es
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Ir al canal en Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Mostrar más
636
Suscriptores
Sin datos24 horas
-47 días
-1230 días
Archivo de publicaciones
❤ ከዚህም በኋላ በመቃብሩ ላይ እያበራ ያ መብራት ደግሞ ታያቸው ሥጋውም በዚያ እንዳለ ሁለተኛ በሕልም ነገራቸው ምዕመናንም አክብረው በግመል ጭነው ወደ አገሩ መካከል ወደ ሆሪን ወሰዱት ነስሪን ከሚባል አገር መካከል ሲደርሱ ግመሉ በዚያ ተንበረከከ እንዲነሣም መቱት መነሣትንም እምቢ አለ መኖሪያው በዚያ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንደሆነ አወቁ። በዚያም በስሙ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ሥጋውን በውስጥዋ አኖሩ ከእርሱም ብዙ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።                             ✝ ✝ ✝  ❤ #ሐዲስ_አባ_ማርቆስ፦ እርሱም በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች አርባ ዘጠነኛ ነው። ይህም አባት ከእስክንድርያ አገር ነው እርሱም በሥራው ሁሉ ቅድስናውን ጠብቆ ኖረ የተማረም ዐዋቂ ሆነ ለወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ በስም ሁለተኛ ነው። አባ ዮሐንስም ዲቁና ሾመው እጅግ መልካም ካህን ሆነ መጻሕፍትን በሚያነብ ጊዜ በአንደበቱ ቅልጥፍና በነገሩ ጣዕም የሚሰሙት ሁሉ ደስ የሚላቸው ሆነ። ከዚያም አባ ዮሐንስ ከእርሱ ጋራ አኖረው በሊቀ ጵጵስናው ሥራ ሁሉ ሥልጣን ሰጠው ያለ እርሱም ምክር አባ ዮሐንስ ምንም ምን አየሰሠራም። ❤ ከዚህ በኋላ በአባ መቃርስ ገዳም የምንኵስና ልብስ አለበሰው በዚያች የምንኵስና ልብስ በለበሰባትም ቀን ቅዱሳን አረጋውያን አንድ ጻድቅ ሰው መጥቶ በእርሱ ላይ እንዲህ ብሎ በሕዝብ ፊት "ይህ ስሙ ማርቆስ የሚባል ዲያቆን በአባቱ በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ሊሸመጥ አለው" ብሎ ትንቢት ተናገረለት። አባ ዮሐንስም የሚሞትበት ጊዜ ሲቀርብ አባ ማርቆስን ሊቀ ጵጵስና እንዲሾሙት ኤጲስቆጶሳቱን አዘዛቸው በእርሱ መሾምም ደስ አላቸው። ከአባ ዮሐንስ ዕረፍት በኋላም ያለ ፈቃዱ ሾሙት እርሱ ግን ከእርሳቸው ሸሽቶ ወደ በአስቄጥስ ሔደ ሰዎችንም ልከው አሥረው ወደ መንበረ ሢመቱ አመጡት። ከዚህ በኋላም ጸጥ ብሎ ስለ አብያተ ክርስቲያን የሚያስብ ሆኖ የፈረሰውን አነፀ ጠገነ። ❤ በዘመኑም መ*ና*ፍ*ቃ*ን*ን ጠባይ ከሕዝቡ ውስጥ አስወገደ ይኸውም በግብጽ አገር የተገለጡ ለብቻቸውም ቤተ ክርስቲያን ሠርተው የሚኖሩ ናቸው እርሱም አስተምህሮ መክሮ መልሶ ከመንጋዎቹ ጋራ አንድ አደረጋቸው። እግዚአብሔር በዚህ አባት እጅ ድውያንን በመፈወስ አጋንንትን በማስወጣት ብዙ ድንቆች ምልክቶችን ገለጠላቸው። ከእርስቸው አንዱን "አስተውል አንተ ያለ ፍርሀት በድፍረት ሥጋውንና ደሙን የምትቀበል ባትሆን ይህ ባላገኘህም ነበር ከእግዲህ ከክፉ ሥራና ከአንደበትህ ከሚወጣ ከከንቱ ነገርም ሰውነትህን ጠብቅ" አለው። ❤ በዘመኑም በምዕራብ ያሉ እስላሞች ይሸጡአቸው ዘንድ ብዙ ክርስቲያኖችን ከሮም ግዛት ውስጥ ማርከው ወደ እስክንድርያ አመጡአቸው ይህም አባት እጅግ አዘነ ከየገዳማቱና ከምእመናን ብዙ ገንዘብ ለምኖ ከእስላሞች እጅ በሠላሳ ሽህ የወርቅ ዲናር ዋጃቸው የነፃነትም ደብዳቤ ጽፎ ነፃ አወጣቸው። እንዲህም አላቸው "ወደ አገሩ መመለስ የሚሻ እኔ ስንቅ ሰጥቼ አሰናብተዋለሁ ከእኔ ጋራ መኖር የሚሻም ካለ እኔ እጠብቀዋለሁ" አላቸው። የተመለሱ አሉ ከእርሱ ዘንድ የቀሩትንም ጠበቃቸው አጋባቸውም። ❤ ከዚህም በኋላ ስለ መድኃኒታችን ቤተ ክርስቲያን አሰበ አደሳትም ሰይጣንም በአገር ውስጥ ሁከት አስነሥቶ በእሳት አቃጠላት ይህም አባት መልሶ ዳግመኛ አደሳት። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊአሳርፈው በወደደ ጊዜ ጥቂት ታመመ በፋሲካ በዓል በእሑድ ቀንም ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ተገለጠለት "ለሚወዱት እግዚአብሔር ስለ አዘጋጀው ተድላ ደስታ ነገረውና ሥጋውንና ደሙን ከተቀበልክ በኋላ ታርፋለህ" አለው። በነቃ ጊዜም እንዴት እንዳየ ከእርሱ ዘንድ ላሉ ኤጲስቆጶሳት ነገራቸው። ከዚያም የቅዳሴውን ሥርዓት ጀምሮ ቀድሶ ሥጋውን ደሙን ተቀበለ በዚያን ጊዜም ሚያዝያ 22 ዐረፈ። የሹመቱም ዘመን ሃያ ዓመት ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።                             ✝ ✝ ✝     ❤ በዚችም ቀን #አባታችን_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም ወርዶ ከከበሩ ቦታዎችና ከሊቀ ጳጳሳት ከባ ሚካኤል በረከትን ተቀበለ። የሁለቱ ቅዱሳን በረከትም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 22 ስንክሳር።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ካህናቲከ ይለብሱ ጽድቀ። ወጻድቃኒከ ትፍሥሕተ ይትፌሥሑ። በእንተ ዳዊት ገብርከ"። መዝ 131፥9-10። የሚነበቡት መልክታት 1ኛ ጢሞ 1፥1-12፣ 1ኛ ዮሐ 2፥22-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 12፥12-18። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችን ይሁንልን።

