es
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Ir al canal en Telegram

Addis abeba Ethiopia

Mostrar más
5 576
Suscriptores
-40724 horas
-2 4147 días
-2 42630 días
Archivo de publicaciones
ታላቅ የድል ዜና ከኤፍራታና ግድም ወረዳ………… በ11/03/2018 ዓ.ም 102ኛ ኮማ/ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ 02 ሻምበሎች በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አሞጃ ገብርኤል ጠላት ከንጋቱ 12:00
+9
ታላቅ የድል ዜና ከኤፍራታና ግድም ወረዳ………… በ11/03/2018 ዓ.ም 102ኛ ኮማ/ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ 02 ሻምበሎች በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አሞጃ ገብርኤል ጠላት ከንጋቱ 12:00 ሠዓት ጀምሮ ከመስቀል በር፣ ከማጥቆሪያና ከከስያት ሀይሉን አሰባስቦ በ03 ዲሽቃ ታግዞ አሞጃ ገብርኤል ላይ ያለውን የወገን ሀይል በመክበብ ተኩስ የከፈተ ሲሆን ሠራዊታችን በፍጥነት አሰላለፉን በማስተካከል በመልሶ ማጥቃት ጠላትን ሙትና ፣ቁስለኛ እና ምርኮኛ አድርጎ የተረፈው ጠላት እግሬ አውጭኝ ብሎ ሬሳውን እና ትጥቁን አንጠባጥቦ ፈርጥጧል። *የጠላት የደረሰ ኪሳራ:-* .የተገደለ ጠላት......15 .የቆሰለ ጠላት......ከ05 በላይ ብሬን መሳሪያ........01 .ጥቁር ክላሽ........03 .ሰደፍ ክላሽ.........05 .ታጣፊ ክላሽ........01 ብሬን አፈሙዝ.......01 .RGD 5 ቦምብ....01 .F 1 ቦምብ..........06 .ብሬን ጥይት.......726 .ክላሽ ጥይት......246 .ወ/ዊ ሳንጃ..........01 .ብሬን ሸንሸን ባለ100...03 .ክላሽ መጋዘን........25 .ስናይፐር መጋዘን.....05 .መገናኛ ሬዲዮ.......01 .የወገብ ትጥቅ......05 .ስ/ፐር ደረት ትጥቅ...04 መረጃው የኤፍራታ ግድም የመንግስት ኮሙኒኬሽን እና የሰሜን ሸዋ ፖሊስ መመሪያ ነው። #ShareThisPost #share #ShareLikeFollowComment #SharePost #ShareThis

የአደዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ስራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ መሆኑን አሥታወቀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር፣
የአደዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ስራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ መሆኑን አሥታወቀ።  የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር፣ በቀጣይ ስራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ሁንዴ ገልፀዋል። የአክሲዮን ማህበሩ ለስራ የሚያስፈልጉ ቢሮዎችን፣ ሙያተኞችን፣ የቢሮ እቃዎችን በማሟላት ላይ ይገኛል ሲሉ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። የአክሲዮን ማህበሩ በዚህ ዓመት የፋይናንስ አቅሙን በማሳደግ፣ ከአስር በላይ ቅርንጫፎችን ለመክፈት ማቀዱንም ጠቁመዋል። አቶ ዲዳ ሁንዴ የአድዋ ድል የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር፣ ለሠራዊት አባላት የብድር አገልግሎት ለመስጠትም በአሰራር እና በመመሪያ ላይ ተካቷል፣ የሠራዊቱን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ፣ በትኩረት የሚሰራበት ነው ብለዋል። የአክሲዮን ማህበሩ በቀጣይ ለሚጀምረው ስራ ዝግጁነቱን ለመፈተሽ እና ለማረጋገጥ፣ በብሄራዊ ባንክ ኢንስፔክሽን እየተደረገ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አቶ ዲዳ ሁንዴ ገልፀዋል። ዘጋቢ ቢያድግልኝ መሪ ፎቶግራፍ አበረ አየነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

