የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Ir al canal en Telegram
5 344
Suscriptores
-22624 horas
-2 2007 días
-2 65830 días
Archivo de publicaciones
ለ70 ዓመታት በሰው ሰራሽ ሳምባ ሲተነፍስ የነበረው ሰው ሕይወቱ አለፈ፡፡
በቅጽል ስሙ ፖል ፖሊዮ ወይም ፖል አሌክሳንድር በመባል የሚታወቀው አሜሪካዊ በፖሊዮ ቫይረስ መጠቃቱን ተከትሎ ነበር ሙሉ ለሙሉ ህይወቱ የተቀየረው፡፡በተወለደ በስድስት ዓመቱ በፖሊዮ ቫይረስ የተጠቃው አሌክሳንድር ከ1952 ጀምሮ ከአንገቱ በታች ያሉት የሰውነት ክፍሎቹ መስራት ማቆማቸውን ተከትሎ በቴክሳስ ባለ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ህይወቱን ሲመራ ቆይቷል፡፡
ይህ ግለሰብ ከበጎ ፈቃደኞች በሚዋጣለት ገንዘብ በሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ በህይወት መቆየት የቻለ ሲሆን አዕምሮው መስራቱን ተከትሎ በሕግ የመጀመሪያ ድግሪውን ሲይዝ መጽሃፍም መጻፍ ችሏል፡፡ይህ ሰው ለ70 ዓመታት ከኖረበት ሰው ሰራሽ ብረት ውስጥ እያለ ህይወቱ ማለፉን ስካይ ኒውስ ዘግቧል፡፡
ፖል አሌክሳንደር ከአራት ዓመት በፊት በሰጠው ቃለ መጠይቅ በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሞትን እንደፈራ ተናግሮ ነበር፡፡ሞትን የፈራበት ምክንያት ደግሞ ኮሮና ቫይረስ በእድሜ የገፉ እና ከመተንፈሻ ህመም ጋር በተያያዘ ህመም ያለባቸውን የበለጠ ይጎዳል የሚለውን ዜና በመስማቱም ነበር፡፡
ብዙዎችን ከህይወቱ ያስተማረው ፖል አሌክሳንደር በርካቶች በሆስፒታል እየተገኙም ሲጎበኙት እና ሲያበረታቱት እንደነበር በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡
ፖል አሌክሳንደር ዓለም እንዲያውቀው እና በጎ ፈቃደኞች እንዲረዱት ያደረገው ክርስቶፈር ኡልመር እንዳለው "ፖል ሁሌም የሚታወስ ሰው ነበር፣ ታሪክህን ስላጋራሀን እናመሰግናለን" ሲል ገልጿል፡፡
እስላም ክርስቲያኑ ገጠመ ጦማቸው
ወደ አምላክ ለመሄድ ቀጠሮ እንዳላቸው
አምላክ ይሄን አይቶ ምነው በረዳቸው
የመቻቻል ነበር ጥንትም ትዳራቸው☪✝💚💛❤
ሃገራችንን ሰላም ያድርግልን 🙏
መድፈኞቹ የሊጉን መሪነት ተረከቡ !
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የሀያ ስምንተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉ መሪ መሆን ችለዋል።
የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ካይ ሀቨርትዝ እና ዴክላን ራይስ ከመረብ ማሳረፍ ሲችሉ ዊሳ የብሬንትፎርድን ግብ አስቆጥሯል።
እንግሊዛዊው አማካይ ዴክላን ራይስ በውድድር ዘመኑ ስድስተኛ የፕርሚየር ሊግ ግቡን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
ካይ ሀቨርትዝ ለመጀመሪያ ጊዜ በአራት ተከታታይ የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ግብ ማስቆጠር ችሏል።
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ስንተኛ ናቸው ?
1️⃣ አርሰናል :- 64 ነጥብ
1️⃣5️⃣ ብሬንትፎርድ :- 26 ነጥብ
ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?
