ሜዳሊክስ
Ir al canal en Telegram
672
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-2530 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
enero '25
enero '250
en 0 canales
diciembre '24
+4
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+3
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+9
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+5
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+570
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+623
en 1 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 25 enero | 0 | |||
| 24 enero | 0 | |||
| 23 enero | 0 | |||
| 22 enero | 0 | |||
| 21 enero | 0 | |||
| 20 enero | 0 | |||
| 19 enero | 0 | |||
| 18 enero | 0 | |||
| 17 enero | 0 | |||
| 16 enero | 0 | |||
| 15 enero | 0 | |||
| 14 enero | 0 | |||
| 13 enero | 0 | |||
| 12 enero | 0 | |||
| 11 enero | 0 | |||
| 10 enero | 0 | |||
| 09 enero | 0 | |||
| 08 enero | 0 | |||
| 07 enero | 0 | |||
| 06 enero | 0 | |||
| 05 enero | 0 | |||
| 04 enero | 0 | |||
| 03 enero | 0 | |||
| 02 enero | 0 | |||
| 01 enero | 0 |
Publicaciones del Canal
ማንችስተር ሲቲ ነጥብ ጥሏል !
በአስራ ስምንተኛ ሳምንት የፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንችስተር ሲቲ ከኤቨርተን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
የማንችስተር ሲቲን ግብ በርናርዶ ሲልቫ ከመረብ ማሳረፍ ሊችል ለኤቨርተን ንዲያዬ አስቆጥሯል።
በጨዋታው የማንችስተር ሲቲው የፊት መስመር ተጨዋች ኤርሊንግ ሀላንድ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀም ቀርቷል።
ማንችስተር ሲቲ ካለፉት አስራ ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጨዋታ ነው ዘጠኙን በሽንፈት አጠናቋል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
6️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 28 ነጥብ
1️⃣5️⃣ ኤቨርተን :- 17 ነጥብ
ቀጣይ መርሐ ግብር ?
እሁድ - ሌስተር ሲቲ ከ ማንችስተር ሲቲ
እሁድ - ኤቨርተን ከ ኖቲንግሀም ፎረስት
| 2 | ማን.ሲቲ 1 - 2 ማን.ዩናይትድ | 241 |
| 3 | ማንቹንያን ደርቢ 🔥
ማን ያሸንፋል ????? | 265 |
| 4 | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ውጤት
🏟️ ሲቲ ግራውንድ
ኖቲንግሀም ፎረስት 2 - 1 አስቶን ቪላ | 236 |
| 5 | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ውጤቶች
🏟️ ኢምሬትስ
አርሰናል 0 - 0 ኤቨርተን
🏟️አንፊልድ ሮድ
ሊቨርፑል 2 - 2 ፉልሀም
🏟️ሴንት ጀምስ ፓርክ
ኒውካስል ዩናይትድ 4 - 0 ሌሲስተር ሲቲ
🏟️ሞሊኒክስ
ወልቭስ 1 - 2 ኢፕስዊች ታውን
https://t.me/Medalichs
https://t.me/Medalichs | 228 |
| 6 | ማን ያሸንፋል ?? | 322 |
| 7 | ሊቨርፑል መሪነቱን አጠናክሯል !
በአስራ ሶስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከማንችስተር ሲቲ ጋር ያደርጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት አሽንፈዋል።
የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች መሐመድ ሳላህ እና ኮዲ ጋክፖ ከመረብ አሳርፈዋል።
ማንችስተር ሲቲ አራተኛ ተከታታይ የፕርሚየር ሊግ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።
መሐመድ ሳላህ በውድድር አመቱ አስራ አንደኛ የፕርሚየር ሊግ ግቡን ከመረብ አሳርፏል።
ግብፃዊው የፊት መስመር ተጨዋች መሐመድ ሳላህ በውድድር አመቱ በሊጉ 1️⃣7️⃣ የግብ ተሳትፎዎችን በማድረግ ቀዳሚው ተጨዋች ሆኗል።
ሊቨርፑሎች በፕርሚየር ሊጉ ያለመሸነፍ ግስጋሴያቸውን ወደ ዘጠኝ ጨዋታ ከፍ ማድረግ ችለዋል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
1⃣ ሊቨርፑል - 34 ነጥብ
5️⃣ ማንችስተር ሲቲ - 23 ነጥብ
ቀጣይ መርሐ ግብር ?