<<የሀሳብ ልዩነትን በጦርነት ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት>> ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ በትግራይ ክልል ውስጥ የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆ
<<የሀሳብ ልዩነትን በጦርነት ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት>> ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ በትግራይ ክልል ውስጥ የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት ሲሉ የቀድሞው  የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ ገለጹ፡፡ ጀነራል ሳሞራ  እንደተናገሩት፤ ከዚህ ቀደም  የተፈፀመው ከባድ ስህተት የትግራይን ህዝብ ዋጋ አስከፍሏል፡፡  አሁን የትግራይ ህዝብ ጦርነት በቃኝ ብሏል፡፡  በሆነ አጋጣሚ የጦርነት አዝማሚያ ቢፈጠር እንኳ ህዝቡ ይህንን የመደገፍ ሀሳብ እንደሌላውም ገልጸዋል፡፡ እንደ ጀነራል ሳሞራ ገለጻ፣ ከዚህ ቀደም ችግሮችን በውይይት መፍታት ባለመቻሉ የተቀሰቀሰው ጦርነት የትግራይን ህዝብ ከባድ ጉዳት አድርሶበታል፡፡ ህዝቡ እስካሁን ድረስ የጦርነቱን ጦስ በጫንቃው ተሸክሟል፡፡ በመሆኑም እንደዚህ ዓይነት  ከባድ ስህተት  መደገም የለበትም ብለዋል፡፡ «ጦርነት ብታሸንፍም ባታሸንፍም ጣፋጭ ሆኖ አያውቅም» ያሉት ጀነራሉ፤ በክልሉ በርካታ ወጣት ህይወቱን አጥቷል፣ እናቶችም በሀዘን ተጎድተዋል፣ ተቸግረዋልም፤ በመሆኑም ህዝቡ በተደጋጋሚ ውጊያ ውስጥ ሊማገድ አይገባውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በትግራይ ውስጥ ማንኛውም ችግር ወይም የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም እንዳለበትና፤ ልዩነቶች በሰላም እና በሰላም ብቻ መፈታት አለባቸው በሚል እምነት መፅናት እንደሚያስፈልግም አስገዝበዋል፡፡ በክልሉ የጦርነት ችግር ይመጣል እያሉ ያልተጨበጠ ወሬ የሚለፍፉ የጦር ጀነራሎችን እሰማለሁ ያሉት ጀነራሉ፤ ይህ የግል ሀሳባቸው ሊሆን ይችላል፤ እኔ የምላቸው ግን የእውነት የህዝብ አገልጋይ ከሆኑ በትግራይ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር መፍታት የመጀመሪያው ጉዳያቸው ሊያደርጉት ይገባልም  ብለዋል። via gazetteplus #ዋሱመሐመድ

የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል። ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም 118ኛው የኢትዮጵ
+4
የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል።       ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም 118ኛው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን በዓል ላይ በመገኘት ንግግር  ያደረጉት የኢትዮጵያ የባህር ሀይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ባስተላለፉት መልዕክት ፣ የለውጡ መንግስት የባህር በር አስፈላጊነት ላይ ባለው የፀና አቋም እና የመከላከያ ሰራዊቱ  ስትራቴጂ አመራሮች ባደረጉት ድጋፍና ክትትል የአንጋፋውን የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ወደ ቀድሞ ገናና ስሙ ለመመለስ የተሰሩት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በየዘመናቱ የገጠሟትን ፈተናዎች በድል እየተወጣች የመጣች ታሪካዊና ቀደምት ሀገረ መንግስት መሆኗን አውስተው የባህር በር ጥያቄው  የኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ባህር ሀይሉ ራሱን ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ፣ የተቋማት ግንባታ ከማሳደጉም ባለፈ የመነሻ የዉጊያ ትጥቆች ማሟላቱንም ተናግረዋል። የባህር በርና ባህር ሀይል የማይነጣጠሉ መሆናቸውን የገለፁት ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ሀገራችን ባላት ታሪክና መብት የባህር በር የማግኘት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ሀገራችን የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ፍትሃዊ ጥያቄ ለጋራ ተጠቃሚነት በሰጥቶ መቀበል መርህ መስራት እንደሚገባም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ ፎቶግራፍ ተሠማ ኡርጌሳ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

