የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 756
المشتركون
-27824 ساعات
-2 5467 أيام
-1 99730 أيام
أرشيف المشاركات
#YouTube
subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://www.youtube.com/@EthiopianCommando
#ቴሌግራም Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
#Facebook https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
+1
አዳዲስ ከተሞች በህዳሴ ዙሪያ‼
በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ከተሞች ማስተር ፕላን እየተዘጋጀ ነው ተብሏል።
📌በሕዳሴው ግድብ በተፈጠረው "ንጋት" 246 ኪ.ሜ ባህር ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት ሥራ መጀመሩ አሳውቋል፡፡
📌በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት እንዲሁም የአሶሳ ከተማ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ፤ 'ሲቲስ አሊያንስ' በተሰኘ ድርጅት አማካኝነት በይፋ መጀመሩን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ እወቁልኝ ብሏል።
📌ወደፊት በአካባቢው ብዙ ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የተገለጸ ሲሆን፤ አካባቢው የዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን ትኩረት መሳቡ ተነግሯል።
📌ቀደም ሲልም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ አልሚዎች እንዳሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ የሐይቁን መሃል በተመለከተ ከፌደራል መንግሥት ጋር በትኩረት የሚሰራ መሆኑ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ብዙ ደሴቶች በመኖራቸው ጥናት እንደሚፈልግ ተናግረዋል።ፎቶ:-ፋይል
#ዋሱመሐመድ
https://t.me/HulugameBot/startapp?startapp=ref_1948449093
አሁኑኑ ሁሉጌም አባል በመሆን በየቀኑ ትርፉን ይዛቁ።
የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስትር ሪምአውክስ ክላውድ የአየር ወለድ ማሰልጠኛን ጎበኙ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሪምአውክስ ክላውድ የተመራው ልዑክ ከልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ እና ከክፍሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በቢሾፍቱ የሚገኘውን የአየር ወለድ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝታቸውም አጠቃላይ የልዩ ዘመቻዎች ማሰልጠኛ ማዕከልን እና በስሩ የሚገኙትን አራት ትምህርት ቤቶች በተመለከተ የዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ለቡድኑ ማብራሪያና ገለፃ የሰጡ ሲሆን የልዩ ሀይሎች ስልጠናን የሚያሳይ አጠር ያለ ዶክመንተሪ ፊልምም ቀርቧል፡፡
በሀገራዊ ለውጡ ተቋሙ ባደረገው ሪፎርም የልዩ ሀይሎች ማሰልጠኛ ማዕከል የማሰልጠን አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ በማሳደግ በሀገር ደረጃ የውጊያ ማሪሽ ቀያሪ የምድር ድሮን የሚል ስያሜ የተሰጣቸውን የኮማንዶ፣ አየር ወለድና ልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር ሀይል መፍጠር መቻሉን አብራርተዋል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ተልዕኮ እና አሁናዊ ብቃቱን ለልዑካን ቡድኑ የገለፁ ከመሆኑም በላይ ማሰልጠኛ ማዕከሉ የራሱን ብቁ አሰልጣኞች በማፍራት ለኢትዮጵያ የሚመጥናትን ሀይል እያሰለጠነ ከመሆኑም በላይ ለአንዳንድ የአፍሪካ ሀገሮችም በስልጠና መስክ ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አውስተዋል፡፡
የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መከላከያ ሚኒስትር ሪምአውክስ ክላውድ በበኩላቸው ዕዙ ባደረገላቸው አቀባበል መደሰታቸውን ገልፀው የኢትዮጵያ የኮማንዶ፣ አየር ወለድና ልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር የስልጠና ሂደት መደነቃቸውን በመግለፅ ስልጠናው የኢትዮጵያ ሠራዊት ጥንካሬ ያሳዬ ነው ብለዋል፡፡
የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ወጣቶች በዚህ ደረጃ እዚህ ሰልጥነው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውና ይህም በሁለቱ ሀገሮች ወታደራዊ ትብብር ስምምነት መሰረት እንደሚፈፀም ተስፋ እንዳላቸው ገልፀዋል። ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን ነው
#YouTube
subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://www.youtube.com/@EthiopianCommando
#ቴሌግራም Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
#Facebook https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
የቅኝ ግዛት ስምምነት ላይ ሙጭጭ ያለችው ግብፅ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከጋራ ተጠቃሚነት መርህ በማፈንገጥ፣ ኢትዮጵያ ቁጥር አንድ ጠላት አድርጋ ሰፋ ያለ እንቅስቃሴ ጀምራለች፡፡
በቅርቡ የዑጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቬኒን ካይሮ በመጋበዝ የተፋሰሱ ሀገሮች በኢትዮጵያ ላይ ጀርባቸውን እንዲያዞሩ ቅስቀሳ ለማድረግ ብትሞክርም፤ ሙሴቬኒ ግን የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲን በቤተ-መንግስታቸው ውሃውን በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለመጠቀም አቀራረቡን ማሳመር እንዳለባቸው ነግረዋቸዋል፡፡
ለዚህም ሁሉም የተፋሰሱ ሀገሮች በዓባይ ውሃ ፍትሃዊ ተጠቀሚነት ላይ በማተኮር ድርድርን ያስቀድሙ ብለዋል።
ግብፅ ግን አሁንም በኢትዮጵያ ዙሪያ ያሉ ጎረቤቶችን በጠላትነት ለማነሳሳት የማትፈነቅለው ድንጋይ እንደሌለ ነው እንቅስቃሴዋ የሚያሳብቀው፡፡ ከዘመኑ አስተሳሰብና ፍላጎት ጋር ለመራመድ የተሳናት ግብፅ ከአሜሪካ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመመካት፣ በተለይም ፕሬዚዳንት ትራምፕ እ.ኤ.አ. ከ2020 የመጀመሪያ ፕሬዚዳንትነታቸው ዘመን እስከ ቅርብ ቀናት ድረስ ያሳዩት የግብፅ ድጋፍ የልብ ልብ የሰጣት ይመስላል፡፡ ነገር ግን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ መሠረት ድንጋይ ከተጣለ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ሒደቱን በትኩረት የሚከታተሉ ኢትዮጵያውያንም ሆኑ ሌሎች ታዛቢዎች፣ የግብፅ አንድ ቦታ ተቸንክሮ ቆሞ ኢትዮጵያን ሰላም መንሳት እንደማይዋጥላቸው በተደጋጋሚ ድምፃቸውን አሰምተዋል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል አንዱ ትልቁ ነገር <<የአፍሪካን ችግር በአፍሪካውያን የመፍታት›› መርህን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ በሌላ በኩል ደግሞ በአሜሪካ በኩል የሚመጡ ተገቢ ያልሆኑ ጫናዎችን በበሳል ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎች ለማስቆም መረባረብ ነው፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ሆኖ በዓለም አቀፍ መድረኮች ኢትዮጵያ ሰፊ ሥራዎች ይጠብቋታል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የመስኩ ባሙያዎች እንደሚያሳስቡት ግብፅ በዓባይ ውኃ ፖለቲካ የአፍራሽነት ሚናዋን ትታ፣ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር የምትሠራባቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት እንዳሉ ማስታወቅ ያስፈልጋል። በኢትዮጵያ በኩል ያለው ግዙፉ ጥቁር ዓባይ (Black Nile) ከገባሮቹ ጀምሮ የውኃ ምንጭሆኖ እንዲቀጥል፣ የተፈጥሮ ልማትና ጥበቃ እንደሚያስፈልገው ይታወቃል፡፡ እግረ መንገዱንም ግብፅ በዚህ ረገድ ትብብርስታደርግ ውኃውን በፍትሐዊነት ለመጠቀም አያዳግትም፡፡ ግብፅ አልላቀቅ ካለችው የቅኝ ግዛት ታሪካዊ መብት ከምትለው አባዜ ስትወጣ፣ ሁሉም አገሮች በመተባበር ልማታቸውን ማፋጠን የሚችሉበት ዕድል ይፈጠራል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክአመንጭቶ ውኃው በአግባቡ ወደ ሱዳንም ሆነ ወደ ግብፅ እየተመመ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ለሌሎች የተፋሰሱ አገሮችም ልማት መልካም ምሳሌነትን እያሳየ መሆኑን ዓለምን ማስገንዘብ ይገባል፡፡