እሁድ - ማንችስተር ሲቲ ከ አርሰናል
ቅዳሜ - በርንሌይ ከ ብሬንትፎርድ
ሰበር ዜና ‼️
የመከላክያ ሰራዊት ቀይ መለዮ ለባሽ አባል የነበረና ከመከላክያ ሰራዊት በመውጣት የእስክንድር የግል ጠባቂና ወጣቶችን መልማይ አሰልጣኝ የነበረው ግዛቸው ይቴ ከነ ግብራበሮቹ እርምጃ ተወስዶባቸው ተደምስሰዋል::
ግዛቸው ይቴ ከዚህ ቀደም የዘመነ ካሴ እና የማስረሻ ሰጤ ጠባቂ ሆኖ መቆቀቱ ይታወቃል::
ከአንዱ የማዕረግ ዕድገት ወደ ሌላኛው የምንሸጋገረው በተቋሙ መሥፈርትና ልኬት ነው !!
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም
የሠራዊት አባላት በአካል ብቃት በቅተን ለመገኘት፤ በታጠቅነው መሣሪያ ላይ ያለንን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ እንሠለጥናለን፡፡ በተለያዩ ሙያዎች ተገቢውን አቅም ለመጨበጥ እንማራለን፡፡ መፅሐፍ ብቻ ሳይሆን ሠማይና ምድሩን የብስና ባህሩን ጭምር በወታደራዊ ዕይታ በጥልቀት እናነባለን፡፡
የምንሠለጥነው የምንማረው ዘወትር ሥራን ህይወት አድርገን የምንኖረው ግላዊ መሻታችንን ለማሟላት ፤ጉልበታችንን ለማሳየት አሊያም በሌላ የራስ ምክንያት ሳይሆን ለተልዕኮ ስኬትና ለድል አድራጊነት ነው፡፡ በወታደራዊ ዕውቀትና ክህሎት ከፍ ስንል ማንንም ለመጉዳት ሳይሆን ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ለመጥቀም ነው፡፡
ዕድገትና ሹመት በግል ከሚሰጠን ጥቅም ለሀገር የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ይጎላል፡፡ ከፍ ስንል ሠንደቅ ዓላማዋ ከፍ እንዳለ ይኖራል ብለን የምናምን ሁሉም ስኬታችን ስኬቷ የሚሆን አደራ ጠባቂዎች ከራስ በላይ ያልን ዜጎች ነን፡፡
ከአንዱ የማዕረግ ዕድገት ወደ ሌላው የምንሸጋገረው በግልፅ መሥፈርትና ልኬት ነው፡፡የቆይታ ጊዜ አለው፡፡የላቀ የሥራ አፈፃፀም ግድ ይላል፡፡ሙያዊ ፍቅር ዲሲኘሊንና ወታደራዊ ስነምግባር ለድርድር አይቀርቡም፡፡የመሾሚያ ቦታም አንዱ ነው፡፡
እኛ የሠራዊት አባላት ታዲያ ይሄን ሁሉ መሥፈርት አልፈን ማዕረግ ስንሾም ወይም ስንሸለም ከደስታና ፈንጠዚያ ይልቅ ወደ ጥያቄ እንገባለን፡፡ ምን ባደርግ? ምን ብጨምር? ሀገር በሠጠችኝ ሃላፊነት ተቋሙ በሠጠኝ ሹመት ላይ ብቁ ሆኜ እገኛለሁ? ብለን ራሳችንን መልሱን እስክናገኝ ድረስ እንጠይቃለን፡፡
