የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Ir al canal en Telegram
5 344
Suscriptores
-22624 horas
-2 2007 días
-2 65830 días
Archivo de publicaciones
Good news : ከነገ ጀምሮ በሳምንት 12 በረራዎች በማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን የመመለሱ ስራ እንደሚከናወን ተገለፀ
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራና 14 አባላት ያሉት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በሳውዲ ዓረቢያ ሽሜሲ የማቆያ ማዕከል የሚገኙ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን ወደ አገር መመለስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የሳውዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካ ግዛት ሀላፊ ከሆኑት አምባሳደር መአዚን ቢን ሀማድ አል-ሐምሊ ጋር ተወያይተዋል።
ዜጎቻችንን ወደ አገር ቤት ለመመለስ ከሚሰራው ስራ ባሻገር በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎች የኢትዮጵያ እና ሳኡዲ አረቢያን ግንኙነት ለማጎልበት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል።
በሁለቱ አገራት መካከል የተቋማት ጉድኝት እንዲጠናከር የኢትዮጵያ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አብራርተዋል።
ዜጎችን ወደ አገር የማስመለስ ዘመቻን አስመልከቶ ከጅዳ በሳምንት 9፣ እንዲሁም ከሪያድ 3 በረራዎች በድምሩ 12 በረራዎች በማድረግ በቀጣዮቹ 4 ወራት ዜጎችን የመመለስ ስራ እንደሚሰራ ተገልጿል።
ክቡር አምባሳደር መአዚን በበኩላቸው ዜጎቻችን በሰላም ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ያላቸውን መልካም ምኞት ገልጸው፤ ህጋዊ የሥራ ስምሪት በማድረግ ሁለቱንም ወዳጅ አገራት ተጠቃሚ ማድረግ የሚገባ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።
ክብርት አምባሳደር ብርቱካን በማዕከሉ የሚገኙ ዜጎቻችን ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ፤ ሁሉም ዜጎች እንደምዝገባቸው ቅደም ተከተል ወደ አገር ቤት የሚሸኙ መሆኑን ገልፀውላቸዋል።
#MFAEthiopia 🇪🇹
"የኢትዮጵያና እና የሜክሲኮ የወዳጅነት ታሪክ"
🇪🇹 🇪🇹 🇪🇹 = 🇲🇽 🇲🇽 🇲🇽
ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ግርማዊ ለቀዳማዊ ዓፄ ኃይለሥላሴ በጄኔቫ ሲውዘርላንድ ተገኝተው በሀገሬ ላይ ግፍ እና ወረራ እየተፈፀመብን ነው ብለው ንግግር ሲያደርጉ.....
በወቅቱ League of Nation ላይ የተገኙት የአለም ሀገራት መሪዎች ጉዳዮን ችላ በማለት ፊታቸዉን ባዞሩበት ወቅት ወረራውን ከተቃወሙ አምስት ሃገራት መካከል አንዷ ሜክሲኮ ነበረች።
ቀሪዎቹ አራት አገራት አሜሪካ፥ ሶቭየት ህብረት፥ ኒው ዚላንድ እና ሀይቲ ነበሩ።
የሜክሲኮ ህዝብና መንግሥት በኢጣሊያ ወረራ ዘመንና ኤርትራን ከኢትዮጵያ ጋር ለማዋሃድ በተደረገው የዲፕሎማሲ ዘመቻ ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ለፈጸሙት አኩሪ ተግባር አደባባዩ በሜክሲኮ ስም እንዲጠራ ተወስኗል።
ይህን የምንግዜም አጋርነቷን ላሳየችው ሜክሲኮ ለዉለቷዋ መታሰቢያ እንዲሆን ታህሳስ 3 ቀን 1951 ዓ.ም የኢትዮጵያ መንግስት የቀድሞ ማይጨው አደባባይ ተብሎ ይጠራ የነበረው ሜክሲኮ አደባባይ ብሎ በመሰየም ሐውልቱ አቁማ ነበር።