ረቡዕ - ኒውካስል ከ ሊቨርፑል
ረቡዕ - ማንችስተር ሲቲ ከ ኖቲንግሃም ፎረስት | 385 |
| 8 | በቫሌንሽያ ማራቶን አትሌት መገርቱ አለሙ አሸነፈች
በ44ኛው የቫሌንሺያ ማራቶን አትሌት መገርቱ አለሙ በቀዳሚነት አጠናቃለች።
የ27 ዓመቷ አትሌት ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2:16:49 ፈጅቶባታል።መገርቱ በውድድሩ መሀል ህመም ተሰምቷት የነበረ ቢሆንም ከማሸነፍ እንዳላገዳት ተናግራለች።
አትሌት መገርቱ በቫሌንሽያ ማራቶን ያሸነፈች 12ኛዋ ኢትዮጵያዊት ሴት አትሌት ሆናለች።
በውድድሩ ኬንያዊቷ አትሌት ሰቴላ ቼሳንግ በሁለተኝነት እንዲሁም አትሌት ጥሩዬ መስፍን በሶስተኝነት አጠናቀዋል።
በወንዶቹ ውድድር አትሌት ደረሰ ገለታ በ2:02:38 በሁለተኝነት አጠናቋል።
በርቀቱ ጭምዴሳ ደበሌ 6ኛ ፣ ሲሳይ ለማ 10ኛ እንዲሁም ብርሀኑ ለገሰ የ11ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል። | 307 |
| 9 | ሩድ ቫን ኒስትሮይ የሌሲስተር ሲቲ ዋና አሰልጣኝ በመሆን ተሹሟል። | 257 |
| 10 | ሊቨርፑል ከ ሪያል ማድሪድ ⚽
👉12ኛ የእርስ በርስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ
👉ሪያል ማድሪድ ካለፉት 11 ግንኙነቶች በ7 አሸንፏል
👉ሊቨርፑል በመጀመሪያ ሶስቱ የእርስ በርስ ጨዋታዎች ካሸነፈ በኋላ ማሸነፍ አልቻለም
👉ሊቨርፑል ሪያል ማድሪድን ካሸነፈ 15 ዓመታት ተቆጥረዋል
ዛሬስ ማይ ያሸንፍ ይሆን ???
ሁለቱ የቻምፒየንስ ሊግ ሀያላን በደማቁ በውቡ አንፊልድ ሮድ በቀያዮቹ ደጋፊዎች ፊት ይጫወታሉ።
You will never waik alone ከፍ ብሎ ሲሰማ Hala Madrid በተጓዥ ደጋፊዎች ይዘመራል።
ቀይ ላባሹ በአርን ስሎት መሪነት በፀጥታ የድል ግስጋሴውን አስቀጥሏል። በቻምፒየንስ ሊጉ ብቸኛው ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈው ቡድን ነው።
ኮንትራት እናራዝምልህ አላሉኝም ብሎ በአፉ ያኮረፈው በእግሩ ግን ክለቡን ተሸክሞ እየተጓዘ ያለው ሞ ሳላህ ለሊቨርፑላውያን የደስታ ምንጭ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
ቪኒሲየስ እና ሮድሪጎን በጉዳት ያጣው ነጭ ለባሹ ሪያል ማድሪድ ለታዳጊዎቹ ኮከቦች አርዳ ጉለር እና ኤንድሪክ የመሰለፍ እድል እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
ወትሮም እንደ ኢትዮጵያዊያን ሯጮች አቀዝቅዞ ጀምሮ መጨረሻ ላይ ዙሩን በራሱ የሚያከረው ማድሪድ አጃማመሩ የሰመረ አልሆነም። ሁለት ድል ሁለት ሽንፈት።
ሆኖም ግን ይህ የእርሱ ውድድር ነው። ከተከታዩ ክለቡ ከእጥፍ በላይ ዋንጫዎችን አሳክቶበታል።
ቀዘቀዘ ከሰመ ሲባል በእንደዛሬ ምሽቱ አይነት ጨዋታዎች አንገቱን ቀና አድርጎ መታየትም ያውቅበታል።
ታላቁ አንፊልድ ይህን ታላቅ ጨዋታ 5:00 ጀምሮ ያስተናግዳል።
ሳላህ ወይስ ምባፔ ..... ዞቦስላይ ወይስ ቤሊንግሀም....ቫን ዳይክ ወይስ ሩዲገር...... አርን ስሎት ወይስ ካርሎ አንቾሎቲ ????