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta): ❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤            ❤ #ሚያዝያ ፳፪ (22) ቀን። ❤ እንኳን #በኒቅያ_ጉባኤ_ሊቀ+መንበር+ለነበረው አርዮስ ለአወገዘው ለእስክንድርያ ዐሥራ ዘጠኛ ሊቀ ጳጳሳት ለታላቁ አባት #ለአባ_እለእስክንድሮስ ለዕረፍት በዓል፣#ለሐዲስ_ሐዋርያ_ለታላቁ_አባት_ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም ከከበሩ ቦታዎች ለመባረክ ለሆዱበት መታሰቢያ ቀንና ከግብጽ ደቡብ ከእብክ አውራጃ ከሆሪን ከተማ ለሆነ ለከበረ አባት #ለአባ_ይስሐቅ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ  በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክንድርያ አርባ ዘጠነኛ ሊቀ ጳጳሳት #ከአባ_ማርቆስና ሃምሳ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳሳት ከከበረ አባት #ከአባ_ሚካኤል ከዕረፍታቸው መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                            ✝ ✝ ✝  ❤ #አባ_እለእስክድሮስ፦ ይህ አባት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳትም ዐሥራ ዘጠነኛ የሆነ ነው። ❤ ስለርሱም ሐዋርያዊ አባት አትናቴዎስ እንዲህ አለ "አባቴ እለእስክንድሮስ ተቀምጦ ወንጌልን አያነብም ቁሞ ያነባል እንጂ ከርሱ ጋራም ብርሃን አለ"። ሁለተኛም ስለርሱ ሲናገር "ወደርሱ እመምኔቶች መጥተው በእኛ ዘንድ ሰባት ሰባት ቀን የሚጾሙ ደናግል አሉ። በእጅዎቻቸውም ምንም ምን ሥራ አይሠሩም" ብለው ነገሩት። እርሱም "እኅቶቼ ሆይ እኔ ሁለት ቀን እንኳ ከቶ አልጾምኩም ፀሐይ እስኪገባም ቆይቼ አልበላሁም በልክ እበላለሁ በልክም እጾማለሁ በሌክ በመጠንም እሠራለሁ በልክ ይበሉ ዘንድ በልክም ይጾሙ ዘንድ በልክም ሥራ ይሠሩ ዘንድ ንገሩአቸው በበጎ ሥራ ሁሉ ይሰለፉ" አለ። ❤ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ደጎች ምዕመናን ናቸው እርሱም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ ሁኖ ከታናሽነቱ ጀምሮ በውስጥዋ አደገ። አባ መክሲሞስ አናጒንስጢስነት አባ ቴዎናስ ዲቁና፤ ተፍጻሜተ ሰማዕት ጴጥሮስም ቅስና ሹመውታልና እርሱም ከታናሽነቱ ጀምሮ ንጹሕ ድንግል ነው። ❤ አባ ጴጥሮስ በሰማዕትነት የሚሞትበት ጊዜ ሲቀርብ በግዞት ቤት ሳለ ይህ እለእስክንድሮስና አኪላስ ወደርሱ ገብተው ለመኑት ስለርሱ አባ ጴጥሮስ ይማልዱለት ዘንድ ሁለቱን ለምኖአቸዋልና። አባት ጴጥሮስ ግን በውግዘት ላይ ውግዘትን ጨመረበት እንዲህም ብሎ ነገራቸው "የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀደደ ልብስ ለብሶ ተገለጸልኝ ልብሴን አርዮስ ቀደዳት አለኝ። ይህም የባሕርይ አንድነቴን ለያት ማለት ነው ውግዘቱንም እንድጨምርበት እርሱ አዘዘኝ"። ደግሞ እንዲህ ገለጠላቸው አኪላስ ሊቀ ጵጵስና እንዲሾም ከርሱም በኋላም እለእስክንድሮስ እንደሚሾም አርዮስ እንዳይቀበሉት በምንም ሥራው እንዳይተባበሩት አዘዛቸው። አባ ጴጥሮስም ምስክርነቱን በፈጸመ ጊዜ አኪላስ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ የአባት ጴጥሮስንም ትእዛዝ ተላልፎ አርዮስን ከውግዘቱ ፈታው። ቅስናም ሾመው ስለዚህ አኪላስ በመንበረ ሢመቱ ያለ ስድስት ወር አልኖረም በድንገት ሞተ። ❤ ከዚህ በኋላ ይህ አባት እለእስክድሮስ ሊቀ ጵጵስና ተሹሞ በመንበረ ሢመቱ ላይ ተቀምጠ አርዮስንም ከወገኖቹ ጋራ አውግዞ አሰሠደደው። የአገር ታላላቆችም ከሕዝቡ መጡ ከውግዘቱ እንዲፈታውም ለመኑት። በውግዘት ላይ ውግዘትን እንዲጨምር እንጂ እንዳይፈተሠው አባት ጴጥሮስ እንደአዘዘው ነገራቸው። ❤ ከዚህም በኋላ አርዮስ ወደ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሒዶ በግፍ አወገዘኝ ብሎ እለእስክድሮስን ከሰሰው። ስለዚህም ንጉሥ ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት የከበሩ አባቶችን በኒቅያ ከተማ ሰበሰበ። ይህም አባት እለእስክድሮስ ተመርጦ ለጉባኤው ሊቀ መንበር ሆነ አትናቴዎስም ጸሐፊ ነበር። አርዮስንም ተከራክረው ክህደቱን ግልጽ አደረጉ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከአባቱ ከአብ ጋራ ከሕይወቱ መንፈስ ቅዱስም ጋራ በመለኮቱ ትክክል እንደሆነ አስረዱት። ከክህደቱ ባልተመለሰ ጊዜ አውግዘው ለይተው ከቤተ ክርስቲያን አሳደዱት። በአንድ ቃልም ጸሎተ ሃይማኖትን ከአባቶች ጋራ ሠሩልን ደግሞ በእርሳቸው ቤተ ክርስቲያን ለዘላለም የምትመራባቸው ሃያ ቀኖናን ሠርተው ወሰኑ። ❤ ከዚህም በኋላም ይህ አባት እለእስክንድሮስ ወደ መንበረ ሢመቱ ከድል ጋራ ተመለሰ። በበጎ አጠባበቅም መንጋውን ጠበቀ በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ መንበርም ዐሥራ ሰባት ዓመት ኖረ ሚያዝያ22 በሰላም ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አሜን።                           ✝ ✝ ✝                       ❤ #አባ_ይስሐቅ፦ ይህ አባት ከግብጽ አገሩ ደቡብ ከእብክ አውራጃ ከሆሪን ከተማ የሆነ ነው። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱም ስም ሶስና ነው ታናሽም ሁኖ ሳለ እናቱ ሙታ ብቻውን ያለእናት አባቱ እያሳደገው ኖረ። ❤ ጥቂት በአደገም ጊዜ የአባቱን በጎች የሚጠብቅ ሆነ አባቱም ሌላ ሚስት አገባ በዚያ ወራትም ታላቅ ረኃብ ሆነ የአባቱም ሚስት ትጠላው ነበረ ከጥቂትም በቀር እንጀራ አትሰጠውም ያንኑም ሁልጊዜ ለእረኞች ሰጥቶ እርሱ ግን እስከምሽት ይፈጸማል። ምሳውን ለእረኞች እንደሚሰጥና ሁልጊዜ እስከምሽት እንደሚጾም አባቱ ሰምቶ እውነት እንደሆነ ሊያይ ወደርሱ ሔደ። ቅዱሱም ሕፃን አባቱን መምጣት ዐውቆ በልብሱ ሦስት ጭቃ አድበልብሎ አሠረ እንደ ታሠረ በሚያየው ጊዜ ለአባቱ አምባሻ እንዲመስለው ብሎ። አባቱም በመጣ ጊዜ የልጁን ልብስ ፈትቶ አየ አምባሻም ሁነው አገኛቸው። የነገውንም ሰው ምግቡን ለእረኞች ከሰጠ በዛሬዪቱ ቀን ይህ አምባሻ ከወዴት ተገኘለት" ብሎ ጠየቀው እርሱም "በእውነት ሰጥቷል" አለ ሌሎችም ብዙዎች መጥተው በዚህ ነገር ምስክሮች ሆኑ አባቱም አደነቀ እግዚአብሔርንም አመሰገነ። ❤ ይህም አባት በአደገ ጊዜ አባ ኤልያስ ወደሚባል ሰው ሔዶ መንኵሶ በዚያ እየተጋደለ ብዙ ዓመታት ኖረ። አባ ኤልያስም በዐረፈ ጊዜ በርኑግ ወደሚባል ገዳም ሔዶ ስሙ ዘካርያስ ከሚባል አረጋዊ ዘንድ በታላቅ ገድል ተጠምዶ ኖረ። አባቱም ያገኘው ዘንድ በአገሮች ሁሉ ይዞር ነበር በዚህ በበርኑግ ገዳምም በአገኘው ጊዜ ከእርሱ ጋራ እንዲመለስ አባቱ ለመነው አይሆንም አለ አባ ዘካርያስም ከአባቱ ጋራ ይሔድ ዘንድ እስከሚዐርፍም ከእርሱ ዘንድ እንዲኖር አዘዘው ይህ ቅዱስም ከአባቱ ጋራ ሔዶ እስከሚዐርፍ ድረስ ከእርሱ ዘንድ ኖረ። ❤ አባቱም በዐረፈ ጊዜ አባቱ የተወውን ገንዘብ ሁሉንም ለድኆችና ለምስኪኆች ሰጠ ከከተማውም ጥቂት ራቅ ብሎ ለራሱ ታናሽ ማደሪያ ሠራ በሰላም እስከሚዐርፍባት ቀን በጾም በጸሎት በስግደት ኖረ በዐረፈ ጊዜም በመልካም ቦታ አኖሩት ከዚያም ተሠወረ። ከብዙ ዘመናትም በኋላ እግዚአብሔር ሊገልጠው ወዶ በመቃብሩ ላይ መብራት ሲበራ እህል ለሚዐጭዱ ሰዎች ሦስት ቀን ያህል ታየ ሊያዩትም ወደቦታው ሲደርሱ ያ መብራት ከእርሳቸው ይሠወራል በሁሉ ዘንድ እስቲሰማም እንዲህ ሁኖ ኖረ።