"ኤርትራ በአፍሪካ የበርካታ ኢንዱስትሪ ባለቤት ነበረች፣አሁን ላይ ግን የታሸገ ውሃና ሳሙና እንኳን ከውጭ ለማስገባት የተገደደች ሀገር ሆናለች።አሁን ላይ የውስጥ ችግሯ እንዳለ ሆኖ ከኢትዮጵያ ጋር በ
"ኤርትራ በአፍሪካ የበርካታ ኢንዱስትሪ ባለቤት ነበረች፣አሁን ላይ ግን የታሸገ ውሃና ሳሙና እንኳን ከውጭ ለማስገባት የተገደደች ሀገር ሆናለች።አሁን ላይ የውስጥ ችግሯ እንዳለ ሆኖ ከኢትዮጵያ ጋር በአሰብ ወደብ ምክንያት ውጥረት ውስጥ ገብታለች።በዚህም የኤርትራ ሉዓላዊነት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል"ዘ ኢኮኖሚስት ‎#ዋሱመሐመድ አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቶች ለምን ይቋረጣሉ ? የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ በርካታ አገልግሎቶቹ እንደሚቋረጡ ገልጾልናል። ባንኩ " ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቶች ለምን ይቋረጣሉ ? የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ በርካታ አገልግሎቶቹ እንደሚቋረጡ ገልጾልናል። ባንኩ " ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ መስከረም 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት እስከ ለሊቱ 9፡30 ሰዓት ድረስ ከሲቢኢ ብር አገልግሎቶች በስተቀር ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች በጊዜያዊነት ይቋረጣሉ " ብሏል። የሚቋረጡት አገልግሎቶች ፦ - የሞባይል ባንኪንግ፣ - ኢንተርኔት ባንኪንግ፣ - ኤቲኤም ማሽኖች - የፖስ ማሽኖች እና በኮር ባንኪንግ የሚሰጡ አገልግሎቶች (Core Banking Services) እንደሆኑ አሳውዋል። ባንኩ ደንበኞቹ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቋል። #CBE ©tikvahethiopia

🇪🇹 ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የጀመረችውን እንቅስቃሴ እደግፋለሁ - ዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ 🇦🇹 በኦስትሪያ ቪየና እየተካሄደ ካለው 69ኛው የኤጀንሲ
🇪🇹 ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የጀመረችውን እንቅስቃሴ እደግፋለሁ - ዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ 🇦🇹 በኦስትሪያ ቪየና እየተካሄደ ካለው 69ኛው የኤጀንሲው መደበኛ ጉባኤ ጎን ለጎን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እና ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ በኢትዮጵያ የኒውክሌር ቲክኖሎጂ ውጥን ዙሪያ ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ኤጀንሲው ብሔራዊ የኒውክሌር ኃይል ግንባታ ላይ የቴክኒክ እና የእውቀት ሽግግር ድጋፍ እንዲያደርግ መጠየቃቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡ ☢️ ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የሚያስችል መሠረት በመጣል ወደ ትግበራ ለመግበት ሰፊ ጥረት እያደረገች እንደሆነም አንስተዋል። 👉 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የኢትዮጵያ የኒውክሌር መሠረተ ልማት በመገንባት ለዘርፈ ብዙ ዔላማ ለማዋል እንዳቀደች በ 'የመደመር መንግሥት' መፅሐፍ ምረቃ ወቅት ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X

የሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መሥከረም 01 ቀን 2018 ዓ.ም ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ መላው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲቪል ሠራተኞች በሙ
የሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መሥከረም 01 ቀን 2018 ዓ.ም ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ መላው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲቪል ሠራተኞች በሙሉ ከሁሉ አስቀድሜ እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡ አዲሱን አመት ስንቀበል ሀገራችን ኢትዮጵያ የጎደፈ ስሟን ያደሱ በርካታ ድሎችን ባስመዘገበችበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡ ሀገራችን ከነበረችበት የድህነት ማቅ እንዳትወጣ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ከባንዳዎች ጋር ተጣምረው ያለእረፍት የሰሩ ቢሆንም በህዝቦቿ የተባበረ ክንድ በሠራዊቷ ፅናት ዛሬ የድህነት ተራራ እየተናደ ጠላቶቿ የሀዘን ማቅ እየለበሱ ይገኛሉ፡፡ ዛሬ በብዙ መልካም ማሣያዎች ምሳሌ የሆነችው ሀገራችን ሠላሟ ተረጋግጦ ልማቷ ተፋጥኖ ህዝቦቿ በሠላም ወጥተው የሚገቡበት ጠላቶቿ ወይ ወደ ሠላም የሚመጡበት ካልሆነም እንዲጠፉ ተልዕኳችንን በሚገባ እንወጣለን። እኛ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አመራርና አባላትም በየትኛውም ቦታ የሚሠጠንን ተልዕኮ በድል አድራጊነት ፈፅመን የህዝብን ሠላም በማረጋገጥ ረገድ የህይወት መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር በበርካታ አካባቢዎች ከህዝባችን ጋር በመሆን ሠላም ማረጋገጥ ችለናል። ዛሬም ከትላንትናው በላቀ ደረጃ አቅማችንን አጎልብትን እጅግ ልቀን በሀገራችን ላይ በየትኛውም አቅጣጫ የሚቀጣን ጥቃት ለመከላከል ዝግጁ መሆናችንን በዚሁ አጋጣሚ እያረጋገጥኩኝ አዲሱ አመት የሰላም ፣ የብልፅግና የእድገት እንዲሁም የጤና እንዲሆን እመኛለሁ አመሠግናለሁ።