እ.ኤ.አ በ 1954 ሜክሲኮ በመሀል ከተማዋ በዋና ጎዳና ላይ የሚገኘውን አንድ አደባባይ Plaza de la Ethiopia/የኢትዮጵያ አደባባይ በማለት ሰይማለች።
ይህ ምስል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ደጃዝማች ዘውዴ ገ/ሥላሴ የሜክሲኮ አደባባይን መርቀው በከፈቱበት ወቅት ሲሆን ወቅቱም በወርሃ ታህሳስ 1950 ዓ.ም ነበር
#ታሪክን_ወደኋላ
Join Our Channels
👇
በህገ ወጥ ድርጊት ላይ የተሠማሩ ፅንፈኞች በሠራዊቱ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮማንዶ ክፍለ ጦር ሬጅመንት በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ የሠራዊቱን ትጥቅ በመግዛት ለማስኮብለል እና ለማፍረስ የተሰማሩ የፅንፈኛው ፋኖ ሴሎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሬጅመንት አዛዥ ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ አስታውቀዋል፡፡
ድርሳን ከተባለው የፅንፈኛው እና ዘራፊው ቡድን መሪ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው ሰራዊቱን በጥቅም በማታለል ለማስኮብለል የመጡትን 20 የቡድኑን አባለት የሬጅመንቷ ሠራዊት አባለት ለመኮብለል ዝግጁ መሆናቸውን በመግለፅ እና የሽያጭ መሳሪያ በማቅረብ በልዩ ክትትል በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸውን ገልፀዋል።
ሠራዊቱ በተጠቀመው ጥበብ በተሞላበት ዘዴ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የሬጅመንቷ አዛዥ ተናግረዋል።
አብዛኞቹ የቡድኑ አባለት የፈፀሙት ድርጊት አስፃያፊና አስነዋሪ ተግባር እንደሆነ በመግለፅ ፅንፈኛው ቡድኑ የሚያራምዳቸው የከሰረ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ የአማራን ህዝብ የማይመጥን በመሆኑ ህዝቡ በዚህ ቡድን ከመታላል እራሱን እንዲጠብቅ አሥገንዝበዋል።
መሳሪያ ሊገዛ የነበረው የፅንፈኛ ቡድኑ አባል ወንዴ መኮንን ድርጊቱን በመፈፀሙ መፀፀቱን ገልፆ ፅንፈኛ ቡድኑን በሎጅስቲክ ለመርዳት በማሰብ ከግብረ- አበሮቹ ጋር በመሆን መሳሪያ በግዥ ለመሰብሰብና ለቡድኑ አቅርቦት ለማሳለጥ በማሰብ ከቴፒ ተነስቶ ወደ ደሴ ከተማ መምጣቱን ገልጿል።
ይህን ዕኩይ አላማውን ሳያሳካ በሬጅመንቷ አባላት ልዩ ጥበብ በቁጥጥር ስር መዋሉንና የሬጅመንቷ አባላትም በጥሩ ህዝባዊነት በእንክብካቤ ከሚበሉት ቀለባቸው እያካፈሉ በፍቅር ይዘውኝ ቆይተዋል ብሏል።
ሌላው የቡድኑ አባል ፋንታው ደስአለው ከዚህ በኋላ በአማራ ክልል ውስጥ የሚደረገው አላማና ግብ አልባ የግለሰቦች ጥቅም ማስጠበቂያ ጦርነት እንዲቆምና በበረሃ ትርጉም የሌለው መስዋዕትነት እየከፈሉ ለሚገኙ ጓደኞቹ ይበቃችኋል የሰላም ጥሪን ተቀብላችሁ ወደ ሰላም ኑ ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
ሀገር ጠባቂ ከሆነው ለሀገሩ ከሚሞተው መከላከያ ጋር የሚደረገው ግጭት እንደሀገር አደጋ ላይ የሚጥለን እኛንም ታሪክ አልባ ትውልድ የሚያደርገን በመሆኑ የፅንፈኛው አካሃድ መቆም አለበት ሲል መልዕክት አስተላልፏል።
ሻምበል ታሪኩ ሻሜቦ ቡዱኑ 01 መትረየስ ፤ 01 ስናይፐር ፤ 04 ክላሽና የደረት ትጥቅ ከእነ ቦንቦች በመግዛት ሠራዊቱን ለማፍረስ ተዘጋጅቶ እንደነበርና በሬጀመንቷ አባላት ጥበብ የተሞላበት ቴክኒክ የፅንፈኛውን ቡድን እቅድ ማክሸፍ መቻሉን ገልፀዋል።
ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሰን
"እኛ ላይ መዝመቱን ይዝመቱ ግን ለምን?"