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ሚያዝያ ፳፩ (21) ቀን። ❤ እንኳን አምላክን ለወለደች #ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም ወራዊ በዓልዋ መታሰቢያ፣ ለከበረ አባት #ለአባ_ቡሩታዎስ ለዕረፍቱ በዓል  እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ከቅዱሳን_አካርክስ_ከቅሪይስና #ከይወራስ ከመታሰቢያቸው  ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                       ✝ ✝ ✝  ❤ በዚች ቀን አምላክን የወለደች #የእመቤታችን_የከበረች_ድንግል_ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው። እርስዋ ወደ ተወዳጅ ልጅዋ ስለ ሰው ልጆች ትማልዳለችና ስሟን ለምንጠራ ለእኛ ኃጢአታችንንም ያስተሠርይልን ዘንድ ስለዚህም በየወሩ ሁሉ መታሰቢያዋን ልናደርግ ይገባል። ልመናዋ በረከቷ ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።                            ✝ ✝ ✝  ❤ #የከበረ_አባት_አባ_ቡሩታዎስ፦ ይህም አባት የአቴና አገር የሆነ ከምሁራን ጥበበኞች አንዱ ነው እርሱም ደግሞ ደራስያን ከሆኑ ከአረጋውያን መምህራን ጋራ የተቆጠረ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስንም ተገኝቶት ስለ ቀናች ሃይማኖት ተከራከረው። የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት የቀናች እንደሆነች ተረድቶ አመነ በሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እጅ ተጠምቆ የቤተ ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ተማረ። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ በአቴና አገር ቅስና ሾመው። በታላቂቱ አገር በአቴና የመምህራን አለቃ ከሆነ ዘመደ ላሕም አብሮባ ከተባለ ከከበረ ዲዮናስዮስ ጋራ ተገናኘ። እርሱም የክብር ባለቤት ስለሆነ ጌታ ኢየሱስ ሃይማኖት ብዙ ገለጠለት ከውስጡ ሥውር የሆነበትንም ተረጐመለት እጅግም ዐዋቂ ሆነ። ❤ ይህም አባት አምላክን የወለደች እመቤታችን የከበረች ድንግል ማርያም በዐረፈችበት ቀን ደርሶ በሐዋርያት መካከልም ቆመ በደረሰው ማኅሌትና ዝማሬ ጣዕም ባለው በመሰንቆ በዜማ ድምጽም አጽናናቸው። ከአይሁድና ከአሕዛብም ብዙዎቹን መልሶ ወደ ክብር ባለቤት ወደ ጌታ ክርስቶስ እምነት አስገባቸው። በተሰጠችውም ጸጋ ነግዶ ታላቅ ትርፍ አስገኘ። ❤ ሐዋርያትም ኤጲስቆጶስነት ሊሾሙት በፈለጉ ጊዜ ጌቶቼ ይቅርታ አድርጉልኝ እኔ ለዚች ለከበረች ሹመት አልበቃሁምና የቅስናንም አገልግሎት ልፈጽም አልቻልኩምና ተውኝ ብሎ ማለዳቸው። በዕውቀቱና በሥራው ሰማያዊ ሀብትን ተቀብሎ ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔር ሚያዝያ21 ቀን ሔደ። የአባ ቡሩታዎስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።                                                                        ✝ ✝ ✝  ❤ "#ሰላም_ለብሩታዎስ_ዘዘመረ_ማዕከለ_ሐዋርያት ዘኤፍራታ። #በጺሖ_ለማርያም ጊዜ ዕረፍታ። ወአመ ፈቀዱ ይሢምዎ ዘኢጲስቆጶስ መዐረገ ፆታ። ኢይክል ይቤ ሢመታተ መንታ። እስመ ኢያብጻሕኩ ለቅስና ሠናየ መልእክታ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_21።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት። ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ"። መዝ 44፥9-10።  የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥39፥57።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኵሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር። ኵሉ ክብራ ለወለተ ንጉሠ ሐሴቦን። በዘአዝፋረ ወርቅ ዑፅፍት ወኊብርት"። መዝ 44፥12-13። የሚነበበው መልዕክታት ኤፌ 5፥15-21፣ 1ኛ ጴጥ 2፥4-11 እና የሐዋ ሥራ 17፥30-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 17፥1-11። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                          

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ሚያዝያ 20 (፳) ቀን። ❤ እንኳን ደንደራ ከሚባል አገር ደግሞ እልበደራ ከሚባል አገር ለሆነ #ለቅዱስ_በብኑዳ ሰማዕትነት ለተቀበለት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_በብኑዳ፦ ይህ ቅዱስ ለብቻው የሚኖር ዕውነተኛ ተጋዳይ ነው እግዚአብሔር መልአክም ተገልጦለት "የመቀደሻ ልብስ ለብሰህ ወርደህ ለመኰንኑ ተገለጥለት" አለው። በዚያን ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ከመርከብ ወርዶ ወደዚያች አገር ወደብ መድረሻው ጊዜ ነበር። ይህንንም ባሕታዊ ፈልጎት አላገኘውም ነበር። እነሆ ቅዱስ በብኑዳም በፈቃዱ መጥቶ ወደ መኰንኑ ሔዶ "በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የማምን በግልጥ እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ በታላቅ ቃል ጮኸ። መኰንኑም ፈልጎ ያጣው የታወቀ ባሕታዊ መሆኑን በአወቀ ጊዜ እንዲአሠቃዩት በእግር ብረትም አሥረው ከጨለማ ቤት እንዲጥሉት አዘዘ። በዚያን ጊዜም ብርሃን ወጣ የእግዚአብሔር መልአክ ከሕማሙ ፈወሰው አበረታው አጽናናውም። ❤ በዚያችም አገር ስሙ ቄርሎስ የሚባል ምዕመን ሰው ነበር ከእርሱ ጋራም ሚስቱና ዐሥራ ሁለት ጐልማሶች ልጆቹ አሉ። እነዚህን ሁሉንም የከበረ በብኑዳ አስተማራቸው አጽናንቷቸውም ራሶቻቸውን ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ሙተው አክሊል ተቀበሉ። ❤ አርያኖስም ተቆጥቶ በቅዱሱ አንገት ከባድ ደንጊያ ሰቅለው ወደ ባሕር ይጥሉት ዘንድ አዘዘ በእግዚአብሔር ኃይልም ከድንጋዩ ጋራ ዋኘ። ደግሞ ከሰሎን ዛፍ ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ያቺም ሰሌን ዐሥራ ሁለት ዘለላን አፍርታ ለመጪው ትውልድም መታሰቢያ ሆነች። ከዚህም በኋላ የከበረች ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ። የቅዱስ በብኑዳ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 20 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝               ❤ "#ሰላም_ዕብል_ለበቡኑዳ_ሰማዕት። እንተ አግሀደ ብርሃነ በቤተ ጽልመት። ወአመ ሰቀልዎ ሎቱ መልዕልተ በቀልት። አውጽአት ፍሬ በይእቲ ሰዓት። እስከ ጉቡአን አንከሩ እምዛቲ ትእምርት"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርከ) #የሚያዝያ_20።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባእ ቅድሜከ ገዓሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 3፥7-12፣ ያዕ 3፥13-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥38-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 25፥14-31። የሚቀደሰው ቅዳሴ ሠለስቱ ምዕት ወይም የቅዱስ ዲዮስቆሮ ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓለ ሃምሳ ሶሞን። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለክብር ባለቤት ለጌታችን ለአምላካችን ­ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለዳግም ትንሣኤ በዐል በሰላም አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሉ ሉያ "#ይትፌሣሕ_ሰማይ_ወትትሐሠይ_ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ኅምዝ ወይወውዑ አድባር ወአውግር ወኵሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዐባይ ፍሥሓ በሰማያት #ወምድርኒ_ትገብር_ፋሲካ_ተሐጺባ_በደመ_ክርስቶስ። ትርጉም፦ ምድርና ሰማይ ይደሰቱ፣ ቀርነ መለከትም ይነፋ፤ ተራሮችና ኮረብቶችም የዱር ተክሎችም ይደሰቱ፤ ዛሬ በሰማያት ታላቅ ደስታ ሆነ፣ #ምድርም_በክርስቶስ_ደም_ታጥባለችና_ፋሲካ (ደስታን) ታደርግ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ዳግም_ትንሣኤ፦ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤ ሳምንት ለሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ተገለጠለት በእጆቹና በእግሮቹ ውስጥ የችንካሮቹን ምልክትም አሳየው የቶማስንም እጅ ይዞ በመለኮታዊ ጐኑ ውስጥ አኖረውና በጦር የተወጋበትን ቦታ አሳየው ቶማስም "ጌታዬና ፈጣሪዬ መነሣትህን አመንኩ" አለ። ጌታችንም "ብታየኝ አመንከኝ የሚመሰገንስ ሳያየኝ የሚአምንብኝ ነው" ብሎ መለሰለት። ስለዚህ፦ ዳግመኛ ጌታችን ለሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ባለበት ለሁለተኛ ጊዜ ስለተገለጠ ዕለቱ "ዳግም ትንሣኤ" ተባለ። ዮሐ 20፥24-29። ❤ በትርጓሜ ወንጌልም እንዲህ ይላል ቶማስ በመድኃኒታችን ጐን ውስጥ እጁን በአስገባ ጊዜ እጁ በመለኮት እሳት ተቃጠለ በመለኮቱም ደግሞ በታመነ ጊዜ እጁ ከመቃጠል ዳነች። ምንጭ፦ የሚያዝያ 6 ስንክሳር።                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም። ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን። ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ"። መዝ 77፥65-66። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 28፥1-ፍ.ም፣ ማር16፥1-ፍ.ም፣ ሉቃ 24፥1-13።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "ይትነሣ እግዚአብሔር ወይዘረዉ ፀሩ። ወይጒየዩ ጸላዕቱ አምቅድሙ ገጹ። ከመ የሐልቅ ጢስ ከማሁ የሐልቁ"። መዝ 67፥1-2 ወይም መዝ 117፥24-25 ። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 15፥1-20 ወይም 1ኛ ቆሮ 15፥20-41፣ 1ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም ወይም 1ጴጥ 1፥1-13 እና የሐዋ ሥራ 23፥1-10 የሐዋ ሥራ 2፥22-37። የሚነበው ወንጌል ዮሐ 20፥20-ፍ.ም ወይም ዮሐ 20፥1-19 ወይም ዮሐ20፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ከቊርባን_በኋላ_ምስባክ፦ "እምሥራቀ ፀሐይ እስከነ ዓረብ። ይትአኰት ስሙ እግዚአብሔር። ልዑል እግዚአብሔር መልዕልተ ኵሉ አሕዛብ"። መዝ 112፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ17፥1-ፍ.