ቀዩ ጦር🔴 ወይስ ነጩ ወራሪ⚪️ | 283 |
| 11 | ሲቲ ዛሬም .....🤔
እስከ 74ኛ ደቂቃ ፌይኖርድን 3 - 0 ሲመራ የነበረው ሲቲ 3 - 3 ጨዋታውን አጠናቋል። የጋርድዮላም ቅዠት ቀጥሏል።
ፔፕ አይቶት የማያውቀው ቀውስ ውስጥ ገብቷል። በማያውቀው ዓለም ረዘም ላሉ ቀናት ለመቆየትም ተገዷል።
በአርን ስሎት የቀድሞ ቡድን በካም ባክ ነጥብ የተጋራው የፔፕ ውሀ ሰማያዊ ቡድን እሁድ ደግሞ ከአሁኑ የአርን ስሎት ቡድን ሊቨርፑል ጋር ትልቅ ፈተና ይጠብቀዋል።
ምን ይውጠው ይሆን ?? | 237 |
| 12 | የ2024/25 የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ይጀምራሉ | 262 |
| 13 | የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት የሚወዳደሩ ዕጩዎች ይፋ ሆኑ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ለመምራት የሚወዳደሩ አምስት የመጨረሻ ዕጩዎችን ይፋ ሆነዋል።
ዕጩዎቹ ከስድስት ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች የተወከሉ ናቸው።
ከትግራይ ክልል አትሌት ገ/እግዚአብሔር ገ/ማርያም ፣ ከአማራ ክልል አቶ ያየህ አዲስ ፣ ከኦሮሚያ ክልል አትሌት ስለሺ ስህን ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ኮ/ር ግርማ ዳባ ፣ ከድሬዳዋ አቶ ጌቱ ገረመው እንዲሁም ከአዲስ አበባ አቶ ዱቤ ጅሎ ናቸው።
ለስራ አስፈፃሚ አባልነትም ዕጩዎች ይፋ ሲሆኑ ከሶማሌ ክልል እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ውጪ ሁሉም ክልሎች የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ሁለት ሁለት ዕጩዎችን አቅርበዋል።
የፕሬዚዳንት እና የስራ አስፈፃሚ ምርጫው ታህሳስ 12 - 13/2017 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በሚካሄደው የፌዴሬሽኑ 28ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ይደረጋል። | 242 |
| 14 | የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በፌስ ቡክ አይተላለፉም!