መላው ዓለም ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ መቃረቡን በተገነዘበበት በዚህ ጊዜ፣ ግብፅ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ እያየችው ያለው ጉዳይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የእርስ በርስ ግጭት ነው፡፡ ግብፅ በታሪኳ የምትታወቀው ኢትዮጵያን ለማጥቃት ወይም ለማተራመስ የምትነሳው ተዳክማለች ብላ በምታምንበት ጊዜ ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያንም የውስጥ ችግራችንን በስክነት ለመፍታት ባለመቻላችን ምክንያት የጥቃት ተጋላጭ እየሆንን ነው፡፡ የዓባይ ወንዝ ለኢትዮጵያ ምንም ዓይነት ጥቅም ሳይሰጥ ለዘመናት በከንቱ ድንበር ተሻግሮ መንጎዱ ሲያንገበግባቸው የኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ በወርኃ መጋቢት 2003 ዓ.ም. የግንባታው የመሠረት ድንጋይ መጣል በቀጥታ ሥርጭት ሲበሰር ያሳዩት የደስታ ሲቃና የዘመናት ቁጭት መቼም ቢሆን የማይረሳ ነው፡፡ ለግንባታው መሳካትም ከአገር ቤት እስከ ውጭያሉ ወገኖች ድረስ የተደረገው ርብርብ ዳግማዊ ዓድዋ ተብሎም ነበር፡፡ አሁን ምረቃው ተቃርቦ እያለም ቢሆን ያለው ስሜት ያንኑ ነው የሚያንፀባርቀው፡፡
ነገር ግን አሁንም ቢሆን እርስ በርስ መገፋፋቱና መጨራረሱ በፍጥነት ቆሞ በታሪካዊ ጠላት ፊት በአንድነት መቆም ካልተቻለ፣ ለ14 ዓመታት ከባድ ዋጋ ያስከፈለው ታላቅ ብሔራዊ ፕሮጀክት ከሥጋት ነፃ ይሆናል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ ውስጣዊ ችግሮችን በሰላማዊ አማራጮች በመፍታት ግብፅ አንዲት ጠብታ ውኃ ሳትጎድልባት በዓባይ ወንዛችን ላይ የመልማት መብት እንዳለን በጋራ ማሳየት ይጠበቅብናል፡፡ ዓለም ወደፊት እየገሰገሰ በግብፅ የቅኝ አገዛዝ አስተሳሰብ በወለደው ሴራ መጠለፍ አይገባም፡፡ ግብፅ ኋላቀር በሚባለው የቅኝ አገዛዝ አስተሳሰብ ተጠፍራ ኢትዮጵያን ወደፊት ከመገስገስ ለማስቆም የሚቻላት ከሆነ፣ ጥፋቱ የማንም ሳይሆን የእኛ የኢትዮጵያውያን መሆኑን ከገዥው ፓርቲ ጀምሮ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ከታሪክ ተወቃሽነት ማምለጥ እንደማይቻል ይገንዘቡ፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመቆም የሚያስችል ቁመና መያዝ ሲቻል፣ ግብፅ የኢትዮጵያን የመልማት መብት ለመገዳደር አንዳችም አቅም አይኖራትም፡፡
በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች መካከል ያለው የጂኦ ፖለቲክስ መሳሳብና መገፋፋት ራሱን የቻለ ችግር መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡ በተለይ የአፍሪካ ቀንድ አገሮች ለዘመናት ከግጭት፣ ከረሃብና ከስደት ውስጥ ለመውጣት ያልቻሉት የውክልና ጦርነት አራማጆች በመሆናቸው እንደሆነ ነጋሪ አያስፈልግም፡፡ በሱዳን ውስጥ የሚካሄደው ደም አፋሳሽ አደገኛ ጦርነት በእነ ማን እንደሚደገፍ ፀሐይ ከሞቀው ሰነባብቷል፡፡ ከኤርትራ እስከ ሶማሊያ ያለው የጠላትነት ስሜት ከኌላው በማን እንደሚገፋና እንደሚደገፍም የታወቀ ነው፡፡ ሁሉም አካባቢ ግብፅ እጆቿን አስረዝማ አስገብታ ኢትዮጵያን በተዘዋዋሪ ለማዳከም እንደምትሠራ ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ግብፅ በዚህ ወሳኝ ጊዜ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ሙሉ ትኩረቷን አድርጋ ስትነሳ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የእርስ በርስ ፍጅቱን በሠለጠነ መንገድ አስቁሞ እንደ ጥንቶቹ ጀግኖቹ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ለመቆም
አለመፈለግ በታሪክና በመጪው ትውልድ እንደሚያስጠይቅ ግንዛቤ ይያዝ፡፡ በህዳሴ ግድብ ላይ የተከፈተው የግብፅ ዘመቻም በጋራ ይመከት!
- Ethioian Reporter #GERD #የዓባይልጅ
ሞዐ ተዋህዶና ፋኖ ምንና ምን ናቸው
ጆሮ አይሰማው የለ!