#YouTube subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://www.youtube.com/@EthiopianCommando #ቴሌግራም Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Comman
#YouTube subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://www.youtube.com/@EthiopianCommando #ቴሌግራም Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command #Facebook https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces

አዳዲስ ከተሞች በህዳሴ ዙሪያ‼ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ከተሞች ማስተር ፕላን እየተዘጋጀ ነው ተብሏል። 📌በሕዳሴው ግድብ በተፈጠረው "ንጋት" 246 ኪ.ሜ ባህር ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ ከ
+1
አዳዲስ ከተሞች በህዳሴ ዙሪያ‼ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ከተሞች ማስተር ፕላን እየተዘጋጀ ነው ተብሏል። 📌በሕዳሴው ግድብ በተፈጠረው "ንጋት" 246 ኪ.ሜ  ባህር ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት ሥራ መጀመሩ አሳውቋል፡፡ 📌በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት እንዲሁም የአሶሳ ከተማ  የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ፤ 'ሲቲስ አሊያንስ' በተሰኘ ድርጅት አማካኝነት በይፋ መጀመሩን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ እወቁልኝ ብሏል። 📌ወደፊት በአካባቢው ብዙ ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የተገለጸ  ሲሆን፤ አካባቢው የዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን ትኩረት መሳቡ ተነግሯል። 📌ቀደም ሲልም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ አልሚዎች እንዳሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ የሐይቁን መሃል በተመለከተ ከፌደራል መንግሥት ጋር በትኩረት የሚሰራ መሆኑ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ብዙ ደሴቶች በመኖራቸው ጥናት እንደሚፈልግ ተናግረዋል።ፎቶ:-ፋይል #ዋሱመሐመድ

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የ14 ዓመታት ጉዞ - በአንድ ድቂቃ! ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X

https://t.me/HulugameBot/startapp?startapp=ref_1948449093 አሁኑኑ ሁሉጌም አባል በመሆን በየቀኑ ትርፉን ይዛቁ።

የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስትር ሪምአውክስ ክላውድ የአየር ወለድ ማሰልጠኛን ጎበኙ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሪምአውክስ ክላውድ የተመራው ልዑክ ከልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ እና ከክፍሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በቢሾፍቱ የሚገኘውን የአየር ወለድ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም አጠቃላይ የልዩ ዘመቻዎች ማሰልጠኛ ማዕከልን እና በስሩ የሚገኙትን አራት ትምህርት ቤቶች በተመለከተ የዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ለቡድኑ ማብራሪያና ገለፃ የሰጡ ሲሆን የልዩ ሀይሎች ስልጠናን የሚያሳይ አጠር ያለ ዶክመንተሪ ፊልምም ቀርቧል፡፡ በሀገራዊ ለውጡ ተቋሙ ባደረገው ሪፎርም የልዩ ሀይሎች ማሰልጠኛ ማዕከል የማሰልጠን አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ በማሳደግ በሀገር ደረጃ የውጊያ ማሪሽ ቀያሪ የምድር ድሮን የሚል ስያሜ የተሰጣቸውን የኮማንዶ፣ አየር ወለድና ልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር ሀይል መፍጠር መቻሉን አብራርተዋል፡፡ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ተልዕኮ እና አሁናዊ ብቃቱን ለልዑካን ቡድኑ የገለፁ ከመሆኑም በላይ ማሰልጠኛ ማዕከሉ የራሱን ብቁ አሰልጣኞች በማፍራት ለኢትዮጵያ የሚመጥናትን ሀይል እያሰለጠነ ከመሆኑም በላይ ለአንዳንድ የአፍሪካ ሀገሮችም በስልጠና መስክ ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል፡፡ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስትር ሪምአውክስ ክላውድ በበኩላቸው ዕዙ ባደረገላቸው አቀባበል መደሰታቸውን ገልፀው የኢትዮጵያ የኮማንዶ፣ አየር ወለድና ልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር የስልጠና ሂደት መደነቃቸውን በመግለፅ ስልጠናው የኢትዮጵያ ሠራዊት ጥንካሬ ያሳዬ ነው ብለዋል፡፡ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ወጣቶች በዚህ ደረጃ እዚህ ሰልጥነው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውና ይህም በሁለቱ ሀገሮች ወታደራዊ ትብብር ስምምነት መሰረት እንደሚፈፀም ተስፋ እንዳላቸው ገልፀዋል። ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን ነው #YouTube subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://www.youtube.com/@EthiopianCommando #ቴሌግራም Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command #Facebook https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces

የቅኝ ግዛት ስምምነት ላይ ሙጭጭ ያለችው ግብፅ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከጋራ ተጠቃሚነት መርህ በማፈንገጥ፣ ኢትዮጵያ ቁጥር አንድ ጠላት አድርጋ ሰፋ ያለ እንቅስቃሴ ጀምራለች፡፡ በቅርቡ የዑጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮዌሪ  ካጉታ ሙሴቬኒን  ካይሮ በመጋበዝ የተፋሰሱ ሀገሮች በኢትዮጵያ ላይ ጀርባቸውን እንዲያዞሩ ቅስቀሳ ለማድረግ ብትሞክርም፤ ሙሴቬኒ ግን የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲን በቤተ-መንግስታቸው ውሃውን በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለመጠቀም አቀራረቡን  ማሳመር እንዳለባቸው ነግረዋቸዋል፡፡ ለዚህም ሁሉም የተፋሰሱ ሀገሮች በዓባይ ውሃ ፍትሃዊ ተጠቀሚነት ላይ በማተኮር ድርድርን ያስቀድሙ ብለዋል። ግብፅ ግን አሁንም በኢትዮጵያ ዙሪያ ያሉ ጎረቤቶችን በጠላትነት ለማነሳሳት የማትፈነቅለው ድንጋይ እንደሌለ ነው እንቅስቃሴዋ የሚያሳብቀው፡፡ ከዘመኑ አስተሳሰብና ፍላጎት ጋር ለመራመድ የተሳናት ግብፅ ከአሜሪካ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመመካት፣ በተለይም ፕሬዚዳንት ትራምፕ እ.ኤ.አ. ከ2020 የመጀመሪያ ፕሬዚዳንትነታቸው ዘመን እስከ ቅርብ ቀናት ድረስ ያሳዩት የግብፅ ድጋፍ የልብ ልብ የሰጣት ይመስላል፡፡ ነገር ግን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ መሠረት ድንጋይ ከተጣለ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ሒደቱን በትኩረት የሚከታተሉ ኢትዮጵያውያንም ሆኑ ሌሎች ታዛቢዎች፣ የግብፅ አንድ ቦታ ተቸንክሮ ቆሞ ኢትዮጵያን ሰላም መንሳት እንደማይዋጥላቸው በተደጋጋሚ ድምፃቸውን አሰምተዋል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል አንዱ ትልቁ ነገር <<የአፍሪካን ችግር በአፍሪካውያን የመፍታት›› መርህን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ በሌላ በኩል ደግሞ በአሜሪካ በኩል የሚመጡ ተገቢ ያልሆኑ ጫናዎችን በበሳል ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎች ለማስቆም መረባረብ ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ሆኖ በዓለም አቀፍ መድረኮች ኢትዮጵያ ሰፊ ሥራዎች ይጠብቋታል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የመስኩ ባሙያዎች እንደሚያሳስቡት ግብፅ በዓባይ ውኃ ፖለቲካ የአፍራሽነት ሚናዋን ትታ፣ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር የምትሠራባቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት እንዳሉ ማስታወቅ ያስፈልጋል። በኢትዮጵያ በኩል ያለው ግዙፉ ጥቁር ዓባይ (Black Nile) ከገባሮቹ ጀምሮ የውኃ ምንጭሆኖ እንዲቀጥል፣ የተፈጥሮ ልማትና ጥበቃ እንደሚያስፈልገው ይታወቃል፡፡ እግረ መንገዱንም ግብፅ በዚህ ረገድ ትብብርስታደርግ ውኃውን በፍትሐዊነት ለመጠቀም አያዳግትም፡፡ ግብፅ አልላቀቅ ካለችው የቅኝ ግዛት ታሪካዊ መብት ከምትለው አባዜ ስትወጣ፣ ሁሉም አገሮች በመተባበር ልማታቸውን ማፋጠን የሚችሉበት ዕድል ይፈጠራል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክአመንጭቶ ውኃው በአግባቡ ወደ ሱዳንም ሆነ ወደ ግብፅ እየተመመ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ለሌሎች የተፋሰሱ አገሮችም ልማት መልካም ምሳሌነትን እያሳየ መሆኑን ዓለምን ማስገንዘብ ይገባል፡፡ መላው ዓለም ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ መቃረቡን በተገነዘበበት በዚህ ጊዜ፣ ግብፅ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ እያየችው ያለው ጉዳይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የእርስ በርስ ግጭት ነው፡፡ ግብፅ በታሪኳ የምትታወቀው ኢትዮጵያን ለማጥቃት ወይም ለማተራመስ የምትነሳው ተዳክማለች ብላ በምታምንበት ጊዜ ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያንም የውስጥ ችግራችንን በስክነት ለመፍታት ባለመቻላችን ምክንያት የጥቃት ተጋላጭ እየሆንን ነው፡፡ የዓባይ ወንዝ ለኢትዮጵያ ምንም ዓይነት ጥቅም ሳይሰጥ ለዘመናት በከንቱ ድንበር ተሻግሮ መንጎዱ ሲያንገበግባቸው የኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ በወርኃ መጋቢት 2003 ዓ.ም. የግንባታው የመሠረት ድንጋይ መጣል በቀጥታ ሥርጭት ሲበሰር ያሳዩት የደስታ ሲቃና የዘመናት ቁጭት መቼም ቢሆን የማይረሳ ነው፡፡ ለግንባታው መሳካትም ከአገር ቤት እስከ ውጭያሉ ወገኖች ድረስ የተደረገው ርብርብ ዳግማዊ ዓድዋ ተብሎም ነበር፡፡ አሁን ምረቃው ተቃርቦ እያለም ቢሆን ያለው ስሜት ያንኑ ነው የሚያንፀባርቀው፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን እርስ በርስ መገፋፋቱና መጨራረሱ በፍጥነት ቆሞ በታሪካዊ ጠላት ፊት በአንድነት መቆም ካልተቻለ፣ ለ14 ዓመታት ከባድ ዋጋ ያስከፈለው ታላቅ ብሔራዊ ፕሮጀክት ከሥጋት ነፃ ይሆናል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ ውስጣዊ ችግሮችን በሰላማዊ አማራጮች በመፍታት ግብፅ አንዲት ጠብታ ውኃ ሳትጎድልባት በዓባይ ወንዛችን ላይ የመልማት መብት እንዳለን በጋራ ማሳየት ይጠበቅብናል፡፡ ዓለም ወደፊት እየገሰገሰ በግብፅ የቅኝ አገዛዝ አስተሳሰብ በወለደው ሴራ መጠለፍ አይገባም፡፡ ግብፅ ኋላቀር በሚባለው የቅኝ አገዛዝ አስተሳሰብ ተጠፍራ ኢትዮጵያን ወደፊት ከመገስገስ ለማስቆም የሚቻላት ከሆነ፣ ጥፋቱ የማንም ሳይሆን የእኛ የኢትዮጵያውያን መሆኑን ከገዥው ፓርቲ ጀምሮ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ከታሪክ ተወቃሽነት ማምለጥ እንደማይቻል ይገንዘቡ፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመቆም የሚያስችል ቁመና መያዝ ሲቻል፣ ግብፅ የኢትዮጵያን የመልማት መብት ለመገዳደር አንዳችም አቅም አይኖራትም፡፡ በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች መካከል ያለው የጂኦ ፖለቲክስ መሳሳብና መገፋፋት ራሱን የቻለ ችግር መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡ በተለይ የአፍሪካ ቀንድ አገሮች ለዘመናት ከግጭት፣ ከረሃብና ከስደት ውስጥ ለመውጣት ያልቻሉት የውክልና ጦርነት አራማጆች በመሆናቸው እንደሆነ ነጋሪ አያስፈልግም፡፡ በሱዳን ውስጥ የሚካሄደው ደም አፋሳሽ አደገኛ ጦርነት በእነ ማን እንደሚደገፍ ፀሐይ ከሞቀው ሰነባብቷል፡፡ ከኤርትራ እስከ ሶማሊያ ያለው የጠላትነት ስሜት ከኌላው በማን እንደሚገፋና እንደሚደገፍም የታወቀ ነው፡፡ ሁሉም አካባቢ ግብፅ እጆቿን አስረዝማ አስገብታ ኢትዮጵያን በተዘዋዋሪ ለማዳከም እንደምትሠራ ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ግብፅ በዚህ ወሳኝ ጊዜ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ሙሉ ትኩረቷን አድርጋ ስትነሳ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የእርስ በርስ ፍጅቱን በሠለጠነ መንገድ አስቁሞ እንደ ጥንቶቹ ጀግኖቹ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ለመቆም አለመፈለግ በታሪክና በመጪው ትውልድ እንደሚያስጠይቅ ግንዛቤ ይያዝ፡፡ በህዳሴ ግድብ ላይ የተከፈተው የግብፅ ዘመቻም በጋራ ይመከት! - Ethioian Reporter #GERD #የዓባይልጅ