ም። ❤ መልካም የዳግም ትንሣኤ በዐል ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤            ❤ #ሚያዝያ ፲፱ (19) ቀን። ❤ እንኳን #ለአርማንያ_ሰው_የፋርስ_ኤጲስቆጶስ ለከበረ #አባ_ስምዖንና ከእርሱም ጋራ #መቶ_ሃምሳ_ሰማዕታት ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ስምዖንና_መቶ_ሃምሳ_ሰማዕታት፦ ይህ አባት የአርማንያ ሰው የፋርስ ኤጲስቆጶስ ነው። ❤ ይህም ቅዱስ ትከሻ ነቃይ የተባለ የሐርመዝ ልጅ ሳቦር ግዛት ውስጥ ይኖራል ይህም ሳቦር ሌላውን ንጉሥ ድል በሚያደርግ ጊዜ አሥሮ ትክሻውን ይመዝዘዋልና ትከሻ ነቃይ ተባለ። ይህም ከሀዲ ለጣዖት እንዲሰግዱ እያስገደደ ምዕመናንን በጽኑዕ ሥቃይ አሠቃያቸው። ❤ ይህም የከበረ አባ ስምዖን ለንጉሥ ሳቦር መልእክት ጽፎ ላከለት እንዲህ የሚል "የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ የዋጃቸው ከሰው ተገዢነት ድነዋል የክብር ባለቤት የክርስቶስ ተገዥ ናቸውና። ስለዚህ ተገዥ መሆን ከተሠራው ሕግ አብዝቶ መገበርም አይገባቸውም። የሕያው እግዚአብሔርን ሕግ ለለወጡ ከሀድያን አይገዙም። ስለ እርሳቸው ደሙን በአፈሰሰ በክብር ባለቤት በክርስቶስ ስም እንዲሞቱ እነርሱ ይመርጣሉ"። ንጉሥ ሳቦርም መልእክት በአነበበ ጊዜ በዚህ አባት ላይ እጅግ ተቆጣ በሁለት ሰንሰለትም አሥሮ በእሥር ቤት ጣለው በዚያም ሃይማኖታቸውን ክደው ሰማይን ያመለኩ እነርሱም በሌላ የታሠሩ ብዙ እሥረኞችን አገኘ። ይህ ቅዱስም ገሠጻቸው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው መሰገሩ ራሶቻቸውንም ቆረጡአቸውና የሕይወት አክሊል ተቀበሉ። ❤ ከዚህም በኋላ ይህን አባት ወደ ምስክርነት ሸንጎ አቀረቡት ከእርሱም ጋራ መቶ ሃምሳ ሰዎች አሉ እነርሱም አንገታቸውን እስከ ቆረጡአቸውና አክሊል እስከ ተቀበሉ ድረስ ያጽናናቸው ነበር። ከእርሳቸውም አንዱ ሰይፍን ከመፍራት የተነሣ ደንግጦ ሃይማኖቱን ሊክድ ወደደ በዚያ ከቆሙት አንዱ "አትደንግጥ የሰይፍ በትር ዓይንህን ከሸፈንክ ምንም አይደለም ጽና። ከሰማዕታት ጋራ ተቆጥረህ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ጋራ ለዘላለም ነግሠህ ትኖራለህ" ብሎ አጽናናው። እንዲሁም አደረገ የሕይወት አክሊልንም ተቀበለ። ስሙ ባሴቅ የተባለ ያንን ያጥናናውን ሰው ከሰሱት ንጉሡም አስቀርቦ ምላሱን አስቆረጠው። ቆዳውንም አስገፈፈውና ነፍሱን አሳለፈ የድል አክሊልንም ተቀበለ። ❤ ከዚህም በኋላም የከበረ ስምዖንን ወደ እርሱ አቅርቦ "ለአማልክት ስገድ ያለዚያ በጽኑ ሥቃይ አሠቃይሃለሁ" አለው። ቅዱስም ትእዛዙን አልሰማም ሥቃዩንም አልፈራም ያን ጊዜም ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዝዞ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕታትን አክሊል ተቀበለ። በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ19 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለስምዖን_ለአርማንያ_ሞገሳ። ወለሀገረ ፋርስ ኤጲስቆጶሳ። በዐውደ ኵነኔ ወስምዕ ትዕግሥተ ሕማም ዘለብሳ። ሰላም ሰላም ወ፻ ወ፶ሳ። እለ ነፍሳቲሆሙ ክብረ በሰማይ ወረሳ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_19።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ሚያዝያ ፲፰ (18) ቀን። ❤ እንኳን #ለቅዱስ_ሱስንዮስ አገልጋይ #ለቅዱስ_አውሳቢዮስ ለዕረፍቱ በዓል፣ #ለአባ_ብሶይ_ወንድም_ለአባ_ጴጥሮስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከበጠርሴስ _አገር ውስጥ መከራ ከተቀበሉ #ከከበሩ_ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የቅዱስ_ሱስንዮስ_አገልጋይ_ቅዱስ_አውሳቢዮስ፦ ከዲዮቅልጥያኖስ ቅዱስ ሱስንዮስን በሚያሠቃየው ጊዜ ንጉሥ ሆይ "ለሱስንዮስ አውሳብዮስ የሚባል አገልጋይ አለው እርሱም በፍጹም ልቡ እንደ ጌታው ክርስቶስን ያመልከዋል የአንተን አማልክት አያመልኩት" አሉት "አምጡት" አለ። ወደርሱም በቀረበ ጊዜ ስለ ሃይማኖቱ ጠየቀው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ታመነ። ንጉሡም ብዙ አባበለው አማልክቶቹን ማምለክ በመተዉም ገሠጸው ቅዱሱም የእውነተኛ አምላክ የእግዚአብሔር አምልኮ በመተዉ ንጉሡን መልሶ ገሠጸው። ስለዚህም ንጉሥ ቊጣን ጨምረ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ይህም ቅዱስ ከጌታው ከሱስንዮስ ቀድሞ የሰማዕትነትነት አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። የቅዱስ አውሳቢዮስ  በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የአባ_ብሶይ_ወንድም_አባ_ጴጥሮስ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ሲድራቅ የእናቱ ስም ማርያም ነው። ይህንንም ቅዱስ በወለዱት ጊዜ ከርሳ የምትባል የእናቱ እኅት ወስዳ ከልጅዋ ጋራ አሳደገችው። ሰባት ዓመትም በሆናቸው ወደ መምህር ወሰደጀቻቸውና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሕጉንም ተማሩ በጾም በጸሎትም ሲጋደሉ ኖሩ። የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ተገለጠላቸው ስለ ክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ምስክር እንዲሆኑ ነገራቸው። ❤ ከጥቂት ወራትም በኋላ ሰይጣን ከዲዮቅልጥያኖስን አስቶት ለጣዖት በሰገደ ጊዜ እሊህን ቅዱሳን ክርስቲያኖች እንደሆኑ ነገር ሠሩባቸው። የእንዴናው ገዥ አርያኖስም ወደርሱ አስቀርቦ ለጣዖት እንዲሰግዱ ግድ አላቸው እምቢ በአሉትም ጊዜ ደማቸው እስኪፈስ ከባላ ላይ ሰቅለው እንዲገርፋቸው አዘዘ። ከጾምና ከስግደት የተነሣ ሥጋው ስለደከመ የሥቃዩ ሕማም ለአባ ጴጥሮስ ታወቀው ያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ከሕማሙ ፈወሰው። አርያኖስም አይቶ አባ ጴጥሮስ ወደ ምሥራቅ አገር ወስደው በዚያ ራሱን በሰይፍ  አዘዘ። ❤ አባ ብሶይም እንዲቆርጡት በእሥር ቤት እያለ መልአክ ነጥቆ ወደ ወንድሙ ወደ ጴጥሮስ አደረሰው። እርስበርሳቸውም ተቃቅፈው ተሳሳሙ በሰማያዊት ኢየሩሳሌምም እንዲሰበስባቸው ወደ ጌታችን ጸለዩ እነሆ ወደ እርሳቸውም ከሰማይ ቃል መጣ። እንዲህ የሚል "ተጋዳዮች ሆይ በሰማያት በብዙ ጉባኤ መካከል ትኖራላችሁና ሰላም ይሁንላችሁ ሥጋችሁም በምድር አይለያይም"። ከዚህም በኋላ መልአክ አባ ብሶይን ወደ እሥር ቤት መለሰው። ጭፍሮችም ኃይል ድል አድራጊ አባ ጴጥሮስ ራሱን ቆረጡ ሥጋውንም በዕንጨት ላይ ሰቀሉ። አባ ብሶይም በጭልታ ይሰደው ዘንድ የእሥር ቤት ጠባቂውን ለመነው ሒዶም የአባ ጴጥሮስን ሥጋ ዋጀው በሽቱ አድርጎ ገንዞም በሥውር ቦታ ቀበረው። የአባ ጴጥሮስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ18 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለጴጥሮስ_ሠናይ_ላህይ_ወገጹ። በምግባረ ንዱቁ ወበሃይማኖት ሕኑጽ። ሶመ አመትሮ መኰንነ ግብጽ። ድኅረ ወድቀ መልዕልተ ምድር ርእሱ ቅሩጽ። ሥጋሁ ወዐለ ስቁለ በዕፅ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_18።

ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ ተወያየ። ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በ
+4
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ ተወያየ። ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በስቅለት ዕለት በፎኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በቅድስት ድንግል ማእያም ዙሪያ ያስተላሐፉትን ትምህርት በተመለከተ ውይይት አድርጓል። በብፁዕነታቸው  የተላለፈውን ትምህርት ዝርዝር ሁኔታን በመመርመርም ውሳኔ ለማስተላለፍ  ይቻል ዘንድ ሁሉም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት በተገኙበት  ለአርብ ሚያዚያ ፲፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ/ም ቀጠሮ ተይዞል። በተያያዘ ዜና የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ፍራንሲስ ስርዓተ ቀብር ላይ፦ ብፁዕ አቡነ ዲዮናሲዩስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ(ዘአውሮፓ) ቤተክርስቲያናችንን በመወከል እንዲገኙ ተወስኗል። © የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለትንሣኤ_አምስተኛ_ቀን_ለቅዱስ_አዳም መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                        ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_መዝሙር፦ "ይቤሎ እግዚኡ ለአዳም ተፈሣሕ ዮም/፪/"። ትርጉም፦ ጌታ አዳምን ዛሬ ተደሰት አለው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ።                 ❤ #ዕለተ_ሐሙስ።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐሙስ_አዳም_ሐሙስ_ይባላል፦ በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና "የአዳም ኀሙስ" ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ 24-25-49። ❤ #ምስባክ_መልዕክታት_ወንጌል_ቅዳሴ እንደ ብርሃነ ትንሣኤ። መልካም የበዓለ ትንሣኤ ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤        ❤ #ሚያዝያ ፲፮ (16) ቀን። ❤ እንኳን #ለወንጌላዊው-ቅዱስ-ዮሐንስ ረድኡ (አገልጋዩ) ለሆነ ለበአርማ አገር ኤጲስቆጶስ #ለቅዱስ-አንቲቦስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከሰማዕት-ሳባ ከመታሰቢያው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_አንቲቦስ፦ እርሱም የመለኮትን ነገር ለሚናገርና ለወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ረድኡ ነው። እርሱም ከአይሁድ ወገን በግዛቱ ውስጥ አንድ ሰው የሚታይ እስከ አልሆነ ድረስ አይሁድን ያጠፋቸውና ኢየሩሳሌምንም በአፈረሳት በአስባስያኖስ ልጅ በግማትያኖስ ዘመን ነበር። ከእስራኤል መንግሥት ትውልድ ያላቸውንም ብዙዎችን ገደላቸው ለመንግሥቱና ለራሱ ስለ ፈራ ነው። የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ አምላካቸውና ንጉሣቸው ድል አድራጊና እርሱም ወገኖቹ እንደሆኑ ክርስቲያኖች ይናገራሉና ስለዚህ ከአማንያን ብዙዎችን ገደለ። ❤ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስም ከእርሱ ሸሸ የዮሴፍ ልጅ በሮሜ ከተማ ታሥሮ ሳለ ወደ ኢየሩሳሌም ጭፍራ ልኮ የይሁዳን ተወላጆች ወደርሱ አስመጣቸው የክብር ባለቤት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት በጠየቃቸው ጊዜ ክርስቶስ ሰማያዊ ንጉሥና በሰማያት የሚኖር እንደሆነ በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ለሁሉም እንደየሥራው ሊከፍለው ዳግመኛ ይመጣ ዘንድ እንዳለው አስረዱት። ይህንንም ሰምቶ እጅግ ፈራ ክርስቲያኖችንም ማሠቃየቱን ተዋቸው። ❤ ቅዱስ አንቲቦስ ግን የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስን ሊአስክደው ሽቶ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው እርሱም በሥቃዩ ውስጥ በመታመን ጸና። ከዚህም በኋላ ከናስ በተሠራ በላም ፈጅ ጋን ውስጥ አድርገው ከበታቹ እሳትን አነደዱ እርሱም በውስጧ ሁኖ ስለከበረ ስሙ ምስክር ሊሆን ያደውን እግዚአብሔርን ፈጽሞ ያከብርና ያመሰግን ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ስሙን ለሚጠሩና መታሰቢያውን ለሚያደርጉ ከነፍስ ከሥጋ ደዌ ሁሉንም ይፈውሳቸው ዘንድ እግዚአብሔር ፈለገ።  ከዚህም በኋላ ከነሐስ በተሠራው በላም ፈጅ ውስጥ የምስክርነቱን ተጋድሎ ፈጽሞ ሚያዝያ 16 ቀን ነፍሱን ሰጠ። በድኑንም ሲጥሉት ምዕመናን አንሥተው በታላቅ ክብር ፈጽሞ እያመሰግኑ ወስደው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖሩት። ❤ እርሱም አስቀድሞ በግዞት ቤት ሳለ ከወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ የሚያጽናናውና የሚያአረጋጋው "ቸር ጠባቂ እረኛና ታማኝ አገልጋይ ካህን" የሚለው መልእክት ወደርሱ መጣ። እንዲህም ብሎ ሁለተኛ ነገረው "በሰማዕትነት እንደሚሞት አንተ በከበሩ ሐዋርያትና ከሰማዕነት ጋራ ተቆጥረሃል"። ❤ ደግሞ ከሥጋው ጣፋጭ የሽቱ ቅባት እንደሚፈስ ስለርሱ ተነገረ እርሱም መዓዛው እጅግ ጣፍጭ የሆነ በእምነት ለሚሻው ሁሉ እስከ ዛሬ ጠቃሚ የሆነ ነው። የቅዱስ አንቲቦስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።                      