መልሱ ሲገኝ ሹመት ይበልጥ የሚያሠራ ትልቅ አደራ መሆኑን ተገንዝበን ይበልጥ እንተጋለን፡፡ አመራር በኛ በመከላከያ ሠራዊት አባላት እምነት የላቀ ሐላፊነት ትጋት የሚጠይቅ ቦታ መሆኑን አምነን መሄድ ያለብንን ያህል ወደፊት እንሄዳለን ፡፡ከፊታችን የሚጠብቀን ተጨማሪ ሥራ፣ እቅድና ትግበራ መሆኑ ይገባናል፡፡
ለኛ ሹመት ማለት ለተጨማሪ ሐላፊነት የተልዕኮ ስኬት ለድምር ተቋማዊ፤ ሁለንተናዊና ዘመናዊ ዝግጁነት መታጨት መትጋትና መብቃት ነው፡፡ሰምኑን የተሾሙትን የሠራዊታችን አባላት ብትጠይቋቸው ምላሻቸው ተመሣሣይ ነው፡፡ ምክንያቱም ትርጉሙን ሳይረዳ የተሾመበትን ምክንያት ሳያውቅ የበላይ አካል የሚያለብሰውን ማዕረግ ለመልበስ የሚሠናዳ ሠራዊት የለም፡፡
በፈይሳ ናኔቻ
የካራማራው ድል በአድዋው ቀና ኢትዮጵያዊ መንፈስ የተገኘ ድል ነው፡፡ ከግንባታ ሰነዶች ዝግጅትና ሥልጠና ሥራዎች ዳይሬክቶሬት
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የካቲት 26 ቀን 2016 ዓ.ም
ከጥንት ጀምሮ የጦርነት ታሪካችን ሁሉ መደምደሚያው ድል ማብሰር ነው፡፡ የዚህ ሚስጢሩ ደግሞ ለውጊያ የመታደማችን አካሄድ ሁሉ ያለ ልዩነት በፍፁም ኢትዮጵያዊ መንፈስ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡
ኢትዮጵያዊያን ሀገር ተወረረ ብሔራዊ ክብር ተገፈፈ፤ ድንበር ተገፋ ተብሎ መንግሥት ሲነገረው፤ ወራሪውን ጠላት በጀግንነት ለመፋለም በመትመም ይታወቃል፡፡ ይህ ደግሞ የአድዋና የአርበኝት ፀረ ወራሪ ጦርነቶች በግልፅ ተንፀባርቋል፡፡
የካራማራው የድል ብሥራትም መላው ኢትጵያዊያን ከጥንት አርበኞቻችን በተረከቡት የሀገር ፍቅርና የጀግንነት ውርስ የፈፀሙት ታላቅ ተጋድሎ ውጤት ነው፡፡ በ1956 ዓ.ም በኢትዮጵያ ላይ ወረራ በመፈፀምና የኦጋዴንን ግዛት በመያዝ የታላቋ ሶማሊያ ህልሟን እውን ለማድረግ ሞክራ ባለመሳካቱ አመቺ ጊዜ ለመጠበቅ ተገደደች፡፡
ለዚህ ደግሞ መልካም አጋጣሚ ሆኖ ያገኘችው ጊዜ የኢትዮጵያ ጊዚያዊ አስተዳደር ደርግ ወደ ሥልጣን የመጣበትንና በውጭም በውስጥም በተለያዩ የፖለቲካ ኃይላት እንደ ብራና የተወጠረበትን ወቅት ነበር፡፡ ይህን አጋጣሚ ለመጠቀም በ1969 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ የዚያድ ባሬ መንግሥት መጠነ ሰፊ ወረራ ፈፀመ፡፡
በወቅቱ ሥልጣን ላይ የነበረው መንግሥት በተለያዩ የውጭና የውስጥ የፖለቲካ ኃይላት ከመወጠሩም በላይ በእጁ የነበረው የሀገሪቱ የምድር ጦር ሠራዊት ከአራት ክፍለጦሮች የማይበልጥ ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለሠራዊት ወታደራዊ ድጋፍ ትሰጥ የነበረችው ልዕለ ኃያሏ ሀገር ቃል የገባችውን ወታደራዊ ድጋፏን ጭምር ሙሉ በሙሉ በመከልከሏ ሠራዊቱ በትጥቅም ጭምር ወራሪውን ለመቋቋም የሚያስችል አቅም አልነበረውም፡፡