{መምህር ፋንታሁን ዋቄ ገለታ ይግባህ}
መምህር ፋንታሁን ዋቄ ነገር መደበቅ አይሆንላቸውም ሞዐ ተዋህዶ ስለተባለው ቡድን አመሰራረትና ከፋኖ ጋር ያለውን ጥብቅ ቁርኝት ለማእዛ መሀመድ እስክትጮህ ድረስ በግልፅ ተንትኖ ነግሯታል።
መምህር ፋንታሁን ዋቄ በአጭሩ ሶስት ነገሮች Clarify አድርጎልናል።
አንደኛ ፦ ሞዐ ተዋህዶ የተባለ ሰለሞናዊ (ሃይማኖታዊ) መንግስት ለመመስረት የተቋቋመና ከረጅም ግዜ በፊት ሲሰራ የነበረ ቡድን እንዳለ።
ሁለተኛ ፦ አሁን ያሉት የፋኖ አመራሮችም የዚህ ቡድን አባል እንደሆኑና ፋኖም በሞዐ ተዋህሶ እሳቤ ስለተመጠመቀ Anti-Islam ሆኖ የተቋቋመ ቡድን እንደሆነ።
ሶስተኛው ፦ አሁንም ከሞዐ ተዋህዶ አቋም ጋር አብሮ የማይሄድ የፋኖ መሪ እንደሚሰደድ፣ እንደሚገደልና ከትግል እንደሚወገድ።
የሞዐ ተዋህዶ መስራች ከሆኑት አንዱ መምህር ፋንታሁን ዋቄ እነዚህን ሶስት ነገሮች በግልፅ ስላስረዱልን እግዜር ይባርኮት። እኛና አንዳንድ የነቁ የአማራ አክቲቪስቶች ስንጮህበት የነበረውን ጉዳይ ነው መጥተው ማረጋገጫ ማህተም የመቱልን።
መምህር ፋንታሁን ብዙ ነገር ነው የተናዘዙት። እንደሳቸው ትንተና በሞዐ ተዋህዶና በፋኖዎቻቸው አይን አማራ ማለት ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ያለው ብቻ ነው። "የአማራ" ትግል የተባለውም ለሽፋን እንጂ ውስጥ ውስጡን የኦርቶዶክስ ቤተእምነትን በትረመንግስት ማስጨበጥና የድሮውን ሰለሞናዊ መንግስት የመትከል አላማ ይዞ ነው የሚንቀሳቀሰው። ይሄንን መምህሩ ቃል በቃል ነው የተናገሩት። እንግዲህ ፋኖ ነኝ የምትይ ሙስሊም፣ ጴንጤ፣ ካቶሊክ፣ ኤቲይስት እርምሽን አውጪ ነው ያለሽ በአጭር አማርኛ!!! 😁
መምህር ፋንታሁን ሌላም ሚስጥር ነግሮናል። ይሄ ቡድን በትግራዩ ጦርነት ግዜ ሰራዊቱን ሲያስታጥቅና ለቀጣዩ ጦርነት ፋኖዎቹን ሲያዘጋጅ እንደነበር፣ (ትክክለኛው ፋኖ ከፊት ሲዘምት የኢትዮጵያን ሰራዊት ከጀርባ እየወጋ ሲታጠቅ የነበረውን ማለታቸው ነው) የተለያዩ ቪዲዮዎችንና ፅሁፎችን እያዘጋጀ አሁን ላሉ የፋኖ መሪዎች ከባባድ ሀይማኖታዊ ስልጠና ሲሰጥ እንደነበርም ገልፀዋል።
መምህር ፋንታሁን ዋቄ በዚህም አላበቃም። አሳምነው ፅጌ ይሄ በህቡእ የተደራጀ አክራሪ ሃይማኖተኛ ቡድን ላይ በደህንነቶቹ አማካኝነት ደርሶበት እንደነበርና የተወሰኑትን አስሮ ሲጠይቅ "ሰለሞናዊውን መንግስት ለማምጣት በህቡእ እንደተደራጁ" ይነግሩታል። አሳምነውም “ይሄማ የኔም አላማ ነው” በማለት ጭራሽ የነሱ አባል ሆኖ እንደቀጠለና አብሯቸው ይሰራ እንደነበር መምህር ፋንታሁን ነግሮናል።
በጣም የሚገርመው የመአዛ መሀመድ ድንጋጤ ነው 😁 መአዛ እስከዛሬ ይሄንን ነገር ሳታውቅ ነበር እንዴ የፋኖ አፋሽ አጎምባሽ ሆና ስትሰራ የነበረችው? የእውነት መአዛ መሀመድ ከምትኖርበት ሐገር ህግ ጋር በሚጋጭ መልኩ በጋዜጠኝነት ካባ ታጣቂን ሃይል ስትደግፍ፣ አማራና አማራ እንዲጋደል ገንዘብ ስታሰባስብ፣ ፌክ ዶክመንተሪ ስታሰራ፣ የሀሰት ዜናዎችን ስታሰራጭ ይሄን ሐገር ያወቀውን ሚስጥር አታውቅም ነበር ወይ የሚለው የእውነትም አጠራጣሪ ነው።
መምህር ፋንትሽ በኩራት የገለጠው የፋኖና የሞዐ ተዋህዶ ጥምረት ብዙ ነገሮችን ግልፅ ያደረገላችሁ ይመስለኛል። ያ ሁሉ ቤተክህነት ውስጥ ተቀምጦ ግርግር ሲያስነሳ የነበረ ካህን ሴራ፣ የከሸፈው "የጥቁር ለብሳችሁ ውጡ" አድማ፣ ገዳማትንና አቢያተክርስቲያናትን እንደምሽግ ተጠቅሞ ሲደረግ የነበረ ስልጠናና በየአውደምህረቱ ጓሮ ተቀብሮ የተገኘ የጦር መሳሪያ ክምችት በየቦታው ማን እንዳስነሳቸው ያልታወ የቤተክርስቲያን ቃጠሎዎችና በማግስቱ እሱን ተከትሎ ይደረጉ የነበሩ የሚዲያ ጩኸቶችና የክተት ጥሪዎች፣ የፋኖ አመራር ነን የሚሉ ሰዎች አንገታቸው ላይ የሚያስሯቸው ካህን እንኳን የማያደርጋቸው ትልልቅ መስቀሎችና ሃይማኖታዊ ቅርፅ ያላቸው ፕሮፖጋንዳዎች፣ የዚህ ሁሉ Mastermind የፋኖዎች አለቃና አስታጣቂው የሰለሞናዊ መንግስት አስመላሹና ሙስሊምና ፕሮቴስታንት ጠሉ ሞዐ ተዋህዶ ነበር። Case Closed!