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለትንሣኤ_አራተኛ_ቀን_ለቅዱስ_አልዓዛር መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ።                                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ጽፍት፦ "ተንሥአ ወአንሥአ ኵሎ ሙታነ ተንሥአ ወፈወሶሙ ለሙቁሐን ተንሥአ ወፈወሶሙ ለሙቁሐን። አዝ............... በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን ወአግዓዘ ነፍሰ ጻድቃን። አዝ………………… ለአልዓዛር ተንሥእ ዘይቤሎ ወእውርኒ ዘፈወሶ በቃሉ። አዝ…………………… ትንሣኤሁ ገብረ በሰንበት በሣልስት ዕለት"። ትርጉም፡- ሙታንን ሁሉ ያስነሳ የታሠሩትንም የፈወሳቸው በታላቅ ሥልጣን ተነሣ የጻድቃን ነፍሳትን አጋዘ አልዓዛን ተነሥ ያለው ዕውሩንም የፈወሰው ትንሣኤውን በሰንበት አደረገ።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_መዝሙር፦ "ዛቲ ፋሲካ ዕለተ በርህ ወዋካ ዛቲ ፋሲካ(፪)"። ትርጉም፦ ይህቺ ፋሲካ የብርሃን ቀን ናት። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ።                   ❤ #ዕለተ_ረቡዕ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ረቡዕ_አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልዓዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሚያዝያ ፲፬ (14) ቀን። ❤ እንኳን #በእስክንድርያ_ለተሾሙ ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ አምስተኛ ለሆነ ለከበረ አባት #ለአባ_መክሲሞስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_መክሲሞስ፦ ይህም አባት መንፈሳዊና በሥራ ሁሉ እግዚአብሔርን የሚፈራ ነው። እርሱም ከእስክንድርያ ሰዎች ወገን ነው ወላጆቹም ሃይማኖታቸው የቀና ነበር የዮናውያንንም ጽሕፈትና መጽሐፋቸውን ጥበባቸውንም ሁሉ ተምሮ ፍጹም አዋቂና አስተዋይ ሆነ በዮናኒ ቋንቋ። ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ልዑል እግዚአብሔር የሠራውን ሕግና ሥርዓት ተማረ። አባት ያሮክላም ዲቁና በእስክንድርያ ሾመው ከዚያም በኋላ ዲዮናስዮስ ቅስና ሾመው በተሾመባት ሁሉ ላይ ተጠምዶ የሚያገለግልና የሚጋደል ሆነ። አባ ዲዮናስዮስም በዐረፈ ጊዜ አዋቂዎች ኤጲስቆጶሳትና ካህናት ማኅበሩም ሁሉ መረጡት በእግዚአብሔርም በፈቃድ በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት። ❤ ዲዮናስዮስም ስለ ጳውሎስ ሳምሳጢ በአንጾኪያ ከተማ የተጀመረው የኤጲስቆጶሳት ማኅበር ጉባኤ ተጀምሮ ሳይፈጸም ዐረፈ። ይህም አባት መክሲሞስ በተሾመበት ወንበር በተቀመጠ ጊዜ በማኅበሩ ጉባኤ ስለ ተወሰነውና ከሀዲው ጳውሎስ ሳምሳጢን እንደአወገዙት በጉባኤው ሹማምንት መልክቶች ወደርሱ ደረሱ። በትምርቱ ያመኑትንም መልክቶቹንም ካህናቱ በአንድነት በተሰበሰቡበት አነበበው። ከዚያም በኋላ ዳግመኛ ከራሱ መልእክቶችን ጽፎ የጳውሎስ ሳምሳጢን ስሕተት ያርቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲጸልዩና እንዲማልዱ እያዘዘ ወደ ግብጽ አገሮች ሁሉ ወደ ኢትዮጵያና ወደ ኖባ አገር ላካቸው። የክብር ባለቤት ጌታችን ልመናቸውን ተቀበለ ይህም ከሀዲ ከጥቂት ቀኖች በቀር አልኖረም በፍጥነት አጠፋው እንጂ የረከሰች ሃይማኖትንም ከዓለም አስወገደ አራቀ። ❤ በዚህም አባት ዘመን ከምሥራቅ አገር ማኒ የሚባል ራሱን የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስን ያደረገና ክፉ ስሕተትን የሳተ ሰው ተገለጠ። ወደ ሶርያ ምድርም ደረሰ አርኬላዎስ የሚባል ኤጲስቆጶስም ከእርሱ ጋራ ተከራከረ ስሕተቱንም ገላልጦበት አሳፍሮ ከአገሩ አሳደደው። ከዚያም ተመልሶ ወደ ፋርስ ሔደ ራሱንም ነቢይ አደረገ የፋርስ ንጉሥ ብህራምም ይዞ ከሁለት ሠነጠቀው። ተከታዮቹ የሆኑ ሁለት መቶ ሰዎችን ዘቅዝቆ እስከ ወገባቸው በምድር ውስጥ ተከላቸው እነሆ ከሰው አትክልትን ተከልሁ አለ። ❤ ይህም አባት መንጋውን በመጠበቅ ሲጋደልና በቀናች ሃይማኖትም ሲያጸናቸው ኖረ ከመናፍቃንና ከከሀዲያን ችግር እስከ አረፈባት ቀን ድረስ በድርሳናትና በተግሣጻት ጠብቆ አዳናቸው። በቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ ስድስት ዓመት ኑሮ ሚያዝያ14 ቀን በሰላም ዐረፈ። የአባ መክሲሞስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ14 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ሰላም_ለመክሲሞስ_ልዑል። በመንበረ #ማርቆስ_ሰባኬ_ወንጌል። ዕሩቅ ትስብእት እምተዋሕዶ ቃል። በትምህርተ ካህድ ለብእሲ ዘይብል። መጽሐፈ ግዘት አንበረ በኵ ደውል"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_14።              