በአንፃሩ ደግሞ የሶማሊያ ወራሪ ኃይል እስከ አፍንጫቸው በታጠቁ 7 ክፍለጦሮች በተደራጀ ግዙፍ የጦር ኃይል ነበር ወረራውን የፈፀመው፡፡ በዚህም ምክንያት የሶማሊያ ወራሪ ሠራዊት እስከ መቶዎች ኪሎ ሜትር በጥልቀት የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ ለመግባት ችሎ ነበር፡፡ ይህኔ ነው መንግሥት ተነስ፤ ታጠቅ፤ ተዋጋ እናሸንፋለን!! በሚል የእናት ሀገር ጥሪ ያወጀው፡፡
መላው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የተውጣጡ የገበሬና የሠራተኛው 300 ሺህ ሕዝባዊ ሠራዊት ታጠቅ ጦር ሰፈር ፈጥነው ከተቱ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥም ሰልጥኖ በወቅቱ የነበረውን አነስተኛ መደበኛ ጦር ሠራዊት ክንድ ለማፈርጠም ተዘጋጀ፡፡ ዝግጅቱንም በመስቀል አደባባይ በአሳየው ድንቅ የሰልፍ ትርዒት
ይህ ነው ምኞቴ እኔ በህይወቴ
ከራሴ በፊት ለኢትጵያ እናቴ።
በሚል ሕብረ ዜማ ታጅቦ በመትመም አረጋገጠ፡፡
ከዚሁ ጋር የዚህን ሕዝባዊ ኃይል ትጥቅ ለማሟላትና የሠራዊቱን የውጊያ አቅሞች ለማጠናከር መንግሥት ከተለያ ወዳጅ ከሚላቸው ሀገራት ጋር የዲፕሎማሲ ጥረቶቾን በማድረግ ሶስት መቶ ሺህ ሚሊሺያ ኃይል ማስታጠቅ ከመቻሉም በላይ በሜካናይዝድና በመድፍ የተኩስ ድጋፍን ማጠናከር ያስቻለ ወታደራዊ ድጋፍ ተገኝቶ የፀረ ማጥቃት ዘመቻውን በአስተማማኝ ለመጀመር የሚያስችል ደረጃ ላይ ተደረሰ፡፡
ለዚህም እንደ ጥንቱ ሁሉ ከጎናችን የተሰለፈችው ሩሲያ፤ ከጀግኖቻችን ጋር እስከመስዋዕትነት ለመሰለፍ ፈቅደው የተሰለፉ የኩባ ታንከኞችና የየመን መድፈኞች ለዚህ ዓይተኛ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ፈጣን ዝግጅት፤ የኢትዮጵያዊያን እልህ የተመላበት የአትንኩኝ ባይነትና የአርበኝነት መንፈስ ተደምሮ የመልሶ ማጥቃቱ ዘመቻ በምሥራቅም በደቡብም ኢትዮጵያ ተጀምሮ በርካታ በወራሪው ተይዘው የነበሩ የኢትዮጵያ ግዛቶች ነፃ ወጡ፡፡