ትላንት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች በሊጉ አክስዮን ማህበር ፌስ ቡክ አልተላለፉም ፡፡ ብዙ ተመልካቾችም ለ ስፖርት ዞን-Sport Zone ከመኳንት እና ከሰዒድ ጋር ሬድዮ ፕሮግራም ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡
የሱፐር ስፖርት የቀጥታ ስርጭት በ2ተኛው ሳምንት ካቆመ በኋላ የሊጉ አክስዮን በማህበራዊ የፌስ ቡክ ገጹ በአንድ ካሜራ ጨዋታዎችን ያስተላልፍ እንደነበር ይታወቃል፡፡
አክስዮን ማህበሩ ለምስል ባለመብቱ DSTV በደብዳቤ አስቀድሞ ፍቃድ የጠየቀ ሲሆን ከቀናት በፊት ምላሹን አግኝትዋል፡፡
የሊጉ ጨዋታዎች ከሱፐር ስፖርት ውጭ በምንም አይነት ማሰራጫ መተላለፍ እንደሌለበት Dstv ገልጽዋል፡፡በመሆኑም ከዚህ በኋላ በፌስ ቡክ ምንም አይነት ጨዋታ ስርጭት አይኖርም፡፡
Dstv በአመቱ በአጠቃላይ 70 ጨዋታዎችን ለማስተላለፍ ውል የገባ ሲሆን 16 ጨዋታዎች እስካሁን ተላልፈዋል፡፡ቀሪዎቹ ጨዋታዎች መች እንደሚተላለፋ የተረጋገጠ ነገር የለም፡፡ | 144 |
| 15 | የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የዛሬ ምሽት ጨዋታዎች | 184 |
| 16 | ማርቲን ኦዲጋርድ ....
👉ከተጫዋቾቹ ምርጡ ጎደኛክ
ካይ ሀቨርዝ
👉የከበደከ ተጋጣሚ ተጫዋች
ቫን ዳይክ
👉አብረኸው ለመጫወት የተመኘከው
ልዮኔል ሜሲ
https://t.me/Medalichs
https://t.me/Medalichs | 207 |
| 17 | "ለአጥቂዎች የሚሆን የጨዋታ መንገድ የለንም"
አሰልጣኝ ታዲዮስ ተክሉ
አሸናፊ ብሄራዊ ቡድን ለመገንባት አሸናፊ የጨዋታ መንገድ ወይም ሐሳቡ አስፈላጊ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ20 ዓመት በታች ቡድን አሰልጣኝ ታድዮስ ተክሉ ተናግሯል።
አሰልጣኙ ይህን የጨዋታ ሐሳብ ወደ መሬት ያወረደ እና ተግባራዊ አድርጎ ለተመልካች ማሳየት የሚችል አሰልጣኝ ምርጥ ሊባል እንደሚችልም ያስረዳል።
አሰልጣኝ ታዲዮስ ጥሩ የጨዋታ መንገድን ለመገንባት ለአሰልጣኝ ጊዜ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ በሁለት ጨዋታዎች ላይ የጨዋታ ሐሳባቸውን መመልከቱን እንዲሁም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የተረዳው መንገድ መኖሩን ይናገራል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአሰልጣኞች ጊዜ በመስጠት የበኩሉን እንዲወጣ መልዕክቱን አስተላልፏል።
የጀርመን ብሄራዊ ቡድንን በምሳሌነት በመጥቀስ የዓለም ዋንጫን ለማሳካት ከ10 ዓመት በፊት አቅደው በዛ መሰረት ሰርተው ማሳካታቸውን እና የጨዋታ መንገዳቸውን ቀይረው እንደነ ኦዚል ዓይነት ትውልድ ማፍራታቸውን ተናግሯል።
ብሔራዊ ቡድኑ ጨራሽ አጥቂ የለውም ተብሎ በሚነሳው ሀሳብ ላይም አሰልጣኙ እንደማይስማማ ይናገራል።
ከበፊትም ጀምሮ ሰለሃዲን ሰኢድ እና ጌታነህ ከበደ ጥሩ አቋም ላይ በነበሩበት ቡድን ውስጥ ሽንፈት ሲመጣ የአጥቂ እና ግብ ጠባቂ ችግር እንደምክንያት ይነሳ ነበር ብሏል።
አክሎም ከዛ ይልቅ ላሉት አጥቂዎች የሚሆን የጨዋታ መንገድ አለ ብሎ እንደማያስብ አስረድቷል።
ችግሩ የክለቦች የአፍሪካ መድረክ ውድድር ላይም ጎል የማግባት ችግር ብቻ ሳይሆን ጎልም በቀላሉ ስለሚቆጠር እንደ አጠቃላይ የጨዋታ መንገድ ላይ ቢሰራ ችግሮችን መቅረፍ እንደሚቻል አስረድቷል፡፡
https://t.me/Medalichs | 186 |
| 18 | አምስት ክለቦች ዮኬሬሽን ለመከታተል ጠይቀዋል !!