🥀ማክሰኞ #ቶማስ 🥀ቅዱስ ቶማስ በጦር የተወጋ ጎኑን፤ በቀኖት የተቸነከረው እጁንና እግሩን ካላየሁ አላምንም በማለቱ #ክርስቶስም «ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና ወደ ጎኔ አግባ፤ እመን እንጂ ተጠራጣሪ አትሁን» ብሎታል። ቶማስም «ጌታዬ አምላኬም»፤ ብሎ በመለሰ ጊዜ #ጌታችን_ኢየሱስም «ስለ አየኸኝ አመንህን? ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓንስ ናቸው» አለው (ዮሐ ፳፥፳፯-፳፱)፤ ቶማስ የ #ጌታን ፍቅር ተገንዝቦ ትንሣኤውን ስላመነ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዕለቱን ቶማስ ብላ ታስበዋለች። 🥀ዲዲሞስ የተባለ ከአሥራ አንዱ ደቀ መዛሙር አንዱ ቶማስ #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በዝግ ቤት ገብቶ «ሰላም ለሁላችሁ ይሁን» ባላቸው ጊዜ ከእርሳቸው ጋራ አልነበረም»። ከ፲፪ቱ ሐዋርያት አንዱ (ማቴ. ፲፥፪-፫) ቶማስ በአራማይክ ዲዲሞስ በግሪክ መንታ ማለት ነው፤ (ዮሐ. ፳፥፳፬)፡፡ ቶማስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በፋርስና በሕንድ ወንጌልን እንዳስተማረ ይነገራል። ለቶማስ ጎኑን እንዲዳስስ የፈቀደው ለሌሎችም ቅዱሳን ሐዋርያት የተቸነከረውን እጅና እግሩን ያሳየው ካህናት ሥጋውና ደሙን እንዲፈትቱ ነው፤ ዮሐንስም በእጃችን ዳሰስነው ብሏል፤ (ሉቃ. ፳፬፥፴፱)፡፡ 🥀ለማርያም መግደላዊት ግን የተነሣ ዕለት አትንኪኝ ማለቱ ለሴቶች ሥጋውን ደሙን መፈተት አልተፈቀደም ሲል ነው ብለው ሊቃውንት ያትታሉ፤ «አትንኪኝ፤ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሂጅና፡- ወደ አባቴ÷ ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬ÷ ወደ አምላካችሁም አርጋለሁ አለ ብለሽ ንገሪአቸው» አላት፤ (ዮሐ. ፳፥፲፯)። ገቦ መለኮቱን የዳሰሰች እጁ በሕይወት ትኖራለች፤ በሕንድ ሀገር ከታቦት ጋር በመንበር ላይ ትኖራለች። በየዓመቱ በ #እመቤታችን በዓል በአስተርእዮ ሊያጥኑ ሲገቡ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች፤ ዓመት አገልግሎ ያርፋል።

🍂  ሰኞ  ✨ #ማዕዶት ✨   ዐደወ = ተሻገረ     ማዕዶት = መሻገር                                 ✨ዛሬ ሰኞ የፋሲካ ማግስት ማዕዶት የሚል ስያሜ በቤተ-ክርስቲያን ተሰጥቶታል ትርጓሜውም መሻገር ማለት ነው። እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበትን ቀን ነው ፋሲካ ብለው  የሚያከብሩት እግዚአብሔር በሙሴ አማካይነት በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ባሕረ ኤርትራን ከፍለው እስራኤላውያን ተሻግረው ፈርኦንን ከነሰራዊቱ አስጥመው ወደ ዘለአለማዊ እረፍት ምድር ከነዓን ገብተዋል ይኽ ምሳሌ ነው ሙሴ የክርስቶስ በትር የመስቀል ባሕረ ኤርትራ የሲኦል ፈርኦን እና ሰራዊቱ የዲያብሎስ እስራኤላውያን የምዕመናን ምሳሌ ናቸው ክርስቶስ በመስቀል ተሰቅሎ ሲኦልን ከፍቶ አዳምን እና ልጆቹን አሻግሮ ዲያቢሎስን በሲኦል አስጥሞ ምዕመናንንበተድላ ገነት በምስጋናና በእልልታ አኑሯቸዋል።  በዚያምጊዜ የእስራኤል ልጆች ይህንን መዝሙር ለእግዚአብሔር  ዘምረዋል እንዲህም ብለው ተናግረዋል ። #በክብር_ከፍ_ከፍ_ብሎአልና_ለእግዚአብሔር_እዘምራለው ፤ #ፈረሱንና_ፈረሰኛውን_በባሕር_ጣለ ።     .     .     . ✨የፈርዖንን ሰረገሎች ሠራዊቱንም በባሕር ጣላቸው።                  ( ዘጸ 15 ፥ 1 , 4 )    👉 በመንገድም ይጠብቃቸውም ዘንድ መጋቤ ብሉይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ይራዳቸው ነበር። ( ዘጸ 23 ፥ 19 ) 🍀 ይህንንም በዓል የፋሲካ ( የመሻገር ) በዓል ብለው በየአመቱ ያከብሩ ነበር እሥራኤላውያን። ✨ ከግብጽ ነጻ ቢወጡ ፤ ፈርኦን ከሠራዊቱ በባሕር በሲጥም ፣ የኤርትራን ባሕር ተሻግረው ከነዓን ቢገቡም፤   #ዘላለማዊ_ዕረፍትን_ግን_አላገኙም ። የሲኦልን ባሕር አልተሻገሩም ፤ ከዲያብሎስም አገዛዝ ነጻ አልወጡም።    🍂    +    +     +     +   +   🍂 ዘመኑ ሲደርስ በመጀመሪያው ፋሲካ በምሳሌ የተገለጸው        #አማናዊው_ፋሲካችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ +          እውነተኛውን መሻገር አሻገረን።  +         ከሞት ወደ ሕይወት ፣ +          ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ፣    +     ከጨለማ ወደ ብርሃን መለሰን ።   ✨   ከግብጽ ከመሻገራቸው አስቀድሞ ስለ ታረደው ስለ ፋሲካው በግ አማናዊው ፋሲካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ ታርዶ ከሲኦል አንደ ተሻገርን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲል አለ። " #ፋሲካችን_ክርስቶስ_ታርዷልና"         ( 1ኛ ቆሮ  5 ፥ 7 ) 🙏 ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል                  ድል መንሣትን       ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን 🙏             ( 1ኛ  ቆሮ 15 ፥ 55 - 57 )

🔴🔴🔴 "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጉታላችሁ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም" ሉቃ፦24፥5 እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሕያው ከሙታን መካከል ይኖር ዘንድ ይቻለዋልን? ቅዱስ ጳውሎስ  "ብንኖር ለጌታ ነው ብንሞትም ለጌታ ነው"  እንዳለ በክርስቶስ ያለን እኛ ሕያው እንሆን ዘንድ ተጠርተናል። 🔴 ውድ የፍኖተ ብርሃን ልጆች በአገልግሎታችን የሚገጥሙንን ችግሮች ከኛ ፍላጎት ይልቅ የክርስቶስን ዓላማና ፍላጎት በማስቀደም። እንዲሁም ክርስቶስን ከልብ በመውደድ፤ ጥላቻንና መናናቅን አርቀን አገልግሎታችን ሙሉ ይሆን ዘንድ ዕለት ተዕለት ልንተጋ ይገባል። ውድ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሰው በየቀኑ የሚወለድ በየቀኑ ደግሞ በስራው የሚሞነገር ግን ሕያው ይሆን ዘንድ የተፈጠረ ነው። እናም ሕያውነታችንን ለማስጠበቅ በአገልግሎታችን ተግተን ፈጣሪ ከላይ ሊሰጠን ካቀደው ፀጋና በረከት እንዳንጎድል በቅንነት እናገልግል ዘንድ ለማስታወስ እንወዳለን። ። ። ። የትንሳኤው በረከት አይለየን። አሜን🙏 የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ፅ/ ቤት