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም
በጋዳፊ ዘመን ዘለግ ላሉ ዓመታት የተከበሩ ጄኔራል ሆነው ሀገራቸውን ሊቢያ አገልግለዋል።ጄኔራል አፍጣር።
የጋዳፊ አመራር ስጋት የደገነባቸው ምዕራባዊያን በስመ "የአረብ አብዮት" ሴራ የህዝብን ስሜት ክፉኛ በማናር ሊቢያ በአመፅ የተናጠችበት ሴራ ምስጢረ-ብዙ ነበር።
የጋዳፊን በተቃውሞ መዳከም ተከትሎ በውስጥም በውጭም ጦር የተሰበቀበት የሊቢያ ሰራዊት ሲበተን የተወሰነ ጦር ይዘው በራሳቸው መንገድ አሁንም የሚንገታገቱት ጄኔራል አፍጣር በአንድ ወቅት በሚዲያ እንዲህ ሲሉ ተናገሩ "ሊቢያ ዛሬ ላይ ለዚህ ሁሉ ውድቀትና በተቃርኖ ክረት የማይግባቡ ሃይሎች መፈንጫ ለመሆን የበቃችው በጋዳፊ ከመንበረ ስልጣን መወገድ ሳይሆን በሊቢያ ጦር መፍረስ ሳቢያ ነው" አሉ።
እውነታቸውን ነው።በአንድ ሀገር ላይ በርካታ ፍላጎቶች አሉ። እነዚህን ፍላጎቶች አመጣጥኖ በጋራ ሀገራዊ ብሄራዊ ጥቅምና ፍላጎት አግባብቶ እንደ ሀገር ጠንክሮ ለመቀጠል የግድ ስርዓት ያስፈልጋል።
ስርዓትን ለማስፈን ደግሞ ሃይል የግድ ነው።የአንድ ሀገር ዜጎች የጋራ ሃይል ሊሆን የሚችለው ደግሞ የሀገሩ መከላከያ ሃይል ነው።
ይህ ሃይል በየትኛውም የስርዓት ልውውጥ እና የመንግስታት መቀያየር ሂደቶች ውስጥ በቋሚነት ጸንቶ የሚቀጥል ቋሚና ሀገር አስቀዳሚ የሀገር ህልውና አስጠባቂ ሆኖ መቀጠል አለበት።
ይህ በሌለበት ሁኔታ የየትኛውም ወገን ፍላጎት እውን ሊሆን አይችልም ብቻ ሳይሆን አሸናፊ የሌለው ከባድ የእርስ በርስ ግጭትና የቀውስ አዙሪት ውስጥ መዘፈቅ ስለመሆኑ ቀደም ሲል ያነሳነው የሊቢያ ጉዳይ ሁነኛ ማሳያችን ነው።
ታዲያ አሁን ላይ በሽብሩም በፅንፈኝነቱም ጎራ አካኪ ዘራፍ ባይ አጉራ ዘለሎች ስለምን እኛ የኢትዮጵያ ምልክቶቹ፣ እኛ ከብሄርም ከፖለቲካም ውግንና ገለልተኞች ሆነን ኢትዮጵያን ለማጽናት ለህይወት የማንሳሳ ወታደሮች ላይ ጩኸት ለምን አስፈለገ?
