎች አጠናክሮ እንዲቀጥል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠይቀዋል።
በዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ፕራክቲስ ማናጀር ኤሪክ ፈርንስትሮም በበኩላቸው ባንኩ ከ56 ሚሊየን የሚልቁ ኢትዮጵያውያንን ከጭለማ ለማውጣት በተለይ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ሥራዎቹ በመልካም ግንኙነት እየተተገበሩ ቢሆንም የሚያጋጥሙትን ማነቆዎች በቅርበት በመነጋገር መፍታት ይገባል ብለዋል።
የተዘጋጀው ስልጠናም ስልታዊ ዕሳቤ ለማሳደግና በጋራ ለመስራት እንደሚያግዝ ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አንዷለም ሲዓ ተቋሙ በሦስት ዓመታት ውስጥ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ መስመር እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ለማከናወን የያዘውን ዕቅድ አቅርበዋል።
ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሥልጠና ላይ በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግበ ከተያዘው መርሐግብር መረዳት ተችሏል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 05 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
መምሪያው እያደረጋቸው ያሉ የአይ ሲ ቲ ድጋፎች ሥራዎችን ለማቀላጠፍ እያገዙ ነው
……..///………
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአይ ሲ ቲ መምሪያ በተቋሙ ለሚገኙ የሥራ ክፍሎች እያደረጋቸው ያሉ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎች ሥራዎችን በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ፡፡
በተቋሙ የምርምርና ልማት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሚራጅ ፈረጃ፣ በገበያና ቢዝነስ ልማት መምሪያ የፕራይሲንግ እና ሪቫሉዌሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ በለጠ፤ በኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ዘርፍ ባለሙያ የሆኑት ራሄል አርዓያ፣ በግዥ መምሪያ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታቸው ጎጃም እንዲሁም የኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ጉቱ እንደተናገሩት የተቋሙ አይሲቲ መምሪያ እያደረጋቸው ያሉ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎች ሥራዎችን በማቀላጠፍ በኩል ፋይዳቸው የጎላ ነው፡፡
ሠራተኞች እንደተናገሩት ለሥራ የሚያገለግሉ ፕሪንተሮችና ኮምፒውተሮች ላይ እንዲሁም ከኔትወርክ እና ከሲስተም ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲያጋጥሙ የተቋሙ የአይሲቲ ባለሙያዎች በሚያደርጉት ድጋፍ ችግሮች እየተቀረፉ ይገኛሉ፡፡
ይህም ሠራተኛው ሥራውን በአግባቡ በማከናውን ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ ያግዛል ነው ያሉት፡፡
ችግር ሲያጋጥማቸውና የባለሙያ ድጋፉ ሲፈልጉ ጥያቄውን በአካል፣ በስልክ እንዲሁም የውስጥ ማስታወሻ ደብዳቤ በማጻፍ እንደሚጠይቁ የተናገሩት ሠራተኞቹ ተጠቃሚው አካል ድጋፉን ለማግኘት ሲፈልግ በሥራ ቦታው ላይ በመሆን ድጋፍ የሚጠይቅበት ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓት (ኦን ላይን) መዘርጋት እንዳለበት ጠይቀዋል፡፡
በተቋሙ የአይ ሲ ቲ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ብዙአየሁ አክሊሉ በበኩላቸው የሥራ ክፍሉ ከሲስተም አጠቃቀም፣ ከሃርድ ዌር ጥገና እና ከኔትወርክ ጋር በተያየዘ የሥራ ክፍሎች በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት ድጋፎች እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ተቋሙ የአሰራር ቅልጥፍናን ይፈልጋል ያሉት ዳይሬክተሩ ይህን ለማድረግ ሲስተሞችን ከማዘጋጀት ጀምሮ ከአጠቃቀምና ከኔትወርክ ችግር ጋር በተያያዘ በሥራው ላይ ተጽዕኖ እንዳይኖር የተለያዩ ድጋፎች እንደሚደረጉ ጠቁመዋል፡፡
በሥራ ክፍሉ እየተደረጉ ያሉ ድጋፎች በተጠቃሚው ላይ ያመጣውን ውጤት ለመገምገም፣ ድጋፍ የሚፈልጉ አካላት ጥያቄያቸውን ወጥነት ባለው መልኩ እንዲያቀርቡ ለማድረግ እና ድጋፉንም ወጥነት ባለው መልኩ ለመስጠት የሚያስችል አሰራር ለመዘርጋት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የሚዘረጋው አሰራር የአይ ሲ ቲ ድጋፍ ጥያቄዎችን በመልዕክት፣ በስልክ፣ በኢሜይል እና ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ለማቅረብ እንደሚግዝ ተናግረዋል፡፡