በመጨረሻም በጋዜጠኛ ሽፋን የምትንቀሳቀሰው መአዚ ይሄ ቡድን በፋኖዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት ስትናገር የአቶ ፋንታሁን ዋቄ ምላሽ አጭርና ቁጣ የተሞላበት ነበር። ቃል በቃል እንዲህ ነበር ያላት. “ሞዐ ተዋህዶን ከፋኖ ትግል ውስጥ ይውጣ የሚሉ ሰዎች ራሳቸው ከትግላችን ይውጡ። ማን ባደራጀው ፋኖ ማን ያዛል?” 😁 ወይ ተአምረኛው ሞዐ ተዋህዶ!
ለማንኛውም ትግሉ የብሔር መስሎህ ነፍስህን የሰጠህ ሙስሊም ነፍስ ይማር እያልን የፋኖ ትግል Secular (ከሀይማኖት ነፃ) መስሎህ አሁንም የምትደግፍ ምስኪን ምእመንም ሆንክ ታጣቂ ቢያንስ አሁን ቆም ብለህ እንድታስብ እንመክራለን።
በመጨረሻም ሃቀኛውን ፋኖ አሶግዶ በህቡእ የተደራጀውን ነፍሰገዳይ ፋኖና የሰለሞናዊው ዙፋን አስመላሽ ቡድን ካባውን ገፍፈው እርቃኑን እንድንመለከተው ላደረጉን ለታጋይ ፋንታሁን ዋቄ እጅ እንነሳለን። 🫡
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም በመንግስትና ህዝብ የተገነባ ነው
ሐምሌ 15፣ 2017 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መቶ በመቶ በራስ አቅም በመንግስትና ህዝብ የተገነባ ነው አለ የግድቡ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት፡፡
ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ላይ እንዳስታወቀው፥ በበጀት ዓመቱ ለግድቡ 1 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል፡፡
በበጀት አመቱ የተሰበሰበው ገንዘብ ከዕቅዱ የ7 በመቶ ብልጫ እንዳለው የጽህፈት ቤቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍቅርተ ታምር በመግለጫው ላይ ጠቅሰዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን በሞራል፣ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በዕውቀት፣ በፕብሊክ ዲፕሎማሲ እና በአካባቢ ጥበቃ በመረባረብ የተመዘገበው ስኬት በትውልድ የሚዘከር ህያው ድል ነው ብለዋል፡፡
ግንባታው ከተጀመረበት ግዜ ጀምሮ በቦንድ ግዥና በስጦታ በሀገር ውስጥ 20 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር እንዲሁም ከዳያስፖራው ማህበረሰብ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል፡፡
በተጨማሪም ከልዩ ልዩ ገቢዎች 1.7 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የገለጹት ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፥ በአጠቃላይ እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ከህብረተሰቡ ከ23 ነጥብ 6 ቢሊየን በላይ ብር ተሰብስቦ ለግድቡ ግንባታ ውሏል ነው ያሉት።
እንደዚሁም በጠቅላላው የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት አንስቶ ከ84 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የጉልበትና የተፋሰሰ ሥራዎች መሰራቱም በመግለጫው ላይ ተነስቷል ሲል (ኤፍ ኤም ሲ) ዘግቧል።
subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://www.youtube.com/@EthiopianCommando
+2
የግብፅ ሚዲያዎች ተቃውሞ ፥ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ድል !