ጉዳዩ ብዙ አልፊ ብዙ አመራማሪ አይደለም።
አዝማቾቻቸው የሰራዊት ፍርሰት የሚያስከትለውን ሀገራዊ የማይታከም በሽታ እና ሀይ ባይ የማይኖርበት የማንም መፈንጫ የመሆንን ነገር እንደሚያዋልድላቸው ያውቁታልና ለዚህ መሻታቸው አበክረው እንዲሰሩ በአጽንኦት ስላዘዟቸው ነው።
ታዲያ ግን የዘነጉት ነገር እኛ ኢትዮጵያዊያንና ኢትዮጵያን ብቻ ባይ የሀገር ዋልታ ማገር እና ጋሻ መከታዎች በጫጫታ የምንበረግግ ነን ወይ? በስም ማጥፋትስ በቀላሉ ሸብረክ የምናውቅ ነን ወይ?
እኛ የአያት ቅድመ-አያቶቻችን መንፈስ ወራሾች ነን።እኛ በሞያዊ ዲሲፕሊናችን ከብረት ጠንክረን የቆምን ነን።እኛ እራሱን በተለያየ የልዩነት ቋት ከትቶ መርጦ አልቃሽ የማይነቀንቀን የኢትዮጵያና የምልዓተ-ህዝቧ ሁሉ እኩል አገልጋዮች ነን።
እናም መሻታቸው መቼም እውን እንዳይሆን በማድረግ ቀጥለናል እንቀጥላለንም።
አንድነቷ የጸና፣ሰላሟ የተረጋገጠ፣በታሪኳ ልክ ከፍ ብላ በኩራት የምትታይ ኢትዮጵያችን እውን እስክትሆን የትኛውንም መስዋዕትነት ደስ እያለን እንከፍላለን። አሸናፊ ሆነን ሀገር ወገን እንደምናኮራም እርግጠኞች ነን።
በአስቻለው ሌንጫ
የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንትና የጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ ክቡር ሳልቫ ኬር ማያርዲት የሀገሪቱን ታላቁን ኒሻን ለኢፌዴሪ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አበረከቱ ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
በደቡብ ሱዳን ብሄራዊ ቤተ-መንግስት በተካሄደው ታላቅ ስነ-ስርዓት የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት እንዲሁም የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለደቡብ ሱዳን ህዝብ ነፃነትና ሉአላዊነት መከበር ለከፈሉት ታላቅ የደም መስዋዕትነትና ድጋፍ ክብር ይገባቸዋል በማለት የሀገሪቱን ታላቅ ኒሻን ማበርከታቸው በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገልጿል ።
ክቡር ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኬር ይህንን ታላቅ ኒሻን በቤተ-መንግስታቸው ሲያበረክቱ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በቸገረን ጊዜ ሁሉ መጠጊያችን መጠለያችን ከመሆኗም በላይ ለዚህ ሀገራዊ ነፃነታችን ክብር የሆኑ በሺህዎች የሚቆጠሩ ልጆቿን ህይወት ጭምር በመክፈል እንደሀገር እንድንቆም ያደረጉ ውለታቸውንም መቼም ከፍለን የማንጨርሰው ባለውለታችን ናቸው ብለዋል።
ዛሬም ድረስ የሠራዊታችንን አቅም በመገንባት የውሰጥ ችግር ሲያጋጥመን ሮጠው በመምጣት ችግራችንን የሚጋሩ ኢትዮጵያዊያን ናቸው ሲሉም ተናግረዋል ።
ክቡር ፕሬዝዳንት ሳልቫኬር ዛሬም ከጎናችን ያልተለዩና የቁርጥ ቀን ወንድሞቻችን ከመሆናቸውም በላይ በደም የተሳሰርን ማንም ሊፈታው የማይችል የአንድ ቤተሰብ ልጆች መሆናችንን የሚያረጋግጥ ሽልማታችን እንደሆነ መላው የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን ህዝብ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን ብለዋል።
በተጨማሪም ይህንን ታላቅ ሽልማት ለጀግናው የኢፌዴሪ የመከላከያ ሠራዊት የበላይ ሃላፊና የምስራቅ አፍሪካ ፊልድ ማርሻል ለሆኑት ለክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በደቡብ ሱዳን ህዝብ ስም ሳበረክት ታላቅ ኩራት ይሰማኛል በማለት ተናግረዋል።
በስነ- ስርዓቱ ላይ የሀገሪቱ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፣ የሀገሪቱ የደህንነት ከፍተኛ ሃላፊዎች ፣ ጄኔራል መኮንኖችና የኢፌዴሪ መከላከያ ጄኔራል መኮንኖች መገኘታቸውን የጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፅህፈት ቤት ያደረሠን መረጃ ያመላክታል።
#ዳውን ሲንድረም (Down Syndrome)
1. ዳውን ሲንድረም (Down syndrome) #ምንድን ነው?