አሰራሩ ሲተገበር የድጋፍ ፈላጊውን እንግልት በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡
እንደ አቶ ብዙአየሁ ገለጻ አሰራሩ ባለሙያው ድጋፉን በአግባቡ መስጠቱን ከተጠቃሚው በቀላሉ እርካታ ለመቀበል እና ድጋፉ የሚሰጠውን ሠራተኛ ለመቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡
ባለሙያው የድጋፍ ሥራዎችን በአግባቡ እንዲያከናውን የተለያዩ የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠናዎችን በመስጠት የእውቅና ማረጋገጫ እንዲያገኙ ( ሰርቲፋይድ እንዲሆኑ) ተደርጓል ነው ያሉት፡፡
ዳይሬክተሩ እንዳሉት መምሪያው ለተቋሙ የሥራ ክፍሎች እያደረገ ካለው ድጋፍ በተጨማሪ ለብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል እና ለኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ዘርፍ የተለያዩ ሶፍትዌሮችን አልምቷል፡፡
በተቋሙ እየተተገበረ ያለው የሳፕ ሲስተም ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ድጋፍ ሲደረግ እንደነበር የጠቆሙት አቶ ብዙአየሁ በአሁኑ ወቅት በተቋሙ በኩል የሥራ ኃላፊ በመመደብ ድጋፉ በራስ አቅም እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 04 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሁለተኛ ሆኖ አጠናቀቀ
.......///.........
አስራ ሶስት ክለቦች በተሳተፉበት የ2015 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሁለተኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 61 ነጥብ በመሰብሰብ አንደኛ ሆኖ የዋንጫ ባለቤትነቱን ሲያረጋግጥ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ52 ነጥብ ሁለተኛ፣ ሐዋሳ ከነማ ደግሞ በ51 ነጥብ ሶስተኛ በመሆን አጠናቀዋል፡፡
በሐዋሳ እና ባህርዳር ከተሞች በተካሔደው የሁለት ዙር ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካደረጋቸው 24 ጨዋታዎች 16 ጨዋታዎችን በማሸነፍ፤ በአራቱ አቻ ወጥቶ እንዲሁም በአራት ጨዋታዎች ተሸንፎ በድምሩ 52 ነጥብ እና 36 ንፁህ ጎል መሰብሰብ ችሏል፡፡
በውድድር ዓመቱ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጠቃላይ 11 ጎሎች ብቻ ተቆጥረውበት ከሁሉም የሊጉ ክለቦች ዝቅተኛ ጎል በማስተናገድ ጠንካራ የተከላካይ ክፍል ያለው መሆኑን አስመስክሯል፡፡
ክለቡ ካስቆጠራቸው ጎሎች መካከል ትንቢት ሳሙኤል ዘጠኝ ጎሎች ከመረብ በማሳረፍ የክለቡ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ስትሆን ምንትዋብ ዮሐንስ በስምንት ጎል ትከተላታለች፡፡
ባለፈው እሁድ በተከናወነው የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ ለአሸናፊ ክለቦች የዋንጫ እና የሜዳሊያ ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ለምስጉን ዳኞች እና ኮሚሽነሮች እንዲሁም ለሊጉ ውጤታማነት አስተዋጽኦ ላደረጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል፡፡
በውድድር ዘመኑ ሁሉም ተጫዋቾች እንደቡድን በጋራ በመጫወት እንዲሁም የአሰልጣኞች አባላትም ተናበው በመስራት ይህ ውጤት እንዲመጣ ጉልህ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሲሆን የክለቡ ቦርድ አመራሮች፣ የክለቡ ጽ/ቤት፣ ደጋፊዎችና መላ የስፖርት ቤተሰቡ የማይተካ ሚና ተጫውተዋል፡፡
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ክለብ ባለፈው ዓመት በተካሔደው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ በተመሳሳይ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 02 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
በጥገና ሥራ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማዳን ተችሏል
---///---
በአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ አቅም በተከናወነ የጥገና ሥራ ከ250 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በላይ ማዳን መቻሉን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ፡፡