ሞዐ ተዋህዶና ፋኖ ምንና ምን ናቸው ጆሮ አይሰማው የለ! {መምህር ፋንታሁን ዋቄ ገለታ ይግባህ} መምህር ፋንታሁን ዋቄ ነገር መደበቅ አይሆንላቸውም ሞዐ ተዋህዶ ስለተባለው ቡድን አመሰራረትና ከፋኖ ጋር ያለውን ጥብቅ ቁርኝት ለማእዛ መሀመድ እስክትጮህ ድረስ በግልፅ ተንትኖ ነግሯታል። መምህር ፋንታሁን ዋቄ በአጭሩ ሶስት ነገሮች Clarify አድርጎልናል። አንደኛ ፦ ሞዐ ተዋህዶ የተባለ ሰለሞናዊ (ሃይማኖታዊ) መንግስት ለመመስረት የተቋቋመና ከረጅም ግዜ በፊት ሲሰራ የነበረ ቡድን እንዳለ። ሁለተኛ ፦ አሁን ያሉት የፋኖ አመራሮችም የዚህ ቡድን አባል እንደሆኑና ፋኖም በሞዐ ተዋህሶ እሳቤ ስለተመጠመቀ Anti-Islam ሆኖ የተቋቋመ ቡድን እንደሆነ። ሶስተኛው ፦ አሁንም ከሞዐ ተዋህዶ አቋም ጋር አብሮ የማይሄድ የፋኖ መሪ እንደሚሰደድ፣ እንደሚገደልና ከትግል እንደሚወገድ። የሞዐ ተዋህዶ መስራች ከሆኑት አንዱ መምህር ፋንታሁን ዋቄ እነዚህን ሶስት ነገሮች በግልፅ ስላስረዱልን እግዜር ይባርኮት። እኛና አንዳንድ የነቁ የአማራ አክቲቪስቶች ስንጮህበት የነበረውን ጉዳይ ነው መጥተው ማረጋገጫ ማህተም የመቱልን። መምህር ፋንታሁን ብዙ ነገር ነው የተናዘዙት። እንደሳቸው ትንተና በሞዐ ተዋህዶና በፋኖዎቻቸው አይን አማራ ማለት ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ያለው ብቻ ነው። "የአማራ" ትግል የተባለውም ለሽፋን እንጂ ውስጥ ውስጡን የኦርቶዶክስ ቤተእምነትን በትረመንግስት ማስጨበጥና የድሮውን ሰለሞናዊ መንግስት የመትከል አላማ ይዞ ነው የሚንቀሳቀሰው። ይሄንን መምህሩ ቃል በቃል ነው የተናገሩት። እንግዲህ ፋኖ ነኝ የምትይ ሙስሊም፣ ጴንጤ፣ ካቶሊክ፣ ኤቲይስት እርምሽን አውጪ ነው ያለሽ በአጭር አማርኛ!!! 😁 መምህር ፋንታሁን ሌላም ሚስጥር ነግሮናል። ይሄ ቡድን በትግራዩ ጦርነት ግዜ ሰራዊቱን ሲያስታጥቅና ለቀጣዩ ጦርነት ፋኖዎቹን ሲያዘጋጅ እንደነበር፣ (ትክክለኛው ፋኖ ከፊት ሲዘምት የኢትዮጵያን ሰራዊት ከጀርባ እየወጋ ሲታጠቅ የነበረውን ማለታቸው ነው) የተለያዩ ቪዲዮዎችንና ፅሁፎችን እያዘጋጀ አሁን ላሉ የፋኖ መሪዎች ከባባድ ሀይማኖታዊ ስልጠና ሲሰጥ እንደነበርም ገልፀዋል። መምህር ፋንታሁን ዋቄ በዚህም አላበቃም። አሳምነው ፅጌ ይሄ በህቡእ የተደራጀ አክራሪ ሃይማኖተኛ ቡድን ላይ በደህንነቶቹ አማካኝነት ደርሶበት እንደነበርና የተወሰኑትን አስሮ ሲጠይቅ "ሰለሞናዊውን መንግስት ለማምጣት በህቡእ እንደተደራጁ" ይነግሩታል። አሳምነውም “ይሄማ የኔም አላማ ነው” በማለት ጭራሽ የነሱ አባል ሆኖ እንደቀጠለና አብሯቸው ይሰራ እንደነበር መምህር ፋንታሁን ነግሮናል። በጣም የሚገርመው የመአዛ መሀመድ ድንጋጤ ነው 😁 መአዛ እስከዛሬ ይሄንን ነገር ሳታውቅ ነበር እንዴ የፋኖ አፋሽ አጎምባሽ ሆና ስትሰራ የነበረችው?  