- ዳውን ሲንድረም ዘላቂ የሆነ እና የአፈጣጠር የጤና እክል ነው። ከዚህም ጋር ተያይዞ ከቀላል እሰከ ከባድ ተጓዳኝ የጤና ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል። ለምሳሌ የልብ፣ የደም፣ የስርዐተ-ልመት እና ሌሎችም
ዳውን ሲንድረም የክሮሞሶም (chromosome) ችግር ሲሆን ክሮሞሶም የህዋስ (cell) ቅንጣት ክፍል ነው ይህ ቅንጣት ክፍል የሰውነት ክፍሎች የሚሰሩበትን መልዕክት ይይዛል። ዳውን ሲንድረም የተጠቃ ሰው ትርፍ ወይም ተጨማሪ የዘረ መህል ቅንጣት (extra chromosome ) ይኖራቸዋል። ይህም ችግር ያለባቸውን ግለሰቦች ከሌለባቸው ሰዎች የተለዩ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል።
በሕክምናው አለም ለምን አንዳንድ ህፃናት በዚህ ችግር እንደሚጎዱ በርግጠኝነት ባይታወቅም የእናቶች እድሜ መጨመር የዚህ የጤና እክል ያለባቸው ልጆች የመውለድ እድልን እንደ ሚጨምር ይታወቃል።
2. #ዳውን ሲንድረም ምልክቶቹስ?
ዳውን ሲንድረም ያለበት/ባት ህፃን እደተወለደ የሚከተሉትን አካላዊ ምልክቶች ይታዩባቸዋል
- ጠፍጣፋ የፊት ገፅታ
- አንገት ኣካባቢ ድርብርብ ቆዳ
- ወደ ላይ የተንሸዋረሩ አይኖች
- ልል ሰውነት ጡንቻ
- ቀጥ/ወጥ የሆነ የመዳፍ መስመር
እያደጉ ሲመጡ የሚከተሉትን ተጨማሪ አካላዊ ምልኽቶችን ሊያሳዩ ይችላል።
- ትንሽ ራስ ቅል (small head)
- ያንገት ማጠር
- ትንሽ ወይም ያልተለመደ የጆሮ ቅርፅ
- አጭር እና ሰፊ የእጅ መዳፎች
- ቦርጫም ሰውነት
3. #ዳውን ሲንድረም #ምርመራዎች?
► ከወሊድ በፊት/ በእርግዝና ጊዜ:- የተለያዩ ምርመራዎችን በማድረግ በዕርግዝና ወቅት ፅንሱ ዳውን ሲንድረም እንዳለበት ወይም እንደሌለበት ማረጋገጥ ይቻላል።
► ከወሊድ በኃላ:- በሚታዩ የአካል ምልክቶች ማወቅ እና በደም ምርመራ ማረጋገጥ ይቻላል።
4. ዳውን ሲንድረም ምን አይነት የአዕምሮ እድገት ውስንነት ችግር ሊያስከትል ይችላል?