ኃላፊዋ ወ/ሮ ዓይናለም ወ/ሚካኤል እንደተናገሩት በተለያዩ ችግር ምክንያት ቆመው የነበሩ የንፋስ ተርባይኖችን በተቋሙ የጥገና ባለሙያዎች መጠገን ተችሏል።
የንፋስ ተርባይኖቹን ለጥገና ከባድ የሚያደርጋቸው በ 65 ሜትር ከፍታ በመገኘታቸውና ለመውጣትና ለመውረድ አስቸጋሪ በመሆኑ ነው፤ ይህንንም 20 ፎቅ ያለውን ህንፃ ቀጥ ባለ መሰላል ከመውጣትና መውረድ ጋር አነጻጽረውታል፡፡
ተርባይኖቹ ሁልጊዜም ኃይል ማመንጨት እንዲችሉ ችግሮች ከመከታቸው በፊት የቅድመ መከላከል የጥገና ሥራ እንደሚሰራ፣ ችግሮች እንደተከሰቱ ወዲያውኑ የሚከናወን የጥገና ሥራ መኖሩን እና ችግሮቹ ከተከሰቱ በኋላም ሳምታዊ የፍተሻ እንደሚካሄድ ኃላፊዋ ገልፃዋል፡፡
እንደ ኃላፊዋ ገለፃ ጣቢያው ባሉት 38 ቴክኒሺያንና መሐንዲስ የጥገና ባለሙያዎች የጥገና ሥራውን በማከናወኑ ለውጭ ባለሙያዎች ሊያወጣ የሚችለውን ከ250 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በላይ ማዳን ተችሏል።
ጣቢያው ያዳነው ወጪ ኃይል ማመንጫው ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ቢሆንም በዋናነት ግን ከባለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ በተደረጉ የጥገና ስራዎች መሆኑን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል፡፡
የአዳማ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሀገራችን ካሉ የነፋስ ኃይል ማመንጫዎች ቀዳሚ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዋ እያንዳንዳቸው 1 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የሚያመነጩ 34 ተርባይኖች ሲኖሩት በድምሩ 51 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው።
አዳማ አንድ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ህዳር 22 ቀን 2005 ዓ.ም. በቀድሞ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃ/ማርያም ደሣለኝ ተመርቆ ሥራ መጀመሩ ይታወሣል::
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 02 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
በስርቆት የተነሳ በቢሾፍቱ ከተማ በከፊል እንዲሁም በዙሪያው ባሉ ፋብሪካዎች ደግሞ ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጧል
………////………
ከቢሾፍቱ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ከተማዋና በከተማዋ ወዳሉት ፋብሪካዎች የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ሁለት ምሰሶዎች በሌቦች ተቆርጠው በመውደቃቸው ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡
በዘርፉ የማዕካላዊ ሪጅን 2 ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንዳስታወቁት ምሰሶዎቹ ተቆርጠው በመውደቃቸው በቢሾፍቱ ከተማ በከፊል እንዲሁም በዙሪያው ያሉ ፋብሪካዎች ደግሞ ሙሉ በሙሉ ኃይል አጥተዋል።
በመሆኑም ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ ለቢሾፍቱ ከተማ በከፊል፣ በአካባቢው ካሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች መካከል ለስቲሊ አር ኤም፣ ሲ ኤንድ ኢ እና አቢሲኒያ የብረት ፋብሪካዎችን ጨምሮ ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ እና ወደ ኢላላ ገዳ የሚሄዱ መስመሮች ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን አቶ አለማየሁ ገልፀዋል፡፡
ምሰሶዎቹ ተቆርጠው የወደቁበት አካባቢ ከመኖሪያ መንደር እና ከአንድ የብረት ማቅለጫ ፋብሪካ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ መሆኑ ድርጊቱን አስደንጋጭ እንዳደረገው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊቶችን በየአካባቢው ያሉ የመስተዳደር አካላት መከላከልና ማስቆም የማይችሉ ከሆነ ዝርፊያ የተፈፀመባቸው አካባቢዎች ለረጅም ጊዜ ኃይል ሊያጡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል ብለዋል።