እንደ ሻምበል ባሻ አሊ በርኬ ያሉ በርካታ ጀግኖቻችን ገድል ወራሪው ከመላው የኢትዮጵያ ግዛት ተጠራርጎ ወጣና በካራማራ ላይ ሰንደቅ ዓላማችን ተውለብልቦ ወሳኙ ድል ተበሰረ፡፡ በወቅቱ እንደእነ ብርጋዲየር ጄኔራል ለገሰ ተፈራና ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ዓይነት የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጀግኖች ፓይለቶቻችን በታጠቋቸው የቆዩ ተዋጊ ጄቶች ከላቁ ዘመናዊ ሩሲያ ሰራሽ ሚግ 21 እና ሚግ 23 ጄቶች ጋር የአየር ለአየር ላይ ተጋድሎ አድርገውና የሶማሊያን እግረኛ ሠራዊት ወደ ሶማሊያ ግዛት ጠልቀው በመግባት አፍረክርከው ለድሉ መገኘት ታላቅ ሚና ተጫውተዋል።
በውጊያው እንደሌሎቹ ያለፉ ጦርነቶች ሁሉ ከመንግሥት በተፃራሪ የተሰለፉ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ኃይላት ከወራሪው ጋር ተሰልፈው ሀገራቸውን በመውጋት የባንዳነት አሳፋሪ ድርጊት ፈፅመዋል፡፡ ይሁን እንጂ ኢትዮጵያዊያን ከአድዋና ከአርበኝነቱ ወቅት በወረሱት ወራሪንም ባንዳንም የመቅጣት ልምድ ኢትዮጵያዊ የአርበኝነትና የጀግንነት ሙያ በደማቸው ውስጥ መኖሩን ያረጋገጠ ወሳኝ ድል በካራማራ ላይ በማብሰር ዓለምን አስደንቀዋል፡፡
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🏴በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
10:00 | ብርንሌይ ከ በርንማውዝ
12:30 | ማንችስተር ሲቲ ከ ማንችተር ዩናይትድ
🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
10:00 | ኢትዮጵያ ቡና ከ ሲዳማ ቡና
01:00 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ አዳማ ከተማ
🇪🇸 በስፔን ላሊጋ
10:00 | ቪያሪያል ከ ግራናዳ
12:15 | አትሌቲኮ ማድሪድ ከ ቤቲስ
02:30 | ማሎርካ ከ ጅሮና
05:00 | አትሌቲክ ቢልባዎ ከ ባርሴሎና
🇮🇹 በጣሊያን ሴሪኤ
08:30 | ቬሮና ከ ሳሱሎ
11:00 | ኢምፖሊ ከ ካግላሪ
11:00 | ፍሮሲኖነ ከ ሊቼ
04:45 | ናፖሊ ከ ጁቬንቱስ
🇩🇪 በጀርመን ቡንደስሊጋ
11:30 | ኮለን ከ ባየር ሌቭርኩሰን
01:30 | ሆፈናየም ከ ወርደር ብሬመን
🇫🇷 በፈረንሳይ ሊግ 1
09:00 | ቶሉስ ከ ኒስ
11:00 | ብረስት ከ ሌ ሃቭሬ
11:00 | ሞንፔሌ ከ ስታርስበርግ
11:00 | ናንትስ ከ ሜትዝ
01:05 | ሬንስ ከ ሎተንት
04:45 | ሊዮን ከ ሌንስ
ቴዲ አፍሮ‼️
ሙሉ ግጥም!!
ቤዛ (ኅብረ ዝማሬ)
ይህቺ ሰንደቅ ዓላማ የክብር ምልክት
ሥፋት እና ምልዓት ርቀት አላት
በዓላማ አንድ ሆና ሦስት ናት በመልክ
ሆ …..
ላላ ….