በእድገታቸው ወቅት እራሳቸውን ችለው መቀመጥ፣ መራመድ እና አፍ የሚፈቱበት እድሜ ይዘገያል ሁሉም ሊባል በሚያስችል ደረጃ የዳውን ሲንድረም ተጠቂ ሰዎች የአዕምሮ ዘገምተኝነት (low IQ) ያጋጥማቸዋል፤ አልፎ አልፎም የስነ-ባህሪ ችግሮች ይኖራቸዋል።
5. ዳውን ሲንድረም ያለበት ሰው የተለያዩ ተጎዳኝ በሆኑ የጤና ችግሮች ሊታመም ይችላል እነሱም:-
- የልብ
- የደም
- የሰውነት በሽታ ተከላካይ (immune system)
- የስረዐተ ልመት (digestive system)
- ሆርሞን
- የመተንፈሻ አካል
- የአይን እና መስማት
- የቆዳ
ሁሉም ዳውን ሲንድረም ተጠቂዎች ከላይ የተዘረዘሩት በሙሉ ይኖርባቸዋል ማለት ሳይሆን በተለያየ ደረጃ በነዚ ተጎዳኝ የጤና አክሎች ሊጠቁ ይችላሉ ለማለት ነው።
6. እርዳታ ያስፈልጋቸዋል? አዎን!
ዳውን ሲንድረም ያለበት ህፃን ቋሚ የህክምና ክትትልና ድጋፍ ይሻል። በተለይ ከላይ የተዘረዘሩት ተጎዳኝ የጤና እክሎችን በየጊዜው ማየትና (screening) ተገቢውን ህክምና ማድረግ ተገቢ ነው።
7. ዳውን ሲንድረም እንዴት ይታከማል?
ዳውን ሲንድረም በመሰረቱ ማከም ባይቻልም አብዛኛወቹ ተጓዳኝ የጤና ችግሮች በህክምና ሊድኑ የሚችሉ ናቸው ለምሳሌ የልብ ችግር በቀዶጥገና (surgery) የአይን ችግር በዐይን መነጵር መታከም ይችላል።
8. ዳውን ሲንድረም የወደፊት ህይወታቸውስ?
ብዙሃኑ የዳውን ሲንድረም ተጠቂዎች ደስተኛና ጥሩ ህይወት መኖር ይችላሉ። ነገርግን አብዛኛውን ጊዜ የቤተሰብ ክትትልና ድጋፍን ይሻሉ።
9. ለማንኛውም ተያያዥነት ላላቸው ጥያቄዎ ከጤና ባለሙያ የሚየገኙት መረጃ ተመራጭ ነው።
#በልዑል ወልዴ
መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
ዋትሳፕ እንደቴሌግራም ቻናል ማስከፈት ጀምሯል እኛም ቻናላችንን በWhatsap ከፍተናል ገብታችሁ ጎብኙን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ዋትሳፕ እንደቴሌግራም ቻናል ማስከፈት ጀምሯል እኛም ቻናላችንን በWhatsap ከፍተናል ገብታችሁ ጎብኙን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ዘሜ ሌላ የትግል ሜዳ ላይ ናት ቂቂቂቂቂቂ😆😆😆😆
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ሰሞኑን የተፈጠረውን ችግር እንደአጋጣሚ ተጠቅመው ደንበኞችን ሊያጭበረብሩ የሚሞክሩ አሉ ‼️
🗣የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰሞኑን የተፈጠረውን ችግር እንደአጋጣሚ በመጠቀም ሊያጭበረብሩ ከሚሞክሩ ግለሰቦች ደንበኞቹ ራሳቸውን እንዲጠብቁ አስጠነቀቀ፡፡
አጭበርባሪዎች ሰሞኑን ከሲስተም ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ችግር እንደ አጋጣሚ ለመጠቀም ሙከራ በማድረግ ላይ መሆናቸውን እንደደረሰበት ባንኩ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