የስፖርቲንግ ሊዝበኑን የፊት አጥቂ ቪክተር ዮኬሬሽን ለማስፈረም በርካታ ክለቦች ፍላጎት እንዳላቸው ይታወቃል።
ይህንን ተጫዋች በጥር አልያም በክረምት ለማስፈረም የሚፈልጉ አምስት ክለቦች የተጫዋቹን እንቅስቃሴ ለመከታተል መልማዮቻቸውን ወደ ሊዝበን እንደሚልኩ ተረጋግጧል።
ባርሴሎና ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ ፣ ማንችስተር ሲቲ ፣ ማንችስተር ዩናይትድ እና ባየር ሙኒክ ስፖርቲንግ ሊዝበን አርሰናልን በሚገጥምበት ጨዋታ ላይ ለመልማዮቻቸው የስታድየም ወንበር የጠየቁ ክለቦች ናቸው።
ስዊድናዊው አጥቂ ቪክተር ዮኬሬሽ በውድድር ዓመቱ ገና ከአሁኑ 30 ግቦችን አስቆጥሯል።
👉ይህን ድንቅ አጥቂ የትኛው ክለብ ያስፈርመዋል ብለው ያስባሉ ??
https://t.me/Medalichs
https://t.me/Medalichs | 155 |
| 19 | "....በሲቲ የመጨረሻ ዓመቴ ይሆናል"
ኬቨን ደ ብሩይን
ቤልጅየማዊው የማንችስተር ሲቲ ድንቅ ተጫዋች ኬቨን ዴ ብሩይን በማንችስተር ሲቲ ቆይታው ዙሪያ እርግጠኛ አለመሆኑን ተናግሯል።
ተጫዋቹ እንዳለው ከሆነ ንግግሮች ይኖራሉ ብሎ አስባለሁ ከሌሉ ግን ይህ በክለቡ የመጨረሻ ዓመቴ ይሆናል ሲል ተናግሯል።
ዓመቱ ሲጀመር ንግግሮች ይኖራሉ ብሎ መጠበቁን ያልሸሸገው ደ ብሩይን ባስተናገደው ጉዳት ምክንያት ትኩረቱን ሙሉ ለሙሉ በማገገም ላይ ማድረጉን አሳውቋል።
ከ2015 ጀምሮ ለማንችስተር ሲቲ በመጫወት ላይ ያለው የ32 ዓመቱ ተጫዋች ከሲቲ ጋር ያለው ውል በዓመተ መጨረሻ ይጠናቀቃል።
👉ኬቨን ደ ብሩይን ከማንችስተር ሲቲ ከተለያየ ወደ የት ያመራል ብለው ያስባሉ ??
https://t.me/Medalichs
https://t.me/Medalichs | 124 |
| 20 | 913 ግቦች - ክርስትያኖ ሮናልዶ
ክርስትያኖ ሮናልዶ ቡድኑ አል ናስር ወደ ኳታር አምርቶ ከ ባደረገው የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል።
የአምስት ጊዜ የባሎን ዲኦር አሸናፊው ሮናልዶ በተጫዋችነት ዘመኑ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶችም 913 ማድረስ ችሏል።
በ2024 ዓመተ ምህረት ብቻ በክለብ እና ብሔራዊ ቡድን ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶችም 40 አድርሷል።
በተጨማሪም 30 ዓመት ከሞላው በኋላ 550ኛ የግብ ተሳትፎ አድርጓል።
👉ሮናልዶ ኳሶ ሳያቆም 1000ኛ ግቡን ያስቆጥር ይሆን ??
https://t.me/Medalichs
https://t.me/Medalichs | 152 |