ቤዛ ለሀገር ቤዛ ሆነው አርበኞቹ
ያቆዩሽ ሀገር ጀግኖቹ
እናት ኢትዮጵያ
ቤዛ ለሀገር ቤዛ ሆነው አርበኞቹ
ያቆዩሽ ሀገር ጀግኖቹ
እናት ኢትዮጵያ
ብለን ተነስተናል ተስፋ አርገን ኹላችን
እኔ ለኔ ሳንል ቅድሚያ ለሀገራችን
እንደ ሐራሴቦን (ወጥተን ከሐራሴቦን) አንድ ዓላማ ይዘን
እንገባለን ከነዓን በፍቅር ተጉዘን
ቤዛ ለሀገር ቤዛ ሆነው አርበኞቹ
ያቆዩሽ ሀገር ጀግኖቹ
እናት ኢትዮጵያ
የጸና ነው በአንድነት ላይ መሠረታችን
አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነው ባንዲራችን
ማነው ደፍሮ በዘር ቋንቋ የሚነጣጥለን
እኛ እንደሆን እማንለያይ አንድ ነን
የጸና ነው በአንድነት ላይ መሠረታችን
አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነው ባንዲራችን
ማነው ደፍሮ በዘር ቋንቋ የሚነጣጥለን
እኛ እንደሆን እማንለያይ አንድ ነን
በዘር በሃይማኖት በማሰብ አንሰናል
ይብቃ በኛ ዘመን ታሪክ ይወቅሰናል
እንቁም ተያይዘን በአንድነት
በኢትዮጵያዊነት
ቤዛ ለሀገር ቤዛ ሆነው አርበኞቹ
ያቆዩሽ ሀገር ጀግኖቹ
እናት ኢትዮጵያ
ዓላማ ነው አንድ ያረገን እኛን
አንድ ያረገን እኛን (x2)
ቤታችን ናት አትንኳት ኢትዮጵያን
አትንኳት ኢትዮጵያን (x2)
የአንድነት ኃይል ጨለማን ድል ነሥቶ
ጨለማን ድል ነሥቶ (x2)
እናያለን አዲስ ፀሐይ ወቶ
አዲስ ፀሐይ ወቶ (x2)
በዝምታ ብንመስልም የተኛን
ብንመስልም የተኛን (x2)
ከተነሣን ማን ሊያቆመን እኛን
ማን ሊያቆመን እኛን (x2)
ከሷ በፊት ይፈሳል ደማችን
ይፈሳል ደማችን (x2)
ቀልድ አናውቅም እኛ በሀገራችን
በእናት ሀገራችን (x2)
ዓላማ ነው
ዓላማ ነው አንድ ያረገን እኛን
አንድ ያረገን እኛን (x2)
ቤታችን ናት አትንኳት ኢትዮጵያን
አትንኳት ኢትዮጵያን (x2)
ከሷ በፊት ይፈሳል ደማችን
ይፈሳል ደማችን (x2)
አትምጡብን በቃ በሀገራችን
በእናት ሀገራችን
―———————————————
ዜማ እና ግጥም — ቴዎድሮስ ካሳሁን ( ቴዲ አፍሮ)
ተጨማሪ የመግቢያ ዜማ — ቆየት ካለ ኅብረ ዝማሬ የተወሰደ
ሙዚቃ ቅንብር፣ ሚክሲንግ እና ሊድ ጊታር — በረከት ተስፋዝጊ (ቤኪ)
ቴነር ሣክስ — ዘሪሁን በለጠ
ማስተሪንግ — ማሩ ዓለማየሁ (ማርቨን ስቱዲዮ)
ተቀባዮች ፤
1. ምኞት ኃይሉ (ዲጄ ዊሽ)
2. ልዑል ሲሳይ
3. ግሩም ታምራት
በ40 ዓመቷ በጨጓራ ካንሰር የተመማችው የዓለምችን ታዋቂዋ ዲዛይነር እና ደራሲ ''ክሪስዳ ሮድሪጌዝ" እንዲህ ስትል ፅፋለች።
ጋራዥ ውስጥ የአለማችን ውድ መኪና ነበረኝ፣ አሁን ግን በዊልቸር መንቀሳቀስ አለብኝ። ቤቴ ሁሉንም አይነት ብራንድ ያላቸው ልብሶች፣ ጫማዎች እና ውድ እቃዎች ይሸጣል፣ አሁን ግን ሰውነቴ በሆስፒታሉ በተዘጋጀ ትንሽ ጨርቅ ተጠቅልሏል።
በባንክ ውስጥ ብዙ ገንዘብ አለኝ። አሁን ግን ከዚህ መጠን ምንም አልጠቀመኝም።
ቤቴ እንደ ቤተ መንግስት ነበር አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ በሁለት አልጋዎች ተኝቻለሁ።
ከባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ወደ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ ከአንድ ላብራቶሪ ወደ ሌላ በመንቀሳቀስ ጊዜዬን አሳልፋለሁ።
በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ፊርማ ሰጥቻለሁ ነገርግን በዚህ ጊዜ የሕክምና መዝገቦች የእኔ ፊርማ ናቸው።
ፀጉሬን ለመስራት ሰባት ፀጉር አስተካካዮች ነበሩኝ ፣ አሁን ግን – በራሴ ላይ አንድ ፀጉር የለኝም።በግል ጄት ላይ፣ የትኛውም ቦታ መብረር እችላለሁ፣ አሁን ግን ወደ ሆስፒታል በር ለመራመድ ሁለት እርዳታዎች ያስፈልጉኛል።
ምንም እንኳን ብዙ ምግቦች ቢኖሩም, አሁን የእኔ አመጋገብ በቀን ሁለት ጽላቶች እና ምሽት ላይ ጥቂት የጨው ውሃ ጠብታዎች ናቸው።
ይህ ቤት፣ ይህ መኪና፣ ይህ አውሮፕላን፣ ይህ የቤት ዕቃ፣ ይህ ባንክ፣ ብዙ ዝናና ዝና፣ አንዳቸውም አይመጥኑኝም። ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም አያዝናኑኝም።
ቱርክ አምርታ የታጠቀቺውን 5ኛ ትውልድ የጦር ጄት ማምረት የሚችሉት ሀገራት ሶስት ብቻ ሲሆኑ እነርሱም አሜሪካ ቻይና እና ሩሲያ ብቻ ናቼው ።
ቱርክ ታሪክ መስራቷን ቀጥላለች ። ማንም ባልጠበቀው መልኩም ከአለማችን አራት የተራቀቁ የጦር ጄት አምራቾች አንዷ ሆናለች ። አሁን የቱርክ ጎራ የነ አሜሪካ ሩሲያና ቻይና ጎራ ሆኗል ። ቱርክ ያመረተቺው KAAN የተሰኘው አምስተኛው ትውልድ የጦር ጄቷ ከአሜሪካው F-35 ከቻይናው J-20 እኛ ከሩሲያው SU-57 የሚፎካከር ሀያል የጦር ጄት ነው ።
ቱርክ እነ አሜሪካ ደረስኩበት ያሉትን የጦር ቴክኖሎጂ ሁሉ በአጭር ጊዜ በመድረስ የአለማችን ባለ ግዙፍና ሀያል ጦር ሀገራት አንዷ ለመሆን ችላለች ። አሁን ቱርክ የማታመርተው የጦር መሳሪያ የለም ማለት ይቻላል ።
ሰው አልባ የጦር ጄቶች ፤ አምስተኛው ትውልድ የጦር አይሮፕላኖች ፤ የጦር ጄት ተሸካሚ መርከቦች ፣ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች ፣ ሚሳኤሎች ፣ ታንኮች ወዘተ ሁሉንም በሚገርም ጥራት እያመረተች ከራሷ አልፋ ለሀገራት በመሸጥ ኢኮኖሚዋንም እያፈረጠመች ትገኛለች ።
የጦር ጄቶች የመጨረሻው ደረጃ አምስተኛው ትውልድ ሲሆን ይህንንም አራት ሀገራት ብቻ ማምረት ይቻላቼዋል ። ቱርክ ፣ አሜሪካ ፣ ሩሲያና ቻይና ብቻ !
ቱርክ ይህንን አስፈሪ ጎራ መቀላቀል መቻሏ የሚደንቅ ነው ።
አሁን ቱርክ የአለማችን ውዱን የጦር ጄት ታጥቃለች ። የጦር ጄቷ KAAN ዋጋ ከአሜሪካው F-35 የጦር ጄትም የሚበልጥ ሲሆን አንዱ የጦር ጄቷ 110 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያወጣል። ይህም የአሜሪካውን F-35 በ አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚበልጠው ሲሆን የሩሲያውን SU-57 ደግሞ ከሁለት እጥፍ በላይ ይበልጣል ።
የቱርኩ ካን የጦር ጄት ከድምፅ በሁለት እጥፍ የሚፈጥን ሲሆን አምስተኛው ትውልድ የያዙትን ነገሮች ሁሉ ይዟል።