የእውነት መአዛ መሀመድ ከምትኖርበት ሐገር ህግ ጋር በሚጋጭ መልኩ በጋዜጠኝነት ካባ ታጣቂን ሃይል ስትደግፍ፣ አማራና አማራ እንዲጋደል ገንዘብ ስታሰባስብ፣ ፌክ ዶክመንተሪ ስታሰራ፣ የሀሰት ዜናዎችን ስታሰራጭ ይሄን ሐገር ያወቀውን ሚስጥር አታውቅም ነበር ወይ የሚለው የእውነትም አጠራጣሪ ነው። መምህር ፋንትሽ በኩራት የገለጠው የፋኖና የሞዐ ተዋህዶ ጥምረት ብዙ ነገሮችን ግልፅ ያደረገላችሁ ይመስለኛል። ያ ሁሉ ቤተክህነት ውስጥ ተቀምጦ ግርግር ሲያስነሳ የነበረ ካህን ሴራ፣ የከሸፈው "የጥቁር ለብሳችሁ ውጡ" አድማ፣ ገዳማትንና አቢያተክርስቲያናትን እንደምሽግ ተጠቅሞ ሲደረግ የነበረ ስልጠናና በየአውደምህረቱ ጓሮ ተቀብሮ የተገኘ የጦር መሳሪያ ክምችት በየቦታው ማን እንዳስነሳቸው ያልታወ የቤተክርስቲያን ቃጠሎዎችና በማግስቱ እሱን ተከትሎ ይደረጉ የነበሩ የሚዲያ ጩኸቶችና የክተት ጥሪዎች፣ የፋኖ አመራር ነን የሚሉ ሰዎች አንገታቸው ላይ የሚያስሯቸው ካህን እንኳን የማያደርጋቸው ትልልቅ መስቀሎችና ሃይማኖታዊ ቅርፅ ያላቸው ፕሮፖጋንዳዎች፣ የዚህ ሁሉ Mastermind የፋኖዎች አለቃና አስታጣቂው የሰለሞናዊ መንግስት አስመላሹና ሙስሊምና ፕሮቴስታንት ጠሉ ሞዐ ተዋህዶ ነበር። Case Closed! በመጨረሻም በጋዜጠኛ ሽፋን የምትንቀሳቀሰው መአዚ ይሄ ቡድን በፋኖዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት ስትናገር የአቶ ፋንታሁን ዋቄ ምላሽ አጭርና ቁጣ የተሞላበት ነበር። ቃል በቃል እንዲህ ነበር ያላት. “ሞዐ ተዋህዶን ከፋኖ ትግል ውስጥ ይውጣ የሚሉ ሰዎች ራሳቸው ከትግላችን ይውጡ። ማን ባደራጀው ፋኖ ማን ያዛል?” 😁 ወይ ተአምረኛው ሞዐ ተዋህዶ! ለማንኛውም ትግሉ የብሔር መስሎህ ነፍስህን የሰጠህ ሙስሊም ነፍስ ይማር እያልን የፋኖ ትግል Secular (ከሀይማኖት ነፃ) መስሎህ አሁንም የምትደግፍ ምስኪን ምእመንም ሆንክ ታጣቂ ቢያንስ አሁን ቆም ብለህ እንድታስብ እንመክራለን። በመጨረሻም ሃቀኛውን ፋኖ አሶግዶ በህቡእ የተደራጀውን ነፍሰገዳይ ፋኖና የሰለሞናዊው ዙፋን አስመላሽ ቡድን ካባውን ገፍፈው እርቃኑን እንድንመለከተው ላደረጉን ለታጋይ ፋንታሁን ዋቄ እጅ እንነሳለን። 🫡