እነዚህ አጭበርባሪዎች በአብዛኛው ከባንክ የደወሉ በማስመሰል “የተዘጋ ሂሳባችሁን እንክፈትላችሁ”፣ “ሂሳባችሁ እንዳይዘጋ የምንልክላቹሁን ኮድ አስገቡ” የሚል የማጭበርበሪያ ዘዴ በመጠቀም የዘረፋ ሙከራ በማድረግ ላይ እንደሆኑም ጠቁሟል።
ሆኖም ግን ባንኩ ስልክ ደውሎ ስለ ሂሳብዎ መረጃ የሚጠይቅበት፣ ሂሳብ የሚከፍትበትም ሆነ የሚዘጋበት አሰራር እንዲሁም ደንበኞች እንዲጠቀሙበት የሚልከው ምንም አይነት ኮድ የለም ብሏል፡፡
በመሆኑም ማንኛውም የባንኩ ደንበኛ መሰል ሁኔታ ሲገጥመው ምንም ዓይነት እርምጃ ከመውሰድ በመቆጠብ በአቅራቢያ ወደሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ አሊያም በ951 ለባንኩ የደንበኞች ጥሪ ማዕከል በመደወል ስለሁኔታው መረጃ መጠየቅ እንዳለበት አስገንዝቧል፡፡
ቭላድሚር ፑቲን ለቀጣይ 6 ዓመታት ሩስያን መምራት የሚያስችላቸውን የምርጫ ውጤት ማስመዝገባቸው ተነገረ
ሩስያን በፕሬዜዳንትነት እየመሩ የሚገኙት የቀድሞው የKGB ሰላይ ቭላድሚር ፑቲን በሀገራቸው የተካሄደውን የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ በከፍተኛ ብልጫ ማሸነፋቸውን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ባለፉት 3 ቀናት በመላ ሩስያ ህዝቡ ድምፅ ሲሰጥ ቆይቷል።
የ71 ዓመቱ ፑቲን " ጠንካራ ተቀናቃኝ አልገጠማቸውም " በተባለው በዚህ ምርጫ ከ87% በላይ ድምፅ በማግኘት ሀገሪቱን በፕሬዜዳንትነት መምራት እንዲቀጥሉ የሚያስችላቸውን ውጤት እንዳገኙ ተገልጿል።
ፑቲን ለቀጣይ 6 ዓመታት ሩስያን ይመራሉ።
በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲሁም በፕሬዜዳንትነት ረጅም ዓመታትን የሀገሪቱን ዋነኛ ስልጣን በመያዝ እየመሩ የሚገኙት ቭላድሚር ፑቲን ይኸኛው የ2024ቱ ምርጫ ለ5ኛ የስልጣን ዘመን ያሸነፉት ምርጫ ነው።
የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ ብሎም የአለም ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ፦
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 08 ቀን 2016 ዓ.ም
ሠላም ከምንም በላይ የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሠጠው የሁሉም ነገር መሠረት ነው። ለዚህም ነው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለተሠለፈበት ዓላማ ፅኑ አቋም በመያዝ በየትኛውም የሀገራችን መልክዓ ምድር ማንኛውንም ምድራዊ ፈተና አልፎ ሠላም የሚያረጋግጠው ።
የኢትዮጵያ ሠራዊት ከሀገሩ አልፎ ለአፍሪካ ብሎም ለአለም ሠላም ዕውን መሆን በተለያዩ የአለም ሀገራት ለሠላም ማሥከበር ተልዕኮ በመሠማራትና በርካታ ፈተናዎችን አልፎ ተልዕኮውን በውጤት በማጠናቀቅ ከአለማችን ተመራጭ ሠራዊት በመሆን የሠላም አምባሳደርነቱን በተደጋጋሚ ያረጋገጠ ጠንካራ ሠራዊት ነው።
ኢትዮጵያን በየትኛውም አጋጣሚ ሠላሟን ለማሣጣት ዕድገቷን ለማደናቀፍ ከውስጥም ከውጪም ትንኮሳዎች ሲሠነዘሩም የዜጎችን ሰላም እና የሃገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ለሠንደቅ ዓላማው ክብር የትኛውንም አይነት ምድራዊ ፈተና አልፎ ግዳጁን በድል የሚፈፅም የህዝብና የሀገራት ኩራት የሆነ ሠራዊት መሆኑ ተመሥክሮለታል።