#maleda : ዛሬ ከጥዋት ጀምሮ የግብፅ ሚዲያዎች በጠቅላይ ሚኒስትራቸው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰሙ ነው። ምክንያቱ ደግሞ ግብፅ በBRICS አገራት ስብሰባ ላይ በብራዚል እየተሳተፈች ባለችበት ወቅት፣ የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ሲሳሳቁ መታየታቸው ነው።
ሚዲያዎቹ "ለምን ይሳሳቃሉ?" በሚል ትችት እያቀረቡ ነው።
ይህ ሁኔታ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል። ስም አይጠሩ (ግብፅ) ለዘመናት የኢትዮጵያን ህልውና ችላ ብላ፣ የአባይን ውሃ ያለ ምንም ገደብ ስትጠቀም ቆይታለች።
በእርግጥም፣ ኢትዮጵያ ምስጋና ሊገባት ሲገባ፣ አሁን ላይ ስም አይጠሩ (ግብፅ) ኢትዮጵያን እንደ ጠላት መቁጠሯ ብዙዎችን ሲያበሳጭ ቆይቷል።
ነገር ግን ታሪክ እየተቀየረ ነው! ኢትዮጵያ በውድ ልጆቿ ላብና ጥረት የተገነባውን ታላቁን ህዳሴ ግድብ የመጨረሻ ምዕራፍ ልታጠናቅቅና ሪባኑን ልትቆርጥ በዝግጅት ላይ ነች።
ከዚህም በላይ፣ የግብፅን መሪ ሲሲን በክብር እንግዳነት ጋብዛለች!
ለዘመናት በኢትዮጵያ ሰላም እንዳይመጣ እጇን ስትከትና ኢትዮጵያውያንን በንቀት ስትመለከት የነበረችው ስም አይጠሩ (ግብፅ)፣ አሁን ላይ እጇን ለኢትዮጵያውያን መስጠቷን እና የሚሆነውን በጉጉት እየተመለከተች መሆኑን በርካቶች እየተናገሩ ነው።
ይህ በብዙ ኢትዮጵያውያን ዘንድ በስም አይጠሩ (ግብፅ) ላይ እንደተገኘ ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ድል ተደርጎ እየተወሰደ ነው።
ይህ የሚያሳየው የኢትዮጵያ አቋም ምን ያህል እየጠነከረ እንደመጣ እና የዲፕሎማሲው መስመር ምን ያህል ውጤታማ እንደሆነ ነው።
https://www.youtube.com/@EthiopianCommando
👉 አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ 🇪🇹
✍️ወታደር ለሀገር ክብር
==============:::
✍️ወታደር መሆን ከራስ በፊት ለህዝብ ጥቅምና ለሀገር ክብር መቆም ማለት ነው። ብዙዎቹ ለሃገራቸው ካላቸው ጥልቅ ፍቅር የተነሳ ሃገራቸውን በእናታቸው ይመስሏታል። ሃገራቸውን እልፎች ለክብሯ ዘብ አድረዋል ለሉዓላዊነቷ በዱር በገደሉ ተዋድቀዋል።
✍️ዘመናት ባስቆጠረው የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ዘመን የማይሽረው ገድል የፃፈው የሃገር ባለውለታው ወታደሮቿ በርካቶች ናቸው። ዛሬም እንደትላንቱ ምቾታቸውን ትተው ከቤተሰቦቻቸው ተራርቀው ሃገራቸውን አስቀድመው ወገናቸውን አስደምመው በየጊዜው ፈተናዎች እያለፉ ታሪክ እየደገሙ ለክብሯ ሲል በርካቶች በየጥሻው ከጠላት እየተዋደቁ ታሪክ ሰርተው አልፈዋል።
✍️ኢትዮጵያ ሃገራችን የጀግና ማፈለቂያ ማህፀነ ለምለም ናት ስትደክም የሚያበረቱ ስታዝን የሚያፅናኑ ስትወጋ የሚጠግኑ እንዲሁም ወደ ኃላ ስትቀር የሚያዘምኑ የጀግና ወታደር ባለቤት ናት። ለወራሪዎች አይናቸውን በሚጥሉባትና በሚመኟት ጊዜ አንገት የሚቀላ ሰላሟን የሚያስጠብቅ ጀግና ወታደር አሏት።