የኃይል መቋረጡን በጊዜያዊነት የእንጨት ምሰሶዎችን በመትከል ለማስተካከል ጥረት መጀመሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ ችግሩ እስኪቀረፍ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የፋብሪካ ባለቤቶች በትዕግስት እንዲጠብቁ እና ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል፡፡
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ግንቦት 01 ቀን 2015 ዓ.ም
15 537
ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ የክትትልና ድጋፍ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል
………///………
ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የሚገነባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ፣ ወጪና ጥራት እንዲከናወን ለማድረግ ተገቢው የክትትልና ድጋፍ ሥራ እንዲሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ።
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉማሜ ወረዳ ሞጆ ከተማ አካባቢ በተቋሙ ራስ ኃይል እየተገነባ የሚገኘውን የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሥራ እንቅስቃሴ በመስክ ተገኝተው ገምግመዋል።
የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ከዚህ በፊት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ሲከናወኑ ከነበሩበት አሰራር በመውጣት በአዲስ የአሰራር ሥርዓት ማኑዋል መሠረት የተጀመረ በመሆኑ ሂደቱን በቅርበት በመከታተል በወቅቱ መፍትሔ ለመስጠት የመስክ ጉብኝቱ መካሄዱን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ፕሮጀክቱን ውጤታማ ለማድረግ የግንባታ ሥራው በማኑዋሉ ላይ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት መከናወን አለበት።
ፕሮጀክቱን በስምምነቱ ላይ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ማጠናቀቅ ከተቻለ በቀጣይ ከፋይናንስ አቅራቢዎች ገንዘብ በማፈላለግ ሌሎች ሥራዎች ለውጭ ሥራ ተቋራጮች ሳይሰጡ በራስ አቅም እንዲከናወኑ ለማድረግ እና በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ለመስራት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ከጅምሩ በጥሩ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው ከግንባታ ሥራው በተጓዳኝ የሠራተኞችን ደህንነትና ጤንነት ለመጠበቅ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል።
የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ፣ ንብረቶችን የማስተዳደር፣ የቢሮና የዕቃ ግምጃ ቤቶችን የማደራጀቱ ሥራ አዲሱን ማኑዋል መሠረት ባደረገ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል።
እስከ አሁን ድረስ ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሃ ግብርና በጀት መሠረት እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ፕሮጀክቱ የሚከናወንበትን ቦታ የማጽዳት፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍሉ የሚገነባበት ቦታ የመሬት ቆረጣ እና የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤት ቁፋሮ ሥራ መጠናቀቁንና የስዊችያርድ እና ሌሎች የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የሚተከሉበት የመሠረት ቁፋሮ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያው ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በተቋሙ የራስ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ቢሮ የሚከናወን ሲሆን በማማከር ሥራው ላይ ደግሞ የተቋሙ ኢንጂነሪንግ ቢሮ እየተሳተፈ ይገኛል።
የግንባታ ሥራውን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን ለዚህም በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን የሚሸፈን ከ259 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለታል።
“ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዚያ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