ከጦርነት እንጅ ከሰላም ማትረፍ አይቻልም የሚል እሳቤ ያላቸው ፣ ያልተገባ ለህዝብም ለሀገርም የማይጠቅም ይልቁንም የዕድገት ማነቆ የሆነ ዘመኑን የማይመጥን ተግባር ላይ የሚጣዱ ሃይሎች ያሰቡትን ያህል ርቀት መሄድ እንዳይችሉ ሠራዊቱ ከህዝብ ጋር ሆኖ በተሳሳተ ስሌት የሚያደርጉትን ሴራ እያከሸፈም ይገኛል።
ሀገራችን ሠላሟ ተረጋግጦ ዕድገቷ እውን እንዳይሆን ካለፈው ዘመን ጀምሮ ያለእንቅልፍ የሚሠሩ ሴራ ሸራቢዎች የጥፋት እጃቸውን ለመዘርጋት ቢጥሩም፣ የተንኮል እጣታቸውን ቢቀሥሩም፣ እኛ ብቻ እንደግ የሚል አባዜ በተጠናወታቸው ሀገሮች የሚዘወሩ መሆናቸውን በውል መገንዘብ የግድ ይላል።
እነኝህ የአጭርና የረጅም ጊዜ የጥፋት አጀንዳ ቀርፀው የሚንቀሳቀሱ ሀገራት ኢትዮጵያን የጦርነት ቀጠና በማድረግ ህዝቦቿ ከመተማመን ይልቅ መጠራጠር ከመግባባት ይልቅ መቃረን ከአንድነት ይልቅ ልዩነት ውስጥ ገብተው ለዕድገት መሠረት የሆነው ልማት ላይ ትኩረት እንዳያደርጉ አሁንም ድረስ እንቅፋት መፍጠራቸውን ቀጥለውበታል።
የእነኝህን ፀረ ኢትዮጵያዊ አመለካከት እና ድርጊት የሚደገፉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ከቶውንም ቢሆን የማያስቡ ፣ለራሳቸው ጥቅም ብቻ ፊት የተሠለፉ ፣ በውጪ ጣልቃ ገብ ሀገራት የሚዘወሩ ራስ ወዳዶች በማንኛውም ጊዜ የጥፋት አጀንዳ ማራገብ የተሠለፉበት ዓላማ ነው።
ሥለሆነም ሁኔታዎችን በስክነት በመገንዘብ ፍላጎታቸው እንዳይሳካ የሀገር አፍራሽነታቸው ጉዞ እንዳይሠምር ማድረግ ከሁሉም ሠላም ወዳድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሚጠበቅ አሁናዊ ሥራ ሊሆን ይገባል ። በአለማችን በጦርነት ያደገ ከጦርነት ያተረፈ ሀገርም ህዝብም የለምና ለሀገራችን ሠላም በህብረት መቆም ያሥፈልጋል።
በውብሸት ቸኮል
በቱርክ የድሮን ውድድር ላይ የሚሳተፈው ወጣት ኢብራሂም አሊ ::
ፈጠራ || ባለፉት አመታት በኢትዮጵያ ከ28 በላይ የፈጠራ ስራዎች እና 6 የድሮን አይነቶችን የሰራው የፈጠራ ባለሙያ ኢብራሂም አሊ በሀገረ ቱርክ መማር ከጀመረ 1 ዓመት አስቆጥሯል:: በዚህም በቱርከኛ ቋንቋ 98 በማምጣት ወደ ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ትምህርት ያለፈው ወጣት የቱርክ ታዋቂ ድሮን አምራች እና ኢንጂነር በሆነው በሰልጁክ ባይራክታር የሚዘጋጀው የድሮን ውድድር ላይ ለመሳተፍ በዝግጅት ላይ ነው:: ከውድድሩም ባሻገር ሀገራችን ኢትዩጵያ ወደ ዲጂታል እያደረገች ያለውን ጉዞ ለማገዝ የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ እውቀቱን በመጠቀም ቱርክ ያሉ ሶፍትዌሮችን ወደ ወደ ሀገር በማስገባት የህዝቡን ኑሮ የማቅለል አላማ ሰንቋል:: ይህንንም ለማሳካት በዩኒቨርሲቲው ከሚገኙ ከሚመለከታቸው የቱርክ ፕሮፌሰር እንዲሁም የሶፍትዌር ድርጅቶች ጋር በመመካር ላይ ነው::