✍️ወታደር ስትሆን ሃገር አብዝታ ታምንሃለች ህዝቦቿ ሁሉ ይመኩብሃል ከፈጣሪ በታች ሃገርና ሰላሙን በአደራ የሚሰጥ ለወታደር ነው ሁሌም ቢሆን አባቶች ሃገራቸውን እናቶች ክብራቸውን ወጣቶችና ታዳጊዋች ተስፋቸውን በአንተ ላይ ይጥላሉ። ለሃገር መቆም ከቻልክ አምነህ ትታመናለህ ለዚህም ነው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ማደርም ሆነ መዋል ለወታደር ኩራቱ ሆኖ በልቡ ያተመው።
✍️በአሁኑ ስዓት ለሃገረ ዘብ እደመቆም የሚያኮራ ተግባር የለም ምክንያቱም የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ባንዳዎች ሰላምና አንድነቷን ለማደፍረስ የሚቋምጡባት ሃገር ከመጠበቅ በላይ ትልቅ ሃላፊነት የለም ምክንያቱም ከአበው የወረሰከው የአደራ ቃ አለብህና።
✍️የኢትዮጵያ ወታደሮች በነበራቸው ብቃት፣ጀግንነት የሃገር ፍቅር ፅናትን የተላበሰና ወራሪዋቹን በየትኛውም ጊዜ መቀልበሰ የቻሉ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ቀንዲል የአርበኝነት ፋና ወጊ በመሆን የጥቁር ህዝቦች መከበሪያ የነፃነት መረዋ በመባል የተሞካሸላቸው ጀግኖች ናቸው።
✍️ወታደር ወዶና ፈቅዶ በጀግንነት የህይወትና የአካል መሰዋዕትነት በመክፈል የሰንደቅ ዓላማውን ክብር ማፅናት ነው። በዘመናት መካከል ሁሉ በዚህ የተጋድሎ መንገድ አልፈው ሃገር ያስከበሩ ብዙ ጀግኖች ናቸው።
✍️የውትድርና ህይወት በራሱ የቅብብሎሽ ሂደት ነው ታሪክን ማወሳትና ማጀገን ለትውልድ የሚተላለፍ የአደራ ቃል ነው ።
✍️የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ምወታደር ለሀገር ክብር
==============:::
✍️ወታደር መሆን ከራስ በፊት ለህዝብ ጥቅምና ለሀገር ክብር መቆም ማለት ነው። ብዙዎቹ ለሃገራቸው ካላቸው ጥልቅ ፍቅር የተነሳ ሃገራቸውን በእናታቸው ይመስሏታል። ሃገራቸውን እልፎች ለክብሯ ዘብ አድረዋል ለሉዓላዊነቷ በዱር በገደሉ ተዋድቀዋል።
✍️ዘመናት ባስቆጠረው የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ዘመን የማይሽረው ገድል የፃፈው የሃገር ባለውለታው ወታደሮቿ በርካቶች ናቸው። ዛሬም እንደትላንቱ ምቾታቸውን ትተው ከቤተሰቦቻቸው ተራርቀው ሃገራቸውን አስቀድመው ወገናቸውን አስደምመው በየጊዜው ፈተናዎች እያለፉ ታሪክ እየደገሙ ለክብሯ ሲል በርካቶች በየጥሻው ከጠላት እየተዋደቁ ታሪክ ሰርተው አልፈዋል።
✍️ኢትዮጵያ ሃገራችን የጀግና ማፈለቂያ ማህፀነ ለምለም ናት ስትደክም የሚያበረቱ ስታዝን የሚያፅናኑ ስትወጋ የሚጠግኑ እንዲሁም ወደ ኃላ ስትቀር የሚያዘምኑ የጀግና ወታደር ባለቤት ናት። ለወራሪዎች አይናቸውን በሚጥሉባትና በሚመኟት ጊዜ አንገት የሚቀላ ሰላሟን የሚያስጠብቅ ጀግና ወታደር አሏት።
✍️ወታደር ስትሆን ሃገር አብዝታ ታምንሃለች ህዝቦቿ ሁሉ ይመኩብሃል ከፈጣሪ በታች ሃገርና ሰላሙን በአደራ የሚሰጥ ለወታደር ነው ሁሌም ቢሆን አባቶች ሃገራቸውን እናቶች ክብራቸውን ወጣቶችና ታዳጊዋች ተስፋቸውን በአንተ ላይ ይጥላሉ። ለሃገር መቆም ከቻልክ አምነህ ትታመናለህ ለዚህም ነው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ማደርም ሆነ መዋል ለወታደር ኩራቱ ሆኖ በልቡ ያተመው።
✍️በአሁኑ ስዓት ለሃገረ ዘብ እደመቆም የሚያኮራ ተግባር የለም ምክንያቱም የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ባንዳዎች ሰላምና አንድነቷን ለማደፍረስ የሚቋምጡባት ሃገር ከመጠበቅ በላይ ትልቅ ሃላፊነት የለም ምክንያቱም ከአበው የወረሰከው የአደራ ቃ አለብህና።
✍️የኢትዮጵያ ወታደሮች በነበራቸው ብቃት፣ጀግንነት የሃገር ፍቅር ፅናትን የተላበሰና ወራሪዋቹን በየትኛውም ጊዜ መቀልበሰ የቻሉ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ቀንዲል የአርበኝነት ፋና ወጊ በመሆን የጥቁር ህዝቦች መከበሪያ የነፃነት መረዋ በመባል የተሞካሸላቸው ጀግኖች ናቸው።
✍️ወታደር ወዶና ፈቅዶ በጀግንነት የህይወትና የአካል መሰዋዕትነት በመክፈል የሰንደቅ ዓላማውን ክብር ማፅናት ነው። በዘመናት መካከል ሁሉ በዚህ የተጋድሎ መንገድ አልፈው ሃገር ያስከበሩ ብዙ ጀግኖች ናቸው።
✍️የውትድርና ህይወት በራሱ የቅብብሎሽ ሂደት ነው ታሪክን ማወሳትና ማጀገን ለትውልድ የሚተላለፍ የአደራ ቃል ነው ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም
Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://youtube.com/@tarikushamebo-g7s?si=nuX25KhPmVTc12J2
📌"አሜሪካና ምዕራባውያን ቀጠናዊ ቦታዎቻቸውን ኢራንን ለማጥቃት ከተጠቀሙበት ከአካባቢው እናጠፋቸዋለን" - የኢራን አብዮታዊ ዘብ
ኢራን በመካከላቸው ምስራቅ የሚገኙትን የአሜሪካን ወታደራዊ ሰፈሮች ልታጠቃ እንደምትችል አስጠነቀቀች።
ቴህራን ፕሬዝዳንት ትራምፕ አያቶላህ ኮሚኒን በተመለከተ ያወጡትን ማስጠንቀቂያ አውግዛለች።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ሌሊቱን ባወጣው መግለጫ፣ "አሜሪካና ምዕራባውያን ቀጠናዊ ቦታዎቻቸውን ኢራንን ለማጥቃት ከተጠቀሙበት ከአካባቢው እናጠፋቸዋለን" ብሏል።"እንደዚህ አይነት ድርጊቶች ውጤታቸው ለሌሎች የአካባቢው ሀገራተት አስከፊ ነው" ሲል አስታውቋል።
📌የኢራን ጦር የእስራኤል “ሄርምስ 900” የስለላ ሰው አልባ አውሮፕላን ተኩሶ ጣለ
ሰው አልባ አውሮፕላኑ በእስራኤላውያን የጦር መሳሪያዎች ውስጥ ከ"Heron TP-Eitan" ቀጥሎ ሁለተኛው ትልቁ ሲሆን ለስለላ እና ለስለላ ተልእኮዎች የተነደፈ ነው። የእስራኤል ጦር አውሮፕላኑ መመታቱን አምኗል።
አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command ✅
👇 subscrib አድርጉን👇
https://youtu.be/K0ftpHTJHtY?si=LVhEEXsZQ214